1 ዜና መዋዕል 14 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 14:1-17

የዳዊት ቤትና ቤተ ሰቡ

14፥1-7 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥11-161ዜና 3፥5-8

1በዚህ ጊዜ የጢሮስ ንጉሥ ኪራም ለዳዊት ቤተ መንግሥት እንዲሠሩ መልክተኞችን፣ ድንጋይ ጠራቢዎችንና ዐናጢዎችን ከዝግባ ዕንጨት ጋር ላከ። 2ዳዊትም እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ አንግሦ እንዳጸናውና ስለ ሕዝቡም ስለ እስራኤል ሲል መንግሥቱን ከፍ ከፍ እንዳደረገለት አስተዋለ።

3ዳዊትም በኢየሩሳሌም ብዙ ሚስቶች አገባ፤ ከእነርሱም ወንዶችንና ሴቶች ልጆችን ወለደ። 4በዚያ ሳለ የወለዳቸው የልጆቹ ስም ይህ ነው፤ ሳሙስ፣ ሶባብ፣ ናታን፣ ሰሎሞን፣ 5ኢያቤሐር፣ ኤሊሱዔ፣ ኤሊፋላት፣ 6ኖጋ፣ ናፌቅ፣ ያፍያ፣ 7ኤሊሳማ፣ ኤሊዳሄ፣ ኤሊፋላት።

ዳዊት ፍልስጥኤማውያንን ድል አደረገ

14፥8-17 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 5፥17-25

8ዳዊት በእስራኤል ሁሉ ላይ ተቀብቶ መንገሡን ፍልስጥኤማውያን በሰሙ ጊዜ፣ እርሱን ፍለጋ በሙሉ ኀይላቸው ወጡ፤ ዳዊት ይህን ሰምቶ ስለ ነበር ሊገጥማቸው ወጣ። 9በዚህ ጊዜ ፍልስጥኤማውያን መጥተው የራፋይምን ሸለቆ ወረሩ። 10ስለዚህ ዳዊት፣ “ወጥቼ በፍልስጥኤማውያን ላይ አደጋ ልጣልን? አንተስ በእጄ አሳልፈህ ትሰጣቸዋለህን?” ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ።

እግዚአብሔርም፣ “አዎን ውጣ! በእጅህ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ” ብሎ መለሰለት።

11ስለዚህ ዳዊትና ሰዎቹ ወደ በኣልፐራሲም ወጡ፤ በዚያም ድል አደረጋቸው። ዳዊትም፣ “ውሃ ነድሎ እንደሚወጣ ሁሉ እግዚአብሔርም ጠላቶቼን በእጄ አፈረሳቸው” አለ፤ ከዚህም የተነሣ ያን ቦታ “በኣልፐራሲም” ብለው ሰየሙት። 12ፍልስጥኤማውያን አማልክታቸውን በዚያው ጥለዋቸው ስለ ነበር፣ ዳዊት በእሳት እንዲያቃጥሏቸው አዘዘ።

13ፍልስጥኤማውያን ሸለቆውን እንደ ገና ወረሩ፤ 14ዳዊትም እንደ ገና እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል መለሰለት “ዙሪያውን ከብበህ በሾላው ዛፍ ፊት ለፊት አደጋ ጣልባቸው እንጂ በቀጥታ ወደ ላይ አትውጣ፤ 15በሾላው ዐናት ላይ የሰልፍ ድምፅ ስትሰማ ወዲያውኑ ለጦርነት ውጣ፤ ይህም የፍልስጥኤማውያንን ሰራዊት ለመምታት እግዚአብሔር በፊትህ ወጥቷል ማለት ነውና።” 16ስለዚህ ዳዊት እግዚአብሔር እንዳለው አደረገ፤ ከገባዖን ጀምሮ እስከ ጌዝር ድረስ ፍልስጥኤማውያንን መቷቸው።

17ከዚህም የተነሣ የዳዊት ዝና በየአገሩ ሁሉ ተሰማ፤ እግዚአብሔርም መንግሥታት ሁሉ እንዲፈሩት አደረገ።

Swedish Contemporary Bible

1 Krönikeboken 14:1-17

David i Jerusalem

(2 Sam 5:11-16; 1 Krön 3:5-8)

1Kung Hiram i Tyros skickade budbärare till David med stockar av cederträ och murare och snickare för att bygga Davids palats. 2Nu förstod David att Herren hade befäst hans kungadöme och upphöjt det för hans folk Israels skull.

3David tog sig fler hustrur i Jerusalem och blev far till fler söner och döttrar. 4De söner som föddes i Jerusalem hette Shammua14:4 Shima i 3:5., Shovav, Natan, Salomo, 5Jivchar, Elishua, Elpelet, 6Nogah, Nefeg, Jafia, 7Elishama, Beeljada och Elifelet.

David besegrar filistéerna

(2 Sam 5:17-25)

8Filistéerna fick höra att David var smord till kung över hela Israel, och de gav sig ut efter honom. Men David fick höra om det och drog ut mot dem. 9Filistéerna for fram och plundrade i Refaimdalen. 10Då frågade David Gud: ”Ska jag dra ut mot filistéerna? Kommer du att överlämna dem åt mig?” Herren svarade: ”Ja, gå! Jag ska överlämna dem åt dig!”

11Då gick David till anfall vid Baal-Perasim och slog filistéerna där. David sa: ”Gud har brutit ner mina fiender genom min hand, liksom vatten som bryter fram.” Det är därför platsen kallas Baal-Perasim14:11 En anspelning på det hebreiska ordet för genombrott, Gud bryter fram..

12Filistéerna hade övergett sina gudar på platsen, och David gav order om att de skulle brännas upp.

13Men filistéerna återkom och plundrade dalen igen, 14och David frågade Gud även denna gång.

”Du ska inte gå efter dem, utan ta en omväg runt bakaträden”, svarade Gud, ”och anfall dem sedan från det hållet. 15Gå till attack när du hör ljudet som av en här på marsch i trädtopparna. Då har Gud gått före dig för att slå filistéernas armé.” 16David gjorde som Gud hade befallt honom, och han slog filistéernas armé och förföljde den från Givon ända till Geser.

17Davids ryktbarhet spred sig till alla länder, och Herren lät alla folk bäva för honom.