1 ነገሥት 22 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 22:1-53

ሚክያስ በአክዓብ ላይ ትንቢት ተናገረ

22፥1-28 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥1-27

1በሶርያና በእስራኤል መካከል ለሦስት ዓመት ጦርነት አልነበረም። 2በሦስተኛው ዓመት ግን የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ የእስራኤልን ንጉሥ ለመጐብኘት ወረደ። 3የእስራኤልም ንጉሥ ሹማምቱን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት የእኛ ሆና ሳለች፣ ከሶርያው ንጉሥ እጅ ለመመለስ ምንም እንዳላደረግን አታውቁምን?” አላቸው።

4ስለዚህ ኢዮሣፍጥን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት ላይ ለመዝመት አብረኸኝ ለመሄድ ትፈቅዳለህን?” ሲል ጠየቀው።

ኢዮሣፍጥም፣ “እኔ ያው እንደ አንተው ነኝ፤ ሕዝቤ እንደ ሕዝብህ፣ ፈረሶቼም እንደ ፈረሶችህ ናቸው” አለ። 5ኢዮሣፍጥም የእስራኤልን ንጉሥ፣ “በመጀመሪያ ግን የእግዚአብሔርን ሐሳብ ጠይቅ” አለው።

6ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ አራት መቶ ነቢያትን በአንድነት ሰብስቦ፣ “በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ልዝመት ወይስ ልተው?” ሲል ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዝመትባት” አሉት።

7ኢዮሣፍጥ ግን፣ “የምንጠይቀው የእግዚአብሔር ነቢይ እዚህ የለምን?” አለ።

8የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “መኖሩንማ በእርሱ አማካይነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምንጠይቀው አንድ ሰው አሁንም አለ፤ ነገር ግን ምንጊዜም ቢሆን ስለ እኔ ክፉ እንጂ አንዳችም መልካም ትንቢት ተናግሮ ስለማያውቅ እጠላዋለሁ፤ ይህም ሰው የይምላ ልጅ ሚክያስ ነው” አለ። ኢዮሣፍጥም፣ “ንጉሡ እንዲህ ማለት አይገባውም” ሲል መለሰ።

9ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ከሹማምቱ አንዱን ጠርቶ፣ “በል የይምላን ልጅ ሚክያስን በፍጥነት አምጣው” አለው።

10የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ አልባሰ መንግሥታቸውን ለብሰው፣ በሰማርያ ቅጥር በር አጠገብ ባለው አውድማ ላይ በየዙፋናቸው ተቀምጠው ሳለ፣ ነቢያቱ ሁሉ በፊታቸው ትንቢት ይናገሩ ነበር።

11በዚህ ጊዜ ሴዴቅያስ የተባለው የክንዓና ልጅ የብረት ቀንዶች አበጅቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሶርያውያን እስኪጠፉ ድረስ የምትወጋቸው በእነዚህ ነው’ ” አለው።

12የቀሩትም ነቢያት ሁሉ፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን ወግተህ ድል አድርግ” በማለት በአንድ ቃል ትንቢት ይናገሩ ነበር።

13ከዚያም ሚክያስን ሊጠራ የሄደው መልእክተኛ፣ “እነሆ፤ ሌሎቹ ነቢያት ንጉሡ ድል እንደሚያደርግ በአንድ ቃል ትንቢት እየተናገሩለት ነውና የአንተም ቃል ከእነርሱ ጋር አንድ እንዲሆን እባክህ መልካም ነገር ተናገር” አለው።

14ሚክያስ ግን፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ለእርሱ የምነግረው እግዚአብሔር የነገረኝን ብቻ ነው” አለ።

15እዚያም እንደ ደረሰ ንጉሡ፣ “ሚክያስ ሆይ፤ በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ እንዝመትባት ወይስ እንተው?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዘምተህ ድል አድርጋት” ብሎ መለሰለት።

16ንጉሡም፣ “ከእውነት በቀር በእግዚአብሔር ስም አንዳች ነገር እንዳትነግረኝ የማምልህ ስንት ጊዜ ነው?” አለው።

17ከዚያም ሚክያስ እንዲህ ሲል መለሰ፣ “እስራኤል ሁሉ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በየተራራው ላይ ተበትነው አየሁ፣ እግዚአብሔርም፣ ‘ይህ ሕዝብ ጌታ የለውም፤ እያንዳንዱ በሰላም ወደየቤቱ ይሂድ’ አለ።”

18የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “ስለ እኔ ክፉ ብቻ እንጂ ከቶ መልካም ትንቢት አይናገርም አላልሁህምን?” አለው።

19ከዚያም ሚክያስ እንዲህ አለ፤ “እንግዲህ የእግዚአብሔር ቃል የሚለውን ስማ፤ እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ፣ የሰማይ ሰራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ፤ 20እግዚአብሔርም፣ ‘በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ዘምቶ እዚያው እንዲሞት፣ አክዓብን ማን ያስተው?’ አለ።

“ታዲያ አንዱ ይህን፣ ሌላውም ያን አለ፤ 21በመጨረሻም፣ አንድ መንፈስ ወጣ፤ ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ፣ ‘እኔ አስተዋለሁ’ አለ።

22እግዚአብሔርም፣ ‘እንዴት አድርገህ?’ ሲል ጠየቀው።

“እርሱም፣ ‘እኔ እወጣለሁ፤ በገዛ ነቢያቱም አፍ ሁሉ የሐሰት መንፈስ እሆናለሁ’ አለ።

እግዚአብሔርም፣ ‘በል እንግዲያው ውጣና አስተው፤ ይሳካልሃል’ አለው።

23“ስለዚህ እነሆ እግዚአብሔር በእነዚህ ሁሉ ነቢያትህ አፍ የሐሰት መንፈስ አኖረ፤ በአንተም ላይ መዓቱን እንደሚያመጣብህ ተናገረ።”

24ከዚያም የክንዓና ልጅ ሴዴቅያስ ወጥቶ ሚክያስን በጥፊ መታውና፣ “ለመሆኑ የእግዚአብሔር መንፈስ ከእኔ በየት በኩል ዐልፎ ነው አንተን መጥቶ ያናገረህ?” ሲል ጠየቀው።

25ሚክያስም፤ “ይህንማ ለመደበቅ ወደ አንዲት እልፍኝ በሄድህ ዕለት ታውቀዋለህ” አለው።

26ከዚያም የእስራኤል ንጉሥ እንዲህ ሲል አዘዘ፤ “በሉ ሚክያስን ይዛችሁ ወደ ከተማዪቱ ገዥ ወደ አሞንና ወደ ንጉሡ ልጅ ወደ ኢዮአስ መልሱት፤ 27ከዚያም፣ ‘ንጉሡ፣ በደኅና እስክመለስ ድረስ፣ ይህን ሰው በእስር ቤት አቈዩት፤ ከደረቅ እንጀራና ከውሃ በስተቀር ሌላ እንዳትሰጡት’ ብሏል በሉት” አለ።

28ሚክያስም፣ “አንተ በደኅና ከተመለስህ እግዚአብሔር በእኔ አልተናገረማ!” አለ፤ ከዚያም በመቀጠል፣ “በዚህ ያለኸው ሕዝብ ሁሉ ይህን ቃሌን ልብ ብለህ ያዘው፤” አለ።

አክዓብ በገለዓድ በምትገኘው በሬማት ተገደለ

22፥29-36 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥28-34

29ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በገለዓድ ወደምትገኘው ሬማት ወጡ። 30የእስራኤል ንጉሥ ኢዮሣፍጥን፣ “እንዳልታወቅ እኔ ልብስ ለውጬና ሌላ ሰው መስዬ እገባለሁ፤ አንተ ግን ልብሰ መንግሥትህን ልበስ” አለው። ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ራሱን ደብቆ ወደ ጦርነቱ ገባ።

31በዚህ ጊዜ የሶርያ ንጉሥ ሠላሳ ሁለቱን የሠረገላ አዛዦች፣ “ከራሱ ከእስራኤል ንጉሥ በቀር ትንሽም ይሁን ትልቅ ከማንም ጋር እንዳትገጥሙ” ሲል አዝዟቸው ነበር፤ 32የሠረገላ አዛዦቹ ኢዮሣፍጥን ሲያዩት፣ “ያለ ጥርጥር ይህ የእስራኤል ንጉሥ ነው” አሉ፤ ስለዚህ አደጋ ሊጥሉበት ከበቡት፤ ኢዮሣፍጥ ሲጮህ ግን 33የሠረገላ አዛዦቹ እርሱ የእስራኤል ንጉሥ አለመሆኑን ዐውቀው መከታተሉን ተዉት።

