1 ነገሥት 21 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 21:1-29

የናቡቴ የወይን ተክል ቦታ

1ከጥቂት ጊዜ በኋላ በኢይዝራኤላዊው በናቡቴ የወይን ተክል ቦታ ላይ አንድ ነገር ደረሰ፤ ቦታውም በኢይዝራኤል ውስጥ ከሰማርያ ንጉሥ ከአክዓብ ቤተ መንግሥት አጠገብ ነበር። 2አክዓብም ናቡቴን፣ “የወይን ተክል ቦታህ ከቤተ መንግሥቴ አጠገብ ስለሆነ፣ የአትክልት ቦታ እንዳደርገው ልቀቅልኝ፤ በምትኩ ከዚህ የበለጠ የወይን ተክል ቦታ እሰጥሃለሁ፤ የተሻለ ሆኖ ከታየህም የሚያወጣውን ገንዘብ እከፍልሃለሁ” አለው።

3ናቡቴ ግን፣ “ዐፅመ ርስቴን እለቅልህ ዘንድ እግዚአብሔር አይበለው” ሲል መለሰለት።

4ኢይዝራኤላዊው ናቡቴ፣ “ዐፅመ ርስቴን አልለቅልህም” ስላለው፣ አክዓብ ተበሳጭቶና ተቈጥቶ ወደ ቤቱ ገባ፤ አኵርፎም በዐልጋው ላይ ተኛ፤ ምግብም መብላት ተወ።

5ሚስቱ ኤልዛቤልም ወደ እርሱ ገብታ፣ “እስከዚህ የተበሳጨኸው፣ ምግብስ የማትበላው ለምንድን ነው?” ብላ ጠየቀችው።

6እርሱም፣ “ኢይዝራኤላዊውን ናቡቴን፣ ‘የወይን ተክል ቦታህን ሽጥልኝ፤ ከፈለግህም በምትኩ ሌላ የወይን ቦታ እሰጥሃለሁ’ አልሁት፤ እርሱ ግን፣ ‘የወይን ተክል ቦታዬን አልለቅልህም’ ስላለኝ ነው” አላት።

7ሚስቱ ኤልዛቤልም፣ “አንተ አሁን የእስራኤል ንጉሥ ትባላለህ? በል ተነሥና እህል ቅመስ፤ ደስም ይበልህ፤ የኢይዝራኤላዊውን የናቡቴን የወይን ተክል ቦታ እኔ እንድታገኝ አደርግሃለሁ” አለችው። 8ስለዚህ በአክዓብ ስም ደብዳቤዎች ጻፈች፤ በገዛ ማኅተሙም ዐትማ በናቡቴ ከተማ አብረውት ለሚኖሩ ሽማግሌዎችና መኳንንት ላከች። 9በደብዳቤዎቹም ላይ እንዲህ ስትል ጻፈች፤

“የአንድ ቀን ጾም ዐውጁ፤ ናቡቴንም በሕዝቡ መካከል ከፍ ባለ ቦታ ላይ አስቀምጡት። 10እንዲሁም ሁለት የሐሰት ምስክሮች ከፊት ለፊቱ አስቀምጡና፣ ‘እግዚአብሔርንም ንጉሡንም ሰድቧል’ ብለው ይመስክሩበት፤ ከዚያም አውጥታችሁ በድንጋይ ወግራችሁ ግደሉት።”

11ስለዚህ በናቡቴ ከተማ የሚኖሩ ሽማግሌዎችና መኳንንት በደብዳቤዎቹ ላይ እንደ ጻፈችላቸው አደረጉ። 12የአንድ ቀን ጾም ዐወጁ፤ ናቡቴንም በሕዝቡ መካከል ከፍ ባለ ቦታ ላይ አስቀመጡት። 13ከዚያም ሁለት የሐሰት ምስክሮች መጥተው ከፊት ለፊቱ ተቀመጡ፤ በሕዝቡም ፊት፣ “ናቡቴ እግዚአብሔርንና ንጉሡን ሰድቧል” ብለው መሰከሩበት። ስለዚህ ከከተማዪቱ ውጭ ወስደው በድንጋይ ወግረው ገደሉት። 14ከዚያም ለኤልዛቤል፣ “ናቡቴ በድንጋይ ተወግሮ ሞቷል” ብለው ላኩባት።

