1 ነገሥት 16 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 16:1-34

1ከዚያም የእግዚአብሔር ቃል በባኦስ ላይ እንዲህ ሲል ወደ አናኒ ልጅ ወደ ኢዩ መጣ፤ 2“ከትቢያ አንሥቼ፣ የሕዝቤ የእስራኤል መሪ አደረግሁህ፤ አንተ ግን በኢዮርብዓም መንገድ ሄድህ፤ ሕዝቤ እስራኤል ኀጢአት እንዲሠራ፣ በኀጢአቱም ለቍጣ እንዲያነሣሣኝ አሳሳትኸው። 3ስለዚህ ባኦስንና ቤቱን ፈጽሜ አጠፋለሁ፤ ቤትህንም እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮርብዓም ቤት አደርገዋለሁ። 4በከተማዪቱ ውስጥ የሚሞቱትን የባኦስን ወገኖች ሁሉ ውሾች ይበሏቸዋል፤ በገጠር የሚሞቱትንም ሁሉ የሰማይ አሞሮች ይቀራመቷቸዋል።”

5በባኦስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው፣ ሌላው ያደረገው ሥራው በሙሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 6ባኦስ፣ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በቴርሳም ተቀበረ። ልጁም ኤላ በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

7ከዚህም በቀር የእግዚአብሔር ቃል በነቢዩ ኢዩ አማካይነት በባኦስና በቤቱ ላይ የመጣበት ምክንያት፣ በእጁ ሥራ ያስቈጣው ዘንድ እንደ ኢዮርብዓም ቤት ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሥራን ሁሉ በማድረጉና ኢዮርብዓምን በማጥፋቱም ጭምር ነው።

የእስራኤል ንጉሥ ኤላ

8የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሃያ ስድስተኛው ዓመት የባኦስ ልጅ ኤላ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ በቴርሳ ተቀምጦም ሁለት ዓመት ገዛ።

9ከሹማምቱ አንዱና የግማሽ ሠረገሎቹ አዛዥ የሆነው ዘምሪ ዐምፆ ተነሣበት፤ በዚያን ጊዜ ኤላ በቴርሳ ከተማ የቤተ መንግሥቱ ኀላፊ በሆነው በአርጻ ቤት ጠጥቶ ሰክሮ ነበር፤ 10ዘምሪም ገብቶ ኤላን ገደለው፤ እርሱም በኤላ እግር ተተክቶ፣ የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሃያ ሰባተኛው ዓመት ነገሠ።

11ዘምሪ ወዲያው እንደ ነገሠና በዙፋን እንደ ተቀመጠ፣ የባኦስን ቤተ ሰብ በሙሉ ገደለ፤ የሥጋ ዘመድም ሆነ ወዳጅ አንድም ወንድ አላስቀረም። 12በዚህ ሁኔታም በነቢዩ በኢዩ አማካይነት በባኦስ ላይ በተነገረው በእግዚአብሔር ቃል መሠረት፣ የባኦስን ቤተ ሰብ ሁሉ ፈጀ።

13ይህም የሆነው ባኦስና ልጁ ኤላ፣ በማይረቡ ጣዖቶቻቸው ምክንያት የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ያስቈጡት ዘንድ በሠሩት ኀጢአት ሁሉና፣ እስራኤልም እንዲሠሩ በማድረጉ ነበር።

14ሌላው ኤላ በዘመኑ የፈጸመውና ያደረገው ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን?

የእስራኤል ንጉሥ ዘምሪ

15የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሃያ ሰባተኛው ዓመት ዘምሪ በቴርሳ ሆኖ ሰባት ቀን ብቻ ገዛ። በዚህ ጊዜ ሰራዊቱ የፍልስጥኤማውያን ከተማ የሆነችውን ገባቶንን ከብቦ ሰፍሮ ነበር። 16በዚያም ሰፈር የነበሩ እስራኤላውያን ዘምሪ ዐምፆ ንጉሡን መግደሉን እንደ ሰሙ፣ የሰራዊቱን አዛዥ ዖምሪን በዚያኑ ዕለት እዚያው ሰፈር ውስጥ በእስራኤል ላይ ማንገሣቸውን ዐወጁ። 17ከዚያም ዖምሪና አብረውት ያሉት እስራኤላውያን ሁሉ ከገባቶን ወደ ላይ ወጥተው ቴርሳን ከበቡ። 18ዘምሪ ከተማዪቱ መያዟን ሲያይ፣ ቤተ መንግሥቱ ውስጥ ወዳለው ግንብ ገብቶ በቤተ መንግሥቱ ላይ እሳት ለቀቀበትና በዚሁ ሞተ። 19ይህ የሆነውም በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ክፉ ሥራ በመሥራትና በኢዮርብዓም መንገድ በመሄድ፣ እንዲሁም ራሱ በሠራው ኀጢአትና እስራኤልም እንዲሠሩ ባደረገው ኀጢአት ምክንያት ነው።

20ሌላው ዘምሪ በዘመኑ የፈጸመው ድርጊትና ያካሄደውም ዐመፅ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን?