34ነገር ግን አንዱ ቀስቱን ሳያልም እንዲሁ ሲያስፈነጥር በጦር ልብሱ መጋጠሚያ ላይ የእስራኤልን ንጉሥ ወጋው፤ ንጉሡም ሠረገላ ነጂውን፣ “ቈስያለሁና ወደ ኋላ አዙረህ ከጦሩ ሜዳ አውጣኝ” አለው። 35ጦርነቱም ቀኑን ሙሉ ተፋፍሞ ዋለ፤ በዚህ ጊዜም ንጉሡ በሶርያውያን ፊት ለፊት ሠረገላው ላይ ቀና ብሎ እንደ ተደገፈ ነበር፤ የቍስሉ ደም በሠረገላው ወለል ላይ ይወርድ ነበር፤ በዚያኑ ዕለት ማታም ንጉሡ ሞተ። 36ፀሓይ ስትጠልቅም በሰራዊቱ መካከል፣ “እያንዳንዱ ሰው ወደ ቤቱ፣ እያንዳንዱም ወደ ሀገሩ ይሂድ!” የሚል ጩኸት አስተጋባ።

37ንጉሡ ስለ ሞተም ወደ ሰማርያ አምጥተውት እዚያው ተቀበረ። 38ሠረገላውንም አመንዝሮች በታጠቡበት በሰማርያ22፥38 ወይም፣ የጦር መሣሪያ በሚታጠብበት በሰማርያ ተብሎ መተርጐም ይችላል ኵሬ ዐጠቡት፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ቃል ደሙን ውሾች ላሱት።

39ሌላው በአክዓብ ዘመነ መንግሥት የተፈጸመውና ያደረገው ሁሉ፣ ቤተ መንግሥቱን መሥራቱና በዝኆን ጥርስ መለበጡ እንዲሁም የሠራቸው የምሽግ ከተሞች በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 40አክዓብም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ አካዝያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ

22፥41-50 ተጓ ምብ – 2ዜና 20፥31–21፥1

41የእስራኤል ንጉሥ አክዓብ በነገሠ በአራተኛው ዓመት የአሳ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ነገሠ። 42ኢዮሣፍጥ ሲነግሥ ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ነበር፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱ ዓዙባ ትባላለች፤ እርሷም የሺልሒ ልጅ ነበረች። 43በአካሄዱም ሁሉ የአባቱን የአሳን መንገድ ተከተለ፤ ከዚያች ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን አደረገ፤ ይሁን እንጂ በየኰረብታው ላይ ያሉትን የማምለኪያ ቦታዎች አላጠፋም፤ ሕዝቡም በዚያ መሥዋዕት ይሠዋ፣ ዕጣንም ያጥን ነበር። 44እንዲሁም ኢዮሣፍጥ ከእስራኤል ንጉሥ ጋር በሰላም ኖረ።

45ሌላውም ኢዮሣፍጥ በዘመነ መንግሥቱ የፈጸመው፣ ያከናወነውና ያደረገው ጦርነት ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 46ከአባቱ ከአሳ ዘመን በኋላ እንኳ ተርፈው በጣዖት ማምለኪያ ቦታዎች የነበሩትን የወንደቃ ቅሬታዎች ከምድሪቱ አስወገደ። 47በዚያን ጊዜ ኤዶም ንጉሥ አልነበራትም፤ የሚገዛት እንደራሴ ነበር።

48ኢዮሣፍጥ ወርቅ ለማምጣት ወደ ኦፊር የሚሄዱ የንግድ መርከቦች22፥48 ዕብራይስጡ የተርሴስ መርከቦች ይላል አሠርቶ ነበር፤ ይሁን እንጂ በዔጽዮንጋብር ስለ ተሰበሩ ከቶ ወደዚያ መሄድ አልቻሉም ነበር። 49በዚያን ጊዜም የአክዓብ ልጅ አካዝያስ ኢዮሣፍጥን “ሰዎቼ ከሰዎችህ ጋር በመርከብ ይሂዱ” ሲል ጠይቆት ነበር፤ ኢዮሣፍጥ ግን እሺ አላለውም።

50ኢዮሣፍጥ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እነርሱ በተቀበሩበት በአባቱ በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ ኢዮራምም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የእስራኤል ንጉሥ አካዝያስ

51የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በነገሠ በዐሥራ ሰባተኛው ዓመት የአክዓብ ልጅ አካዝያስ የእስራኤል ንጉሥ ሆኖ በሰማርያ ነገሠ፤ እስራኤልንም ሁለት ዓመት ገዛ። 52እርሱም የአባቱንና የእናቱን፣ እንዲሁም እስራኤልን ያሳተውን የናባጥን ልጅ የኢዮርብዓምን መንገድ በመከተሉ፣ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ክፉ ሥራ ሠራ። 53አባቱ እንዳደረገው ሁሉ፣ እርሱም በኣልን አመለከ፤ ሰገደለትም። በዚህም የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ እንዲነሣሣ አደረገ።

Swedish Contemporary Bible

1 Kungaboken 22:1-54

Joshafat lierar sig med Achav

(2 Krön 18:1-27)

1Under tre år var det inte några krig mellan Aram och Israel. 2Men under det tredje året, när kung Joshafat av Juda besökte kungen av Israel, 3sa Israels kung till sina ämbetsmän: ”Har ni tänkt på att Ramot i Gilead tillhör oss? Och här sitter vi utan att göra någonting åt för att ta det från Arams kung!”

4Sedan vände han sig till Joshafat och frågade: ”Vill du dra ut med mig mot Ramot i Gilead?” ”Ja”, svarade Joshafat. ”Det ska jag, jag likväl som du, och mitt folk likväl som ditt folk, mina hästar tillsammans med dina. 5Men”, tillade Joshafat till den israelitiske kungen, ”låt oss först fråga Herren till råds.” 6Då kallade Israels kung samman profeterna, fyrahundra man, och frågade dem: ”Ska jag dra ut i strid mot Ramot i Gilead, eller ska jag låta bli?” De svarade: ”Gå, för Herren ska överlämna den i kungens hand.”

7Men Joshafat frågade: ”Finns det inte någon mer Herrens profet här, som vi också kan fråga?” 8”Jo”, svarade Israels kung Joshafat, ”det finns en till som kan rådfråga Herren åt oss, men honom hatar jag, för han profeterar aldrig något gott för mig, utan bara ont. Det är Mika, Jimlas son.” ”Kungen bör inte tala så”, svarade Joshafat.

9Israels kung kallade då till sig en av sina tjänstemän. ”Skynda dig och hämta hit Mika, Jimlas son”, befallde han.

10Israels kung och Joshafat, Juda kung, satt på var sin tron i sina kungliga kläder på tröskplatsen vid Samarias stadsport, och alla profeterna profeterade inför dem.

11Sidkia, Kenaanas son, gjorde sig horn av järn och förklarade: ”Så säger Herren: Du ska stånga Aram med dessa horn tills de förgörs.” 12Alla de andra profeterade detsamma: ”Ja, anfall Ramot i Gilead och du ska lyckas, för Herren kommer att överlämna staden i kungens hand.”

13Budbäraren, som hade gått för att kalla på Mika, berättade för honom: ”Profeterna förkunnade med en mun framgång för kungen. Låt nu också dina ord stämma med deras och lova framgång!” 14Men Mika svarade: ”Så sant Herren lever, jag ska bara säga honom det Herren säger till mig!”

15När han kom fram inför kungen, frågade denne honom: ”Mika, ska vi dra ut i strid mot Ramot i Gilead, eller ska jag låta bli?” Och Mika svarade: ”Gå, och du ska lyckas, för Herren ska överlämna staden i kungens hand!” 16Kungen sa till honom: ”Hur många gånger måste jag besvärja dig att inte tala något annat än sanning i Herrens namn?”

17Då svarade Mika: ”Jag såg hela Israel förskingrat på bergen, som får utan herde. Och Herren sa: ’De har ingen herre. Låt dem återvända hem i fred, var och en till sitt.’ ”

18Israels kung sa till Joshafat: ”Var det inte det jag sa? Han profeterar inte något gott för mig, utan bara ont.”

19Mika fortsatte: ”Hör här vad Herren säger! Jag såg Herren sitta på sin tron, och himlens hela härskara stod på bägge sidorna om honom. 20Herren sa: ’Vem kan locka Achav att gå ut i strid mot Ramot i Gilead och stupa där?’ Då sa den ene si och den andre så. 21Då kom en ande fram och ställde sig inför Herren och sa: ’Jag kan locka honom.’ ’Hur?’ frågade Herren honom. 22Han svarade: ’Jag ska gå och bli en lögnens ande i munnen på alla kungens profeter.’ Herren svarade: ’Locka honom, du! Du kommer att lyckas. Gå och gör så!’ 23Herren har alltså lagt en lögnens ande i munnen på alla dessa dina profeter, för Herren har bestämt att olycka ska drabba dig.”