15ኤልዛቤልም በድንጋይ ተወግሮ መሞቱን ወዲያው እንደ ሰማች አክዓብን፣ “ናቡቴ በድንጋይ ተወግሮ ሞቷል፤ በል ተነሣና ኢይዝራኤላዊው ናቡቴ ሊሸጥልህ ያልፈለገውን የወይን ተክል ቦታ በርስትነት ውሰደው” አለችው። 16አክዓብ የናቡቴን ሞት ሲሰማ የናቡቴን የወይን ተክል ቦታ በርስትነት ለመያዝ ተነሥቶ ወረደ።

17ከዚያም የእግዚአብሔር ቃል ወደ ቴስብያዊው ወደ ኤልያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 18“ተነሣና በሰማርያ ሆኖ የሚገዛውን የእስራኤልን ንጉሥ አክዓብን ትገናኝ ዘንድ ውረድ፤ የናቡቴን የወይን ተክል ቦታ በርስትነት ለመያዝ ሄዶ አሁን እዚያው ይገኛል። 19እንዲህም በለው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ሰውየውን ገደልኸው፤ ደግሞ ርስቱን ልትወስድ?’ ከዚያም እንዲህ በለው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ውሾች የናቡቴን ደም በላሱበት ቦታ የአንተንም ደም ውሾች እንዲሁ ይልሱታል!’ ”

20አክዓብም ኤልያስን፣ “ጠላቴ ሆይ አገኘኸኝን?” አለው።

ኤልያስም መልሶ እንዲህ አለው፤ “በእግዚአብሔር ፊት የተጠላውን ነገር ለማድረግ ራስህን ሸጠሃልና አዎን አግኝቼሃለሁ። 21‘እነሆ ክፉ ነገር አመጣብሃለሁ፤ ዘርህን ፈጽሜ አጠፋለሁ፤ ባሪያም ይሁን ነጻ እያንዳንዱን የአክዓብን የመጨረሻ ወንድ ልጅ ከእስራኤል እጠርጋለሁ። 22ለቍጣ ስላነሣሣኸኝና እስራኤልንም ስላሳትሃቸው፣ ቤትህን እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮርብዓም ቤት፣ እንደ አኪያም ልጅ እንደ ባኦስ ቤት አደርገዋለሁ።’

23“ስለ ኤልዛቤልም እግዚአብሔር፣ ‘በኢይዝራኤል ቅጥር አጠገብ21፥23 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ ቩልጌትና የሱርስቱ ትርጕም (2ነገ 9፥26 ይመ)፣ በዕርሻው ማሳ ላይ ይላሉ። ውሾች ኤልዛቤልን ይበሏታል’ ይላል።

24“ደግሞም ከአክዓብ ወገን ሆኖ በከተማ የሞተውን ውሾች ይበሉታል፤ በገጠር የሞተውንም የሰማይ አሞሮች ይበሉታል።”

25በሚስቱ በኤልዛቤል ተገፋፍቶ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ለማድረግ ራሱን የሸጠ እንደ አክዓብ ያለ ሰው ከቶ አልነበረም። 26እግዚአብሔር ከእስራኤል ፊት ያሳደዳቸው አሞራውያን እንዳደረጉት ሁሉ፣ እርሱም ጣዖታትን በማምለክ እጅግ የሚያስጸይፍ ርኩሰት ፈጸመ።

27አክዓብም ይህን ቃል ሲሰማ ልብሱን ቀደደ፤ ማቅ ለብሶ፤ ጾመ፤ በማቅ ላይ ተኛ በሐዘን ኵርምት ብሎም ይሄድ ነበር።

28ከዚያም እንዲህ የሚል የእግዚአብሔር ቃል ወደ ቴስብያዊው ወደ ኤልያስ መጣ፤ 29“አክዓብ ራሱን በፊቴ እንዴት እንዳዋረደ አየህን? ራሱን ስላዋረደ ይህን መከራ በዘመኑ አላመጣበትም፤ ነገር ግን ይህን በቤቱ ላይ የማመጣው በልጁ ዘመን ነው።”

Swedish Contemporary Bible

1 Kungaboken 21:1-29

Achav tar Navots vingård

1En tid därefter hände följande: Navot, en man från Jisreel, hade en vingård i utkanten av staden, inte långt från Samarias kung Achavs palats. 2Achav talade till Navot: ”Låt mig få din vingård! Jag vill ha den till trädgård, eftersom den ligger så nära mitt palats.” Han erbjöd Navot en bättre vingård eller bra betalt, vilket han önskade.

