1 ነገሥት 14 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 14:1-31

አኪያ በኢዮርብዓም ላይ የተናገረው ትንቢት

1በዚያን ጊዜ የኢዮርብዓም ልጅ አብያ ታመመ፤ 2ኢዮርብዓም ሚስቱን እንዲህ አላት፤ “ተነሺ፣ የኢዮርብዓም ሚስት መሆንሽ እንዳይታወቅብሽ ሆነሽ፣ ወደ ሴሎ ሂጂ፤ በዚህ ሕዝብ ላይ እንደምነግሥ የነገረኝ ነቢይ አኪያ እነሆ፤ በዚያ ይገኛል። 3ስትሄጂም ዐሥር እንጀራ፣ ጥቂት ሙልሙል ዳቦ እና አንድ እንስራ ማር ይዘሽ ሂጂ፤ እርሱም በልጁ ላይ የሚደርሰውን ይነግርሻል።” 4ስለዚህ የኢዮርብዓም ሚስት ያላትን አድርጋ በሴሎ ወደሚገኘው ወደ አኪያ ቤት ሄደች።

በዚህ ጊዜ አኪያ ከማርጀቱ የተነሣ ዐይኖቹ ፈዝዘው ነበር። 5እግዚአብሔር ግን ለአኪያ፣ “እነሆ፤ የኢዮርብዓም ሚስት ስለ ታመመው ልጇ ልትጠይቅህ ሌላ ሴት መስላ ትመጣለችና እንዲህ ብለህ መልሳት” ብሎ ነገረው።

6አኪያም የእግሯን ኮቴ ድምፅ እበሩ ላይ እንደ ሰማ እንዲህ አላት፤ “የኢዮርብዓም ሚስት ሆይ ግቢ፤ ግን ለምንድን ነው ሌላ ሴት መስለሽ ለመታየት የፈለግሽው? ለአንቺ ከባድ ነገር እንድነግርሽ ተልኬአለሁ። 7አሁንም ሂጂና ኢዮርብዓምን የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው ብለሽ ንገሪው፤ ‘ከሕዝቡ መካከል አንሥቼ የሕዝቤ የእስራኤል መሪ አደረግሁህ፤ 8ከዳዊት ቤት መንግሥቱን ቀድጄ ለአንተ ሰጠሁህ፤ አንተ ግን በፊቴ መልካም ነገር በማድረግ ብቻ ትእዛዜን እንደ ጠበቀው፣ በፍጹም ልቡም እንደ ተከተለኝ እንደ ባሪያዬ እንደ ዳዊት አልሆንህም። 9ከአንተ በፊት ከነበሩት ሁሉ ይልቅ አንተ የከፋ ሥራ ሠራህ፤ ለራስህም ከቀለጠ ብረት ሌሎች አማልክትን ሠራህ፤ ቍጣዬን አነሣሣህ፤ ወደ ኋላህም ጣልኸኝ።

10“ ‘ስለዚህ እኔም በኢዮርብዓም ቤት ላይ ጥፋትን አመጣለሁ፤ ባሪያም ይሁን ነጻ ዜጋ የኢዮርብዓምን ወንድ ልጅ ሁሉ ከእስራኤል አስወግዳለሁ፤ ኩበትም ዐመድ እስኪሆን ድረስ እንደሚቃጠል፣ እኔም የኢዮርብዓምን ቤት እንዲሁ አቃጥላለሁ። 11ከኢዮርብዓም ወገን በከተማ የሞተውን ውሾች፣ በባላገር የሞተውን ደግሞ የሰማይ አሞሮች ይበሉታል፤ እግዚአብሔር ተናግሯልና!’

12“እንግዲህ አንቺም ወደ ቤትሽ ሂጂ፤ የምትኖሪበትን ከተማ እግርሽ እንደ ረገጠ፣ ልጁ ይሞታል፤ 13እስራኤልም ሁሉ አልቅሰው ይቀብሩታል። የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ከኢዮርብዓም ቤት ሁሉ መልካም ነገር ያገኘበት እርሱ ብቻ ስለሆነ፣ በወግ በማዕረግ የሚቀበር እርሱ ብቻ ነው።

