ዘዳግም 32 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 32:1-52

1ሰማያት ሆይ፤ አድምጡ፤ እኔም እናገራለሁ፤

ምድር ሆይ፤ አንቺም የአፌን ቃል ስሚ።

2ትምህርቴ እንደ ዝናብ ትውረድ፤

ቃሌም እንደ ጤዛ ይንጠባጠብ፤

በቡቃያ ሣር ላይ እንደ ካፊያ፣

ለጋ ተክልም ላይ እንደ ከባድ ዝናብ ይውረድ።

3እኔ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ዐውጃለሁ፤

የአምላካችንን (ኤሎሂም) ታላቅነት አወድሱ!

4እርሱ ዐለት፣ ሥራውም ፍጹም ነው፤

መንገዱም ሁሉ ትክክል ነው፤

የማይሳሳት ታማኝ አምላክ፣

ቀጥተኛና ጻድቅ አምላክም እርሱ ነው።

5በእርሱ ላይ ክፋት ፈጽመዋል፤ ከነውራቸው የተነሣ ከእንግዲህ ልጆቹ አይደሉም፤

ወልጋዳና ጠማማ ትውልዶች ናቸው32፥5 ወይም የተጣመሙት እነርሱ እንጂ የእርሱ ልጆች አይደሉም

6አንተ ተላላና ጥበብ የጐደለህ ሕዝብ፣

ለእግዚአብሔር (ለያህዌ) የምትመልስለት በዚህ መንገድ ነውን?

አባትህ ፈጣሪህ32፥6 ወይም ያወጣህ አባትህ።

የሠራህና ያበጀህ እርሱ አይደለምን?

