2 ነገሥት 1 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 1:1-18

የእግዚአብሔር ፍርድ በአካዝያስ ላይ

1አክዓብ ከሞተ በኋላ ሞዓብ በእስራኤል ላይ ዐመፀ። 2በዚህ ጊዜ አካዝያስ በሰማርያ ካለው እልፍኝ ሰገነቱ ላይ ሳለ፣ ከዐይነ ርግቡ ሾልኮ ወድቆ ነበርና ታመመ፤ ስለዚህ፣ “ሄዳችሁ ከዚህ ሕመም እድን እንደ ሆነ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ጠይቁ” ሲል መልእክተኞች ላከ።

3የእግዚአብሔር መልአክ ግን ቴስብያዊውን ኤልያስን እንዲህ አለው፤ “ተነሥተህ የሰማርያን ንጉሥ መልእክተኞች ለመገናኘት ውጣና፣ ‘የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ የምትሄዱ በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን?’ ብለህ ጠይቃቸው። 4ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።’ ” ከዚያም ኤልያስ ሄደ።

5መልእክተኞቹ ወደ ንጉሡ ሲመለሱ እርሱም፣ “ለምን ተመልሳችሁ መጣችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

6እነርሱም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ “አንድ ሰው ሊገናኘን መጥቶ፣ ‘ወደ ላካችሁ ንጉሥ ተመልሳችሁ ሂዱና፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ ሰዎች የምትልከው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ስለዚህ ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።” ’ ”

7ንጉሡም፣ “ለመሆኑ ሊገናኛችሁ መጥቶ እንዲህ ያላችሁ ሰው እንዴት ያለ ነው?” ሲል ጠየቃቸው።

8እነርሱም “ሰውየው ጠጕራም ልብስ የለበሰ ነው፤ በወገቡም ላይ ጠፍር ታጥቋል” አሉት።

ንጉሡም፣ “ዐወቅሁት፤ ቴስብያዊው ኤልያስ ነው” አላቸው።

9ከዚያም ንጉሡ አንድ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ወታደሮቹ ጋር ወደ ኤልያስ ላከ። የአምሳ አለቃውም ኤልያስ ወደ ተቀመጠበት ኰረብታ ጫፍ ወጥቶ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

10ኤልያስም መልሶ የአምሳ አለቃውን፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ፣ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ አንተንና አምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው። ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ የአምሳ አለቃውንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

11እንደ ገናም ንጉሡ ሌላ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ፤ የአምሳ አለቃውም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘አሁኑኑ ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

12ኤልያስም መልሶ፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ እሳት ከሰማይ ወርዳ አንተንና ሃምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው፤ ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ እርሱንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

13ስለዚህም ንጉሡ ሦስተኛውን የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ። ይህም ሦስተኛው የአምሳ አለቃ ወጥቶ፣ በኤልያስ ፊት በጕልበቱ ተንበርክኮ እንዲህ ሲል ለመነ፤ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ እባክህ የእኔና የእነዚህ የአምሳዎቹ አገልጋዮችህ ነፍስ በፊትህ የከበረች ትሁን። 14እነሆ፤ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ የፊተኞቹን ሁለት አምሳ አለቆችና ሰዎቻቸውን ሁሉ በላች፤ አሁን ግን ሕይወቴ በፊትህ የከበረች ትሁን።”

15የእግዚአብሔርም መልአክ ኤልያስን፣ “አብረኸው ውረድ፤ ደግሞም አትፍራው” አለው። ስለዚህ ኤልያስ ተነሣ፤ አብሮትም ወደ ንጉሡ ወረደ።

16ንጉሡንም፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለመሆኑ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ስለ ራስህ ለመጠየቅ መልእክተኞች የላክኸው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ይህን በማድረግህም ከተኛህበት ዐልጋ ፈጽሞ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ’ ” ብሎ ነገረው። 17ስለዚህ አካዝያስ ኤልያስ እንደ ተናገረው እንደ እግዚአብሔር ቃል ሞተ።

አካዝያስ ወንድ ልጅ ስላልነበረው፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮራም በይሁዳ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ወንድሙ ኢዮራም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ። 18ሌላው አካዝያስ በዘመኑ ያከናወናቸውና የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፉ አይደለምን?

Swedish Contemporary Bible

2 Kungaboken 1:1-18

Avslutningen av Elias uppdrag

Achasjas konfrontation med Elia

1När Achav var död, gjorde Moabs folk uppror mot Israel.

2En dag föll Achasja ner från sin sal på övre våningen i Samaria och skadade sig. Han sände bud till Baal Sebub, guden i Ekron, för att fråga om han skulle bli frisk igen.

3Men då kom en Herrens ängel och sa till Elia från Tishbe: ”Gå och möt sändebuden från kungen i Samaria och fråga dem om det är sant att det inte finns någon Gud i Israel, eftersom de går till Baal Sebub, guden i Ekron, för att fråga honom. 4Därför säger Herren: ’Du kommer inte att lämna sängen du ligger i, utan du ska dö.’ ” Så gick Elia.

5Sändebuden återvände genast till kungen.

”Varför är ni redan tillbaka?” undrade han. 6”Där var en man som kom fram till oss”, svarade de. ”Han sa till oss att gå tillbaka till kungen som sänt oss och säga: ’Så säger Herren: Finns det ingen Gud i Israel, eftersom du skickar bud för att fråga Baal Sebub, guden i Ekron, om råd? Därför kommer du aldrig att få lämna sängen du ligger i, utan du ska dö.’ ”

7”Vad var det för en man, som mötte er och sa detta?” frågade kungen. 8”Han hade en mantel av hår och ett läderbälte om höfterna”, svarade de. ”Det var Elia från Tishbe”, sa kungen.

9Han skickade genast en officer med femtio man till Elia. Denne kom upp till honom och fann Elia sittande högst uppe på en kulle. ”Du gudsman, kungen har befallt att du ska komma ner”, sa officeren till honom.

10”Om jag är en gudsman, så ska eld komma ner från himlen och utplåna dig och dina femtio man”, svarade Elia. Omedelbart slog blixten ner och dödade dem allesammans.

11Kungen skickade då ytterligare en officer med femtio man. ”Du gudsman”, ropade officeren till honom. ”Kungen säger att du omedelbart måste komma ner!”

12Men Elia svarade som förut: ”Om jag är en gudsman, så ska eld komma ner från himlen och döda dig och dina femtio man.” Och än en gång kom Guds eld från himlen, och han och hans femtio man förintades.

13För tredje gången skickade kungen iväg en officer med femtio man. Den här gången föll officeren på knä för Elia och vädjade till honom: ”Du gudsman, skona mitt liv och de här femtio männens, som är dina tjänare! 14Eld kom ner från himlen och förtärde de två första officerarna med deras män. Men skona nu mitt liv!”

15Då sa Herrens ängel till Elia: ”Var inte rädd utan följ med dem!” Elia lydde då ängeln och följde med dem till kungen.

16”Så säger Herren: Var det därför att det inte finns någon Gud i Israel som du kan fråga, som du skickade bud till Baal Sebub, guden i Ekron?” frågade Elia kungen. ”Därför ska du inte komma upp ur sängen du ligger i, utan du ska dö.”

17Achasja dog, precis som Herren hade förutsagt genom Elia, och hans bror Joram blev kung efter honom, eftersom Achasja inte hade någon son. Det här skedde under Jorams, Joshafats sons, andra regeringsår över Juda.

18Achasjas historia i övrigt, vad han gjorde, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.