14“ከዚህም በላይ፣ እግዚአብሔር የኢዮርብዓምን ቤተ ሰብ የሚያስወግድ ንጉሥ በእስራኤል ላይ ለራሱ ያስነሣል፤ ይህም ዛሬ፣ አሁኑኑ ይሆናል።14፥14 በዕብራይስጡ የዚህ ዐረፍተ ነገር ትርጕም በትክክል አይታወቅም 15እግዚአብሔር እስራኤልን በውሃ ውስጥ እንደሚንቀጠቀጥ ሸንበቆ ያንቀጠቅጠዋል፤ የአሼራን ምስል ዐምድ14፥15 በዚህም ሆነ በሌሎቹም የመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ክፍሎች፣ የአሼራ ጣዖት አምላክ ምስል ነው በመሥራት እግዚአብሔርን ለቍጣ ያነሣሡት ስለሆነ፣ እግዚአብሔር ለቀድሞ አባቶቻቸው ከሰጣቸው ከዚህች ከመልካሚቱ ምድር እስራኤልን ይነቅላቸዋል፤ ከወንዙም ማዶ14፥15 የኤፍራጥስ ወንዝ ነው ይበትናቸዋል። 16ኢዮርብዓም ኀጢአት ሠርቶ፣ እስራኤልንም እንዲሠሩ በማድረጉ፣ እግዚአብሔር እስራኤልን ይተዋቸዋል።”

17የኢዮርብዓም ሚስትም ተነሥታ ወደ ቴርሳ ሄደች፤ የቤቱን መድረክ ወዲያው እንደ ተራመደች ልጁ ሞተ፤ 18ከዚያም ቀበሩት፤ እግዚአብሔር በባሪያው በአኪያ አማካይነት እንደ ተናገረ፣ እስራኤል ሁሉ አለቀሱለት።

19የቀረው የኢዮርብዓም ታሪክ፣ ያደረገው ጦርነትና አገዛዙም ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፏል። 20እርሱም ሃያ ሁለት ዓመት ነግሦ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ናዳብም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ሮብዓም

14፥2125-31 ተጓ ምብ – 2ዜና 12፥9-16

21የሰሎሞን ልጅ ሮብዓም በይሁዳ ነገሠ፤ በነገሠም ጊዜ ዕድሜው አርባ አንድ ዓመት ነበር፤ እርሱም እግዚአብሔር ለስሙ መጠሪያ እንድትሆን ከእስራኤል ነገድ ሁሉ በመረጣት በኢየሩሳሌም ዐሥራ ሰባት ዓመት ገዛ። እናቱ ናዓማ የተባለች አሞናዊት ነበረች።

22ይሁዳ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ፤ ከአባቶቻቸው ይልቅ እነርሱ በሠሩት ኀጢአት ይበልጥ የቅናት ቍጣውን አነሣሡ፤ 23እንዲሁም በእያንዳንዱ ኰረብታና በየትልልቁ ዛፍ ጥላ ሥር የማምለኪያ ኰረብቶችን አዕማደ ጣዖታት፣ የአሼራን ምስል ዐምድ ለራሳቸው አቆሙ። 24ከዚያም ይልቅ፣ የቤተ ጣዖት ወንደቃዎች በምድሪቱ ላይ ነበሩ፤ እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን ፊት አሳድዶ ያስወጣቸው አሕዛብ የፈጸሙትን አስጸያፊ ድርጊት ሁሉ እነዚህም ፈጸሙ።

25ሮብዓም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት፣ የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ አደጋ ጣለ፤ 26የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የቤተ መንግሥቱን ሀብት ወሰደ፤ ሰሎሞን ያሠራቸው የወርቅ ጋሻዎች እንኳ ሳይቀሩ ሁሉንም ነገር አጋዘ። 27ስለዚህ ንጉሥ ሮብዓም እነዚህን ለመተካት ሲል፣ የናስ ጋሻዎች አሠርቶ የቤተ መንግሥቱን በር የሚጠብቁት ዘበኞች አዛዦች እንዲይዙ አደረገ። 28ንጉሡ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚሄድበት ጊዜ ሁሉ፣ ዘቦቹ ጋሻዎቹን ያነግባሉ፤ ከዚያም በዘብ ጥበቃው ክፍል መልሰው ያስቀምጡ ነበር።

29የቀረው የሮብዓም አገዛዝ፣ ያደረገውም ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 30በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል ያላቋረጠ ጦርነት ተደርጎ ነበር። 31ሮብዓምም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እነርሱ በተቀበሩበትም በዳዊት ከተማ ተቀበረ። እናቱ ናዓማ የተባለች አሞናዊት ነበረች። ልጁ አብያም14፥31 አንዳንድ የዕብራይስጥና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ትርጕሞች ግን፣ አቢጃም ይላሉ በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Swedish Contemporary Bible

1 Kungaboken 14:1-31

Guds dom över Jerobeam

1Vid den tiden blev Jerobeams son Avia sjuk. 2Då sa Jerobeam till sin hustru: ”Gå och förklä dig så att ingen kan känna igen dig som Jerobeams hustru! Sedan ska du gå till Shilo och söka upp profeten Achia, han som förutsade att jag skulle bli kung över detta folk. 3Ta med dig tio bröd, några kakor och en kruka honung och gå till honom. Han kommer då att tala om för dig hur det går med pojken.”