7የጥንቱን ዘመን አስታውስ፤

አባትህን ጠይቅ፤ ይነግርሃልም፤

ሽማግሌዎችህንም ጠይቅ፤ ያስረዱሃል።

8ልዑል ለአሕዛብ ርስታቸውን በሰጠ ጊዜ፣

የሰውንም ዘር በለያየ ጊዜ፣

በእስራኤል ልጆች32፥8 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይላሉ። ቍጥር ልክ፣

የአሕዛብን ርስት ድንበር ለየ፤

9የእግዚአብሔር (ያህዌ) ድርሻ የገዛ ሕዝቡ፣

ያዕቆብ የተለየ ርስቱ ነውና።

10እርሱን በምድረ በዳ፣

ባዶና ጭው ባለ በረሓ ውስጥ አገኘው፤

ጋሻ ሆነው፤ ተጠነቀቀለትም፤

እንደ ዐይኑ ብሌን ጠበቀው።

11ንስር ጐጆዋን በትና፣

በጫጩቶቿም ላይ እንደምትረብብ፣

እነርሱን ለመያዝ ክንፎቿን እንደምትዘረጋ፣

በክንፎቿም እንደምትሸከማቸው፣

12እግዚአብሔር (ያህዌ) ብቻ መራው፤

ምንም ባዕድ አምላክ አብሮት አልነበረም።

13በምድር ከፍታ ላይ አወጣው፤

የዕርሻንም ፍሬ መገበው፤

ከዐለት ድንጋይ ማር አበላው፤

ከባልጩትም ድንጋይ ዘይት መገበው።

14የላሙንና የበጉን መንጋ ቅቤና ወተት፣

የሰቡትን በጎችና ፍየሎች፣

የባሳንን ምርጥ አውራ በግ፣

መልካም የሆነውንም ስንዴ፣

ማለፊያውንም የወይን ጠጅ።

15ይሹሩን32፥15 ይሹሩን ማለት ቅን ወይም ትክክለኛ ማለት ሲሆን፣ ይኸውም እስራኤልን የሚያሳይ ነው። ወፈረ፤ ረገጠ፤

ጠገበ፤ ሰውነቱ ደነደነ፤ ለሰለሰ፤

የፈጠረውንም አምላክ (ኤሎሂም) ተወ፤

መጠጊያ ዐለት የሆነውን አዳኙንም ናቀ።

16በባዕዳን አማልክታቸው አስቀኑት፤

በአጸያፊ ጣዖቶቻቸውም አስቈጡት።

17አምላክ ላልሆኑ አጋንንት፦

ላላወቋቸው አማልክት፣

ከጊዜ በኋላ ለተነሡ አማልክት፣

አባቶቻችሁ ላልፈሯቸው አማልክት ሠዉ።

18አባት የሆነህን ዐለት ከዳኸው፤

የወለደህን አምላክ ረሳኸው።

19እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን አይቶ ናቃቸው፤

በወንድና በሴት ልጆቹ ተቈጥቷልና።

20እርሱም፣ “ፊቴን ከእነርሱ እሰውራለሁ፤

መጨረሻቸው ምን እንደሚሆንም አያለሁ” አለ፤

ጠማማ ትውልድ፣

የማይታመኑም ልጆች ናቸውና።

21አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤

በከንቱ ጣዖቶቻቸው አስቈጡኝ።

እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ።

በማያስተውልም ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ።

22በቍጣዬ እሳት ተቀጣጥሏልና፤

እርሱ እስከ ሲኦል ዘልቆ ይነድዳል።

ምድርን እስከ ሰብሏ ይበላል፤

የተራሮችንም መሠረት ያቀጣጥላል።

23“በመዓት ላይ መዓት አመጣባቸዋለሁ።

ፍላጻዬንም በእነርሱ ላይ እጨርሳለሁ።

24የሚያጠፋ ራብ፣ በልቶ የሚጨርስ ቸነፈርና ከባድ

መቅሠፍት እሰድድባቸዋለሁ፤

የአራዊትን ሹል ጥርስ፣ በምድር የሚሳብ የእባብ መርዝም

እሰድድባቸዋለሁ።

25ሰይፍ መንገድ ላይ ያስቀራቸዋል፤

ቤታቸውም ውስጥ ድንጋጤ ይነግሣል፤

ጕልማሳውና ልጃገረዷ፣

ሕፃኑና ሽማግሌው ይጠፋሉ።

26እበትናቸዋለሁ፤ ከሰዎችም መካከል መታሰቢያቸውን

አጠፋለሁ አልሁ፤

27ነገር ግን ጠላቶቻቸው እንዳይታበዩ፣

‘ድል ያደረገችው እጃችን እንጂ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን ሁሉ አላደረገም’ እንዳይሉ፣

የጠላትን መነሣሣት ሠጋሁ።”

28አእምሮ የጐደላቸው፣

ማስተዋልም የሌላቸው ናቸው።

29አስተዋዮች ቢሆኑ ኖሮ ይህን በተገነዘቡ፣

መጨረሻቸውም ምን እንደሚሆን ባስተዋሉ ነበር።

30መጠጊያ ዐለታቸው ካልሸጣቸው፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ካልተዋቸው በቀር፣

አንድ ሰው እንዴት ሺሑን ያሳድዳል?

ሁለቱስ እንዴት ዐሥር ሺሑን እንዲሸሹ ያደርጋሉ?

31የእነርሱ መጠጊያ ዐለት እንደ እኛ መጠጊያ

ዐለት አይደለምና፤ ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን አይክዱም።

32ወይናቸው ከሰዶም ወይን፣

ከገሞራም ዕርሻ ይመጣል፤

የወይናቸው ፍሬ በመርዝ፣

ዘለላቸውም በምሬት የተሞላ ነው።

33ወይናቸው የእባብ መርዝ፣

የመራዥ እባብም መርዝ ነው።

34“ይህ በእኔ ዘንድ ተጠብቆ ያለ፣

በመዝገቤስ የታተመ አይደለምን?

35በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፤

ጊዜው ሲደርስ እግራቸው ይሰናከላል፤

የመጥፊያቸው ቀን ቀርቧል፤

የሚመጣባቸውም ፍርድ ፈጥኖባቸዋል።”

36ኀይላቸው መድከሙን፣

ባሪያም ሆነ ነጻ ሰው አለመቅረቱን በሚያይበት ጊዜ፣

እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሕዝቡ ይፈርዳል፤

ለአገልጋዮቹም ይራራል።

37እንዲህም ይላል፤ “መጠጊያ ዐለት የሆኗቸው፣

እነዚያ አማልክታቸው የት አሉ?

38የመሥዋዕታቸውን ሥብ የበሉ፣

የመጠጥ ቍርባናቸውንም የወይን ጠጅ የጠጡ አማልክት ወዴት ናቸው?

እስቲ ይነሡና ይርዷችሁ!

እስቲ መጠለያ ይስጧችሁ!

39“እኔ ራሴ እርሱ እንደ ሆንሁ እዩ፤

ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤

እገድላለሁ፤ አድናለሁም፤

አቈስላለሁ፤ እፈውሳለሁም፤

ከእጄም የሚያስጥል ማንም የለም።

40እጄን ወደ ሰማይ አነሣለሁ፤

ለዘላለምም ሕያው እንደ ሆንሁ እናገራለሁ፤

41የሚያብረቀርቅ ሰይፌን ስዬ፣

እጄ ለፍርድ ስትይዘው፣

ባላጋራዎቼን እበቀላቸዋለሁ፤

የሚጠሉኝንም እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ።

42ሰይፌ ሥጋ በሚበላበት ጊዜ፣

ፍላጾቼ በደም እንዲሰክሩ አደርጋለሁ፤

ደሙ የታረዱትና የምርኮኞች፣

የጠላት አለቆችም ራስ ደም ነው።”