24Då gick Sidkia, Kenaanas son, fram och slog Mika i ansiktet. ”Skulle Herrens Ande ha lämnat mig för att tala till dig?” frågade han. 25”Det ska du komma underfund med den dag du går för att gömma dig i det innersta rummet”, svarade Mika.

26Israels kung befallde: ”Arrestera Mika och för honom tillbaka till styresmannen Amon och till kungens son Joash, 27och säg till dem: ’Så säger kungen: Sätt den här mannen i fängelse på vatten och bröd tills jag kommer välbehållen tillbaka.’ ”

28Mika svarade: ”Om du kommer välbehållen tillbaka, så har Herren inte talat genom mig.” Sedan tillade han: ”Hör detta, alla folk22:28 Jfr Mika 1:2!”

Achav dör på slagfältet

(2 Krön 18:28-34)

29Israels kung och Joshafat, Juda kung, tågade nu mot Ramot i Gilead.

30Israels kung sa till Joshafat: ”Jag ska förklä mig och dra ut i striden, men du kan bära dina egna kläder.” Israels kung drog alltså ut i striden förklädd.

31Nu hade Arams kung gett order till sina trettiotvå vagnsofficerare att inte ge sig i strid mot någon annan än Israels kung. 32När vagnsofficerare fick syn på Joshafat, tänkte de: ”Det här är Israels kung.” De omringade honom för att anfalla honom, men när Joshafat ropade till, 33märkte de att det inte var Israels kung och slutade att förfölja honom. 34Men någon spände sin båge och sköt på måfå och träffade Israels kung i en springa i rustningen. Kungen sa till kusken: ”Vänd vagnen och ta mig ut ur striden! Jag är sårad.”

35Striden blev allt intensivare ju längre dagen led. Kungen stod kvar i sin vagn, vänd mot araméerna. Blodet från hans sår rann ner på vagnsgolvet, och när kvällen kom dog han.

36Just som solen höll på att gå ner, ljöd ett rop bland trupperna: ”Låt var och en gå hem till sin stad och sitt land!” 37Kungen var alltså död, och hans kropp fördes till Samaria, där han begravdes. 38De sköljde hans vagn vid dammen i Samaria, där de prostituerade brukade bada, och hundar kom och slickade i sig kungens blod, precis som Herren hade förutsagt.

39Achavs historia i övrigt, vad han gjorde och elfenbenspalatset och städerna som han byggde, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.

40Så dog alltså Achav och gick till vila hos sina förfäder. Hans son Achasja efterträdde honom som kung.

Joshafat regerar i Juda

(2 Krön 20:31—21:1)

41Under Achavs fjärde regeringsår i Israel blev Joshafat, son till Asa, kung i Juda. 42Joshafat var trettiofem år gammal när han blev kung, och han regerade i tjugofem år i Jerusalem. Hans mor var Asuva, dotter till Shilchi. 43Joshafat följde sin far Asa utan att vika av från den vägen och gjorde det som var rätt inför Herren. 44Ändå blev offerhöjderna kvar, och folket fortsatte att offra och bränna rökelse där. 45Han slöt också fred med Achav, kungen i Israel.

46Joshafats historia i övrigt, vad han gjorde och alla hans hjältemodiga krig, finns nedtecknat i Juda kungars krönika.

47Han avskaffade också det som fanns kvar av manlig prostitution sedan hans far Asas tid.

48Det fanns inte någon kung i Edom vid den här tiden, bara en ställföreträdande regent22:48 Den hebreiska benämningens innebörd är osäker..

49Joshafat byggde Tarshish-fartyg som skulle segla till Ofir för att hämta guld, men de kom aldrig dit, eftersom de led skeppsbrott vid Esjon-Gever. 50Achasja, Achavs son, föreslog Joshafat att deras män skulle segla tillsammans, men Joshafat accepterade inte det.

51Joshafat dog och begravdes bland sina förfäder i sin förfader Davids stad. Hans son Joram blev kung efter honom.

Achasja regerar i Israel

52Det var under Joshafats sjuttonde regeringsår i Juda som Achasja, Achavs son, blev kung över Israel i Samaria, och han regerade över Israel i två år. 53Men han gjorde det som var ont i Herrens ögon, för han följde i sina föräldrars och i Jerobeams, Nevats sons, fotspår och förledde Israel till synd. 54Han tjänade och tillbad Baal och väckte Herrens, Israels Guds, vrede, precis som hans far hade gjort.