1 ነገሥት 15 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 15:1-34

የይሁዳ ንጉሥ አብያ

15፥1-27-8 ተጓ ምብ – 2ዜና 13፥1-2፡22–14፥1

1የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም በነገሠ በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት አብያ15፥1 በዚህ ስፍራና በ7 እና 8 ላይ እንዳንድ የዕብራይስጥና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ትርጕሞች ግን፤ አቢጃም ይላሉ በይሁዳ ነገሠ፤ 2በኢየሩሳሌም ሆኖ ሦስት ዓመት ገዛ፤ እናቱ መዓካ የተባለች የአቤሴሎም ልጅ ነበረች።

3እርሱም አባቱ ከእርሱ በፊት የሠራውን ኀጢአት ሁሉ ሠራ፤ እንደ አባቱ እንደ ዳዊትም በፍጹም ልቡ በታማኝነት ለእግዚአብሔር አልተገዛም። 4ነገር ግን ከእርሱ ቀጥሎ እንዲነግሥና ኢየሩሳሌምን እንዲያጸናት፣ አምላክ እግዚአብሔር ስለ ዳዊት ሲል በኢየሩሳሌም መብራት ሰጠው። 5ዳዊት በኬጢያዊው በኦርዮ ላይ ካደረሰው በደል በቀር፣ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር አድርጓል፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ፈቀቅ ያለበት ጊዜ አልነበረም።

6አብያም15፥6 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ አንዳንድ የዕብራይስጥና የሱርስት ትርጕሞች ግን፣ አቢጃም ይላሉ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል ጦርነት ነበር። 7ሌላው አብያ በዘመኑ የፈጸመውና ያደረገው ሁሉ፣ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? በአብያና በኢዮርብዓም መካከልም ጦርነት ነበር። 8አብያም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በዳዊትም ከተማ ተቀበረ። ልጁም አሳ በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ አሳ

15፥9-22 ተጓ ምብ – 2ዜና 14፥2-315፥16–16፥6

15፥23-24 ተጓ ምብ – 2ዜና 16፥11–17፥1

9የእስራኤል ንጉሥ ኢዮርብዓም በነገሠ በሃያኛው ዓመት፣ አሳ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ፤ 10በኢየሩሳሌምም አርባ አንድ ዓመት ነገሠ፤ አያቱ መዓካ ትባላለች፤ እርሷም የአቤሴሎም ልጅ ነበረች።

11አሳ አባቱ ዳዊት እንዳደረገው ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነውን ነገር አደረገ። 12የቤተ ጣዖት ወንደቃዎችን ከምድሪቱ አባረረ፤ አባቶቹ የሠሯቸውን ጣዖታት ሁሉ አስወገደ። 13አስጸያፊውን የአሼራ ምስል ዐምድ በማቆሟ፣ አያቱን መዓካን ከእቴጌነቷ ሻራት፤ ጣዖቷንም ሰባብሮ በቄድሮን ሸለቆ አቃጠለው። 14አሳ የማምለኪያ ኰረብታዎችን ፈጽሞ ባያስወግድም እንኳ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ፣ ልቡ ለእግዚአብሔር የተገዛ ነበር። 15አባቱና እርሱ ለእግዚአብሔር የቀደሱትን ብርና ወርቅ እንዲሁም ዕቃዎችን አምጥቶ ወደ እግዚአብሔር ቤት አስገባ።

16አሳና የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ ዘመነ መንግሥታቸውን ያሳለፉት፣ እርስ በርስ በመዋጋት ነበር። 17የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ ይሁዳን ለመውጋት ወጣ፤ ከዚያም ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ አሳ ግዛት ማንም እንዳይገባና እንዳይወጣ ለመቈጣጠር ራማን ምሽግ አድርጎ ሠራት።

18አሳም በእግዚአብሔር ቤትና በቤተ መንግሥቱ ግምጃ ቤት የቀረውን ብርና ወርቅ በሙሉ ወሰደ፤ ከዚያም በታማኝ ሹማምቱ እጅ በደማስቆ ይገዛ ለነበረው፣ ለጠብሪሞን ልጅ፣ የአዚን የልጅ ልጅ ለሆነው ለሶርያ ንጉሥ ለቤን ሀዳድ ላከው። 19እንዲህም አለ፤ “በአባቴና በአባትህ መካከል የስምምነት ውል እንደ ነበረ ሁሉ፣ አሁንም በእኔና በአንተ መካከል ይኑር። እነሆ፤ የብርና የወርቅ ገጸ በረከት ልኬልሃለሁ። አሁንም የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ ወደ መጣበት እንዲመለስ፣ ሄደህ ከእርሱ ጋር ያደረግኸውን የስምምነት ውል አፍርስ።”