43አሕዛብ ሆይ፤ ከሕዝቡ ጋር ደስ ይበላችሁ32፥43 ወይም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ ደስ ይበላችሁ።32፥43 የማሶሬቱ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም፣ ሕዝቦች ሆይ፤ መላእክት ሁሉ ለእርሱ ይስገዱ ይላሉ።

እርሱ የአገልጋዮቹን ደም ይመልሳል፤

ጠላቶቹንም ይበቀላል።

ምድሪቱንና ሕዝቡን ይቤዣቸዋልና።

44ሙሴም ከነዌ ልጅ ከኢያሱ ጋር መጥቶ የዚህን መዝሙር ቃሎች በሕዝቡ ጆሮ ተናገረ። 45ሙሴም እነዚህን ቃሎች ሁሉ ለመላው እስራኤል ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ፣ 46እንዲህ አላቸው፤ የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ በጥንቃቄ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቻችሁን እንድታዝዟቸው፣ እኔ ዛሬ በግልጥ የምነግራችሁን ቃሎች ሁሉ በልባችሁ አኑሩ። 47ቃሎቹ ለእናንተ ሕይወታችሁ እንጂ እንዲሁ ባዶ ቃሎች አይደሉም፤ በእነርሱ ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ፣ በምትወርሷትም ምድር ረዥም ዘመን ትኖራላችሁ።

ሙሴ በናባው ተራራ ላይ መሞቱ

48በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 49“ከኢያሪኮ ማዶ ባለው የሞዓብ ምድር፣ ከዓባሪም ተራሮች አንዱ ወደ ሆነው ወደ ናባው ተራራ ወጥተህ ለእስራኤላውያን ርስት አድርጌ የምሰጣትን የከነዓንን ምድር አሻግረህ ተመልከት። 50ወንድምህ አሮን በሖር ተራራ ላይ እንደ ሞተና ወደ ወገኖቹ እንደ ተሰበሰበ ሁሉ፣ አንተም በወጣህበት በዚያ ተራራ ላይ ሙት፤ ወደ ወገኖችህም ተሰብሰብ። 51ይህ የሚሆንበት ምክንያት ሁለታችሁም በጺን ምድረ በዳ፣ በቃዴስ በመሪባ ውሃ አጠገብ በእኔ ላይ መታመናችሁን በእስራኤላውያን ፊት ስላጐደላችሁና ቅድስናዬንም በእስራኤላውያን መካከል ስላላከበራችሁ ነው። 52ስለዚህ ምድሪቱን ከሩቅ ሆነህ ታያታለህ እንጂ፣ ለእስራኤል ሕዝብ ወደምሰጣት ምድር አትገባም።”

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 32:1-52

1ฟ้าสวรรค์เอ๋ย ฟังเถิดที่ข้าพเจ้าจะกล่าว

แผ่นดินโลกเอ๋ย จงสดับวาจาจากปากของข้าพเจ้า

2ขอให้คำสอนของข้าพเจ้าพรั่งพรูลงมาดั่งฝน

และให้ถ้อยคำของข้าพเจ้าหยาดหยดมาดุจน้ำค้าง

เหมือนสายฝนโปรยปรายลงบนหญ้าอ่อน

เหมือนฝนชุ่มรินรดพืชพันธุ์เขียวสด

3ข้าพเจ้าจะประกาศพระนามของพระยาห์เวห์

ขอสดุดีความยิ่งใหญ่ของพระเจ้าของเรา!

4พระองค์ทรงเป็นพระศิลา พระราชกิจของพระองค์สมบูรณ์พร้อม

และวิถีทางของพระองค์ล้วนยุติธรรม

ทรงเป็นพระเจ้าผู้ซื่อสัตย์ผู้ไม่ทำสิ่งที่ผิดใดๆ เลย

พระองค์ทรงชอบธรรมและยุติธรรม

5พวกเขาทำตัวเสื่อมทรามต่อพระองค์

น่าอับอายขายหน้าเกินกว่าจะเป็นลูกของพระเจ้าต่อไป

พวกเขาเป็นคนรุ่นที่วิปริตและกลับกลอก32:5 หรือพวกเขาเสื่อมทรามและไม่ได้เป็นบุตรของพระองค์ / เป็นชั่วอายุที่วิปริตและบิดเบี้ยวน่าละอาย

6ท่านตอบสนองต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าเช่นนี้หรือ

ประชากรที่โง่เขลาเบาปัญญา?

พระเจ้าไม่ใช่พระบิดาพระผู้