የእስራኤል ነጉሥ ዖምሪ

21ከዚያም የእስራኤል ሕዝብ ከሁለት ተከፈለ፣ ይህም ግማሹ የጎናትን ልጅ ታምኒን ለማንገሥ ሲሆን፣ የቀረው ደግሞ ዖምሪን በመደገፍ ነበር። 22ሆኖም የዖምሪ ተከታዮች ከጎናት ልጅ ከታምኒ ተከታዮች ይልቅ በረቱ፤ ስለዚህ ታምኒ ሞተ፤ ዖምሪም ነገሠ።

23የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሠላሳ አንደኛው ዓመት፣ ዖምሪ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ ዐሥራ ሁለት ዓመትም ገዛ፤ ከዚህም ውስጥ ስድስቱን ዓመት የገዛው በቴርሳ ሆኖ ነው። 24እርሱም የሰማርያን ኰረብታ በሁለት መክሊት16፥24 70 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ጥሬ ብር ከሳምር ላይ ገዝቶ ከተማ ሠራባት፤ ስሟንም በቀድሞው የተራራዋ ባለቤት በሳምር ስም ሰማርያ ብሎ ጠራት።

25ይሁን እንጂ ዖምሪ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ፤ ከእርሱ አስቀድሞ ከነበሩትም ይልቅ የበለጠ ኀጢአት ሠራ። 26እርሱም እስራኤል በማይረቡ ጣዖቶቻቸው፣ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ እንዲያነሣሡት ባደረገው በናባጥ ልጅ በኢዮርብዓም መንገድ ሁሉና እርሱም ኀጢአት ሠርቶ እስራኤልም እንዲሠሩ ባደረገው ኀጢአት ተመላለሰ።

27ሌላው ዖምሪ በዘመኑ የፈጸመው፣ ያደረገውና ያከናወነው ሁሉ በእስራኤል የነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 28ዖምሪ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በሰማርያም ተቀበረ፤ ልጁም አክዓብ በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

አክዓብ የእስራኤል ንጉሥ ሆነ

29የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሠላሳ ስምንተኛው ዓመት፣ የዖምሪ ልጅ አክዓብ በእስራኤል ላይ ነገሠ፣ በሰማርያም ሆኖ እስራኤልን ሃያ ሁለት ዓመት ገዛ። 30የዖምሪ ልጅ አክዓብ ከእርሱ አስቀድሞ ከነበሩት ሁሉ ይልቅ፣ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ። 31የናባጥን ልጅ የኢዮርብዓምን ኀጢአት እንደ ቀላል ነገር ከመቍጠሩም በላይ የሲዶናውያንን ንጉሥ የኤትበኣልን ልጅ ኤልዛቤልን አገባ፤ ሄዶም በኣልን አመለከ፤ ሰገደለትም። 32ሰማርያ ላይ በሠራውም የበኣል ቤተ ጣዖት ለበኣል መሠዊያ አቆመለት። 33ደግሞም አክዓብ የአሼራን ምስል ዐምድ በማቆም ከእርሱ በፊት ከነበሩት የእስራኤል ነገሥታት ይልቅ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ የሚያነሣሣ ድርጊት ፈጸመ።

34የቤቴል ሰው አኪኤል፣ በአክዓብ ዘመን ኢያሪኮን መልሶ ሠራት። እግዚአብሔር በነዌ ልጅ በኢያሱ አማካይነት የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ መሠረቷን ሲያኖር በኵር ልጁ አቢሮን ሞተ፤ የቅጽር በሮቿንም በሚሠራበት ጊዜ የመጨረሻው ልጁ ሠጉብ ሞተ።

Swedish Contemporary Bible

1 Kungaboken 16:1-34

1Herrens ord kom till Jehu, Hananis son, mot Basha:

2”Jag lyfte upp dig ur gruset för att göra dig till furste över mitt folk Israel, men du har vandrat på Jerobeams vägar. Du har fått mitt folk Israel att synda och mig att bli vred. 3Därför ska jag nu rensa bort Basha och hans familj, på samma sätt som jag gjorde med Jerobeam, Nevats son. 4De i Bashas familj som dör inne i staden ska bli uppätna av hundar, och de som dör ute på landsbygden ska bli mat åt fåglar.”

5Bashas historia i övrigt, vad han gjorde och hans erövringar finns nedtecknat i Israels kungars krönika. 6Basha dog och begravdes bland sina fäder i Tirsa. Hans son Ela blev kung efter honom. 7Genom profeten Jehu, Hananis son, kom Herrens ord till Basha och hans familj: på grund av allt det onda han hade gjort inför Herren, väckt hans vrede genom sina handlingar och förgjort Jerobeams familj, gick det för honom som för dennes familj.

Ela regerar i Israel

8Ela, Bashas son, blev kung i Israel under kung Asas tjugosjätte regeringsår i Juda, och han regerade i två år i Tirsa. 9Då anstiftade hans tjänare Simri, som hade befälet över hälften av stridsvagnarna, en sammansvärjning mot honom. En dag var kung Ela berusad när han befann sig i Tirsa hemma hos Arsa, som hade ansvaret för palatset i Tirsa. 10Simri kom in, slog ner och dödade Ela. Detta hände under kung Asas tjugosjunde regeringsår i Juda. Sedan blev Simri kung i hans ställe.

11Efter att ha blivit kung och intagit tronen dödade Simri hela Bashas familj och skonade ingen enda man eller pojke, varken släktingar eller vänner. 12Simri utrotade hela Bashas ätt i överensstämmelse med vad Herren hade förutsagt mot Basha genom profeten Jehu. 13Detta var en följd av Bashas och hans son Elas synder som de hade förlett Israel till, och så väckt Herren, Israels Guds vrede genom sina värdelösa gudar.

14Elas historia i övrigt, vad han gjorde, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.

Simri regerar i Israel

15Simri regerade i Tirsa i sju dagar under Juda kungs Asas tjugosjunde regeringsår. När Israels armé, som då belägrade den filisteiska staden Gibbeton, 16fick höra att Simri hade gjort en sammansvärjning och mördat kungen, beslöt de att samma dag göra Omri, överbefälhavaren för hären, till kung över Israel. 17Omri förflyttade sig med alla israeliterna från Gibbeton till Tirsa, som han belägrade. 18När Simri såg att staden var förlorad, gick han in i kungapalatset och satte eld på det och sig själv. Han dog, 19därför att han hade syndat och gjort det som var ont i Herrens ögon, gått Jerobeams väg och begått samma synder som han förlett Israels folk till.

20Simris historia i övrigt och hans sammansvärjning finns nedtecknad i Israels kungars krönika.

Omri regerar i Israel

21Men nu blev Israels folk delat i två halvor. Ungefär hälften av folket fortsatte att följa Omri, medan de återstående ville ha Tivni, Ginats son, till sin kung. 22Men Omris anhängare segrade över Tivnis; Tivni, Ginats son, dog, och Omri blev kung.

23Omri blev kung i Israel under Juda kungs Asas trettioförsta regeringsår och regerade i tolv år, sex av dem i Tirsa. 24Omri köpte kullen Samaria av Semer för två siklar silver och byggde en stad där som han kallade Samaria efter Semer, den tidigare ägaren. 25Men Omri gjorde det som var ont i Herrens ögon och syndade mer än de tidigare kungarna. 26Han följde alla Jerobeams, Nevats sons, vägar och begick samma synder som han förlett Israel till, så att de väckte Herrens, Israels Guds vrede med sina värdelösa gudar.

27Omris historia i övrigt, vad han gjorde och hans framgångar, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.

28När Omri dog begravdes han i Samaria, och hans son Achav blev kung efter honom.

Achav regerar i Israel

29Achav, Omris son, blev kung över Israel i Juda kungs Asas trettioåttonde regeringsår. Achav regerade över Israel i Samaria i tjugotvå år. 30Achav gjorde ännu mer ont i Herrens ögon än någon av hans företrädare. 31Som om det inte var ont nog att han tog efter Jerobeams, Nevats sons, synder, gifte han sig med Isebel, dotter till sidoniernas kung Etbaal och började sedan själv tjäna och tillbe Baal. 32Först byggde han ett altare åt Baal i baalstemplet som han byggt i Samaria, 33och därefter tillverkade han en asherapåle och kom på så sätt att uppväcka Herrens, Israels Guds, vrede mer än någon tidigare kung i Israel.

34Under Achavs regering byggde Hiel från Betel upp Jeriko på nytt. När han lade dess grund kostade det honom hans förstfödde son Aviram, och när han satte upp stadsportarna kostade det honom hans yngste son Seguv. Detta var helt enligt Herrens ord, som hade uttalats av Josua, Nuns son.16:34 Se Jos 6:26