20ቤን ሃዳድም የንጉሥ አሳን ሐሳብ ተቀብሎ፣ የጦር አዛዦቹን በእስራኤል ከተሞች ላይ አዘመተ፤ ዒዮንን፣ ዳንን፣ አቤልቤት ማዕካን እንዲሁም ንፍታሌምን ጨምሮ ጌንሳሬጥን በሙሉ ድል አደረገ። 21ባኦስም ይህን ሲሰማ፣ በራማ የጀመረውን የምሽግ ሥራ አቁሞ ወደ ቴርሳ ተመለሰ። 22ንጉሥ አሳ አንድም ሰው እንዳይቀር በይሁዳ ሁሉ ዐዋጅ አስነገረ፤ ከዚያም ሕዝቡ ባኦስ በራማ አስቀምጦት የነበረውን ድንጋይና ዕንጨት አጋዘ፤ ንጉሡም በዚሁ ምጽጳንና በብንያም ውስጥ ጌባን ሠራ።

23በአሳ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ነገር በሙሉ፣ ያደረገውም ሁሉና የሠራቸውም ከተሞች በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፈው የሚገኙ አይደሉምን? ንጉሥ አሳ በሸመገለ ጊዜ ግን እግሮቹ ታመሙ። 24አሳ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እነርሱ በተቀበሩበትም በአባቱ በዳዊት ከተማ ተቀበረ፤ ልጁ ኢዮሣፍጥም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የእስራኤል ንጉሥ ናዳብ

25በይሁዳ ንጉሥ በአሳ ዘመነ መንግሥት በሁለተኛው ዓመት የኢዮርብዓም ልጅ ናዳብ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ ሁለት ዓመትም ገዛ። 26እርሱም በአባቱ መንገድ በመሄድ፣ አባቱ የሠራውንና እስራኤልም እንዲሠሩ ያደረገውን ኀጢአት በመሥራት በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ።

27ናዳብና መላው እስራኤል በፍልስጥኤም የምትገኘውን የገባቶንን ከተማ ከብበው ሳሉ፣ ከይሳኮር ነገድ የተወለደው የአኪያ ልጅ ባኦስ ዐምፆ በመነሣት ናዳብን በገባቶን ገደለው። 28ባኦስ ናዳብን የገደለውና በእግሩ ተተክቶ የነገሠው፣ የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት ነው።

29ወዲያውኑ እንደ ነገሠም የኢዮርብዓምን ቤተ ሰብ በሙሉ ፈጀ። እግዚአብሔር በሴሎናዊው ባሪያው በአኪያ በኩል እንደ ተናገረው፣ ከኢዮርብዓም ቤተ ሰብ አንድም ሰው በሕይወት ሳያስቀር፣ ሁሉንም አጠፋቸው፤ 30ይህም የሆነው ኢዮርብዓም በሠራው ኀጢአትና እስራኤልም እንዲሠሩ በማድረጉ ምክንያት፣ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ በማነሣሣቱ ነው።

31ሌላው በናዳብ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው፣ እርሱም ያደረገው ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 32አሳና የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ ዘመነ መንግሥታቸውን ያሳለፉት እርስ በርስ በመዋጋት ነበር።

የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ

33የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት የአኪያ ልጅ ባኦስ በቴርሳ ከተማ፣ በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤ ሃያ አራት ዓመትም ገዛ። 34በኢዮርብዓም መንገድ በመሄድና እስራኤልም እንዲሠሩ ያደረገውን ኀጢአት በመፈጸም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሥራ ሠራ።

Swedish Contemporary Bible

1 Kungaboken 15:1-34

Aviam regerar i Juda

(2 Krön 13:1-2; 13:22—14:1)

1Under Jerobeams, Nevats sons, artonde regeringsår i Israel blev Aviam kung över Juda. 2Han regerade i Jerusalem i tre år. Aviams mor var Maaka, dotter15:2 Dotterdotter, enligt 2 Krön 13:2 och 2 Sam 14:27. till Avishalom. 3Han syndade på samma sätt som sin far, och hans hjärta var inte hängivet Herren, hans Gud, som hans far Davids hade varit. 4Men för Davids skull lät Herren, hans Gud, alltid en lampa brinna för honom i Jerusalem och upphöjde hans son till hans efterträdare och gjorde Jerusalem starkt. 5David hade gjort det som var rätt inför Herren och aldrig vänt sig bort från hans befallningar under hela sin livstid, med undantag för fallet med hettiten Uria.

6Under hela Rehabeams15:6 Enligt en del andra hebreiska och syriska handskrifter Aviams. livstid var det ständigt krig mellan honom och Jerobeam.

7Aviams historia i övrigt, vad han gjorde, finns nedtecknat i Juda kungars krönika. Det var krig mellan Aviam och Jerobeam.

8Aviam dog och begravdes i Davids stad. Hans son Asa blev kung efter honom.

Asa regerar i Juda

(2 Krön 14:2-3; 15:16—16:6; 16:11-14)

9Asa blev kung i Juda under Jerobeams tjugonde regeringsår i Israel, 10och han regerade i fyrtioett år i Jerusalem. Hans mor15:10 Uppenbarligen farmor…dotterdotter…farmor, se v. 2 med not. var Maaka, Avishaloms dotter. 11Asa gjorde det som var rätt i Herrens ögon, precis som hans förfader David hade gjort. 12Han drev ut de manliga kulttjänarna ur landet och rev ner alla de gudabilder som hans far hade gjort. 13Han avsatte till och med sin mor Maaka som drottningmoder, därför att hon hade låtit tillverka en asherapåle. Den högg han ner och brände upp i Kidrons dal. 14Men offerplatserna blev inte avskaffade, fastän Asa i sitt innersta var trogen till Herren under hela sin livstid. 15Han förde till Herrens hus de silver- och guldföremål som han och hans far hade helgat.

16Det rådde ett ständigt krig mellan kung Asa och Israels kung Basha. 17Kung Basha av Israel drog ut mot Juda och befäste Rama för att hindra att någon kom vare sig till eller från Asa, kungen i Juda. 18Då tog Asa allt silver och guld som fanns kvar i skattkammaren i Herrens hus, och även skatterna i kungapalatset, och bad sina tjänare att föra alltsammans till araméerkungen i Damaskus, Ben-Hadad, son till Tavrimmon, son till Hesjon, och säga:

19”Låt oss ingå förbund, du och jag, liksom det var mellan din far och min far. Jag sänder dig en gåva av silver och guld. Bryt ditt förbund med Israels kung Basha, så att han lämnar mig i fred.”

20Ben-Hadad gick med på kung Asas förslag och sände sina befälhavare mot Israels städer. Han intog Ijon, Dan, Avel Bet-Maaka och hela Kinneret och hela Naftalis land. 21När Basha hörde detta avslutade han bygget i Rama och vände tillbaka till Tirsa. 22Kung Asa sammankallade då alla judéerna, och de förde bort från Rama sten och timmer som Basha använt. Det använde kung Asa till att bygga upp Geva i Benjamin och Mispa.

23Asas historia i övrigt, hans erövringar, vad han gjorde och de städer han byggde finns nedtecknat i Juda kungars krönika.

På äldre dagar fick han en sjukdom i sina fötter. 24När han dog begravdes han bland sina fäder i sin far Davids stad, och hans son Joshafat efterträdde honom.

Nadav regerar i Israel

25Under Juda kung Asas andra regeringsår blev Jerobeams son Nadav kung i Israel. Han regerade i Israel i två år. 26Han gjorde det som var ont i Herrens ögon. Han gick samma vägar som sin far, begick samma synder och förledde Israel till synd.

27Basha, son till Achia från Isaskars stam, ledde en sammansvärjning mot Nadav och mördade honom när han med den israelitiska armén belägrade den filisteiska staden Gibbeton.

Basha regerar i Israel

28Basha dödade Nadav under Juda kung Asas tredje regeringsår och blev själv kung efter honom.

29Så fort han blivit kung dödade Basha alla som tillhörde Jerobeams familj och lämnade ingen levande varelse kvar, utan utplånade dem alla, precis som Herren hade sagt genom sin tjänare Achia från Shilo. 30Detta skedde därför att Jerobeam hade retat Herren, Israels Gud, till vrede genom att synda och förleda Israel till synd.

31Nadavs historia i övrigt, vad han gjorde, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.

32Det rådde ständigt krig mellan Asa och Israels kung Basha. 33Under Juda kungs Asas tredje regeringsår blev Basha, Achias son, kung över Israel och regerade i Tirsa i tjugofyra år. 34Han gjorde det som var ont i Herrens ögon. Han följde Jerobeams vägar och begick samma synder som denne förlett Israel till.