3Men Navot svarade Achav: ”Herren förbjude att jag skulle ge dig mitt fädernearv.”

4Achav gick tillbaka hem missmodig och arg, eftersom Navot från Jisreel talat om för honom att han inte ville ge bort sitt fädernearv. Han vägrade att äta och gick och lade sig med ansiktet mot väggen.

5Hans hustru Isebel kom in och frågade: ”Vad är det som har fått dig på så dåligt humör? Varför äter du inte?”

6Han svarade: ”Jag talade med Navot från Jisreel och bad honom sälja sin vingård till mig, eller byta den mot annan mark, men han vägrade att ge mig sin vingård.”

7”Är det så här du agerar som kung i Israel?” frågade Isebel. ”Ät nu, och bekymra dig inte för den här saken! Jag ska ordna så att du får jisreeliten Navots vingård!”

8Hon skrev brev i Achavs namn, satte hans sigill på dem och skickade dem till de äldste och förnämsta i staden, där Navot bodde. 9I breven stod det:

”Utlys fasta. Låt Navot sitta på en hedersam plats. 10Skaffa fram två onda män, placera dem mittemot Navot och låt dem anklaga honom för att ha förbannat Gud och kungen. För sedan bort Navot och stena honom.”

11De äldste och förnämsta i Navots stad följde Isebels instruktioner och gjorde som hon skrivit i sina brev till dem. 12De utlyste en fasta och placerade Navot på en framskjuten plats. 13Två onda män anklagade honom för att ha förbannat Gud och kungen, och man förde Navot ut ur staden och stenade honom till döds. 14Sedan sände de ett meddelande till Isebel om att Navot var stenad till döds.

15När Isebel fick höra nyheten, sa hon till Achav: ”Nu kan du ta den där vingården, som jisreeliten Navot vägrade att sälja till dig. Han är inte längre i livet. Han är död.”

16Då Achav hörde att Navot var död gick han ner till vingården för att ta den i besittning.

17Men då kom Herrens ord till Elia från Tishbe: 18”Gå och sök upp Israels kung Achav i Samaria. Han är vid Navots vingård och håller på att lägga beslag på den. 19Säg till honom: ’Så säger Herren: ”Har du både mördat en man och tagit hans arv i besittning?” Så säger Herren: ”Hundarna ska slicka i sig ditt blod, på samma plats där de alldeles nyss slickade i sig Navots blod!” ’ ”

20”Jaså, min fiende har hittat mig!” sa Achav till Elia. ”Ja”, svarade Elia. ”Jag har funnit dig, för att du har sålt dig till att göra det som är ont i Herrens ögon. 21’Jag kommer att låta olycka drabba dig, utplåna dig, och jag ska inte låta någon manlig ättling till Achav, vare sig slav eller fri, få överleva. 22Jag tänker låta det gå med din familj på samma sätt som kung Jerobeams, Nevats sons, och kung Bashas, Achias sons, familjer, för du har gjort mig vred genom att locka Israel till synd.’ 23Herren har också talat om för mig att hundarna i Jisreel ska äta upp Isebel. 24De medlemmar av Achavs familj som dör inne i staden ska bli uppätna av hundar, och de som dör ute på landsbygden ska bli uppätna av fåglar.”

25Det var ingen som hade sålt sig till ondskan så som Achav och som uppmuntrades av sin hustru till det. 26Särskilt avskyvärt handlade han genom att tillbe avgudar, precis som amoréerna hade gjort, det folk som Herren hade fördrivit ut ur landet för Israels folks skull.

27När Achav hörde dessa ord rev han sönder sina kläder och klädde sig i säcktyg, fastade och sov i säcktyg och gick omkring utan att säga ett ord.

28Då kom Herrens ord till Elia från Tishbe: 29”Ser du hur Achav har ödmjukat sig inför mig? Därför att han ödmjukat sig så ska jag inte låta olyckan komma medan han lever, utan den kommer i stället att drabba hans ätt.”