4Jerobeams hustru gjorde så och gav sig iväg till Achias hem i Shilo. Achia var nu en gammal man och kunde inte se. 5Men Herren talade om för honom att Jerobeams hustru skulle komma förklädd till honom för att fråga om sin sjuke son. Herren talade också om för Achia vad han skulle svara henne.

6När därför Achia hörde henne komma i dörren, ropade han: ”Kom in, du Jerobeams hustru! Varför försöker du dölja vem du är? Jag har sorgliga nyheter åt dig. 7Gå och säg till Jerobeam: ’Så säger Herren, Israels Gud: ”Jag upphöjde dig ur folket och gjorde dig till furste över mitt folk Israel. 8Jag ryckte kungariket från Davids familj och gav det till dig, men du har inte varit som min tjänare David som lydde mina befallningar och helhjärtat följde mig och gjorde endast det som var rätt inför mig. 9Du har gjort mer ont än någon före dig. Du har gjort andra gudar åt dig och väckt min vrede med dina gjutna gudar. Eftersom du har vänt ryggen åt mig 10ska jag låta olyckor komma över Jerobeams familj. Jag ska utrota alla Jerobeams manliga ättlingar i Israel, både slavar och fria. Jag ska förinta hela hans hus, som man bränner gödsel tills det inte finns något kvar. 11De i Jerobeams familj som dör inne i staden ska ätas av hundar, och de som dör ute på landsbygden blir mat till fåglarna.” ’ Så har Herren talat.

12Gå nu hem. När du går in i staden kommer pojken att dö. 13Hela Israel ska hålla dödsklagan över honom och begrava honom, och han är den ende i Jerobeams familj som kommer att läggas i en grav, för det är bara i honom bland dem som Herren, Israels Gud, har sett något gott.

14Herren ska låta en kung uppstå i Israel, som ska utplåna Jerobeams hela släkt. Och vad händer inte redan nu idag?14:14 Innebörden av den sista satsen är osäker. Ordagrant (ungefär): idag och vad även nu? 15Herren ska slå Israel, så att det blir som vajande vass i vatten. Han ska rycka upp Israel från detta goda land, som gavs till deras förfäder, och sprida ut dem till andra sidan av floden Eufrat. De har väckt Herrens vrede genom sina asherapålar14:15 Representationer av den kanaaneiska fruktbarhetsgudinnan vid samma namn. som de gjort. 16Han ska överge Israel på grund av Jerobeams synd, som har fått hela Israel att synda med honom.”

17Jerobeams hustru återvände till Tirsa, och just som hon gick in genom dörren till sitt hem dog pojken. 18Han begravdes, och hela Israel höll dödsklagan över honom, precis som Herren hade förutsagt genom sin tjänare profeten Achia.

19Jerobeams historia i övrigt, de krig han förde och annat som skedde under hans regeringstid, finns nedtecknat i Israels kungars krönika.

20Jerobeam regerade i tjugotvå år och efterträddes vid sin död av sonen Nadav.

Rehabeam regerar i Juda

(2 Krön 12:9-16)

21Rehabeam, Salomos son, var kung i Juda. Han var fyrtioett år gammal när han började regera och innehade tronen i Jerusalem i sjutton år, i den stad som Herren hade utvalt bland alla Israels stammar att låta sitt namn bo i. Rehabeams mor var ammonitiska och hette Naama.

22Folket i Juda gjorde det som var ont inför Herren, och med de synder de begick väckte de hans vrede ännu mer än vad deras fäder hade gjort. 23De byggde åt sig offerhöjder, satte upp stenstoder14:23 Stenstoderna stod vanligen tillsammans med asherapålar, se not till 14:15, som deras manliga motsvarighet. och asherapålar på alla höjder och under alla grönskande träd. 24Det fanns till och med manliga tempelprostituerade i landet, och folket tog efter alla avskyvärdheter hos de folk Herren hade drivit bort för israeliterna.

25Under Rehabeams femte regeringsår anföll den egyptiske kungen Shishak Jerusalem. 26Han plundrade Herrens hus och kungapalatset på alla skatter. Han tog allting, även de guldsköldar som Salomo hade låtit göra. 27Kung Rehabeam lät i stället för dem göra sköldar av koppar i stället och lämnade dem i förvar hos den kungliga livvakten vid ingången till palatset. 28Varje gång kungen gick till Herrens hus gick livvakterna med och bar dessa sköldar och lämnade dem sedan tillbaka till vaktrummet.

29Rehabeams historia i övrigt, vad han gjorde, finns nedtecknat i Juda kungars krönika.

30Det var ständigt krig mellan Rehabeam och Jerobeam. 31När Rehabeam dog begravdes han bland sina fäder i Davids stad. Hans mor var ammonitiskan Naama. Han efterträddes av sonen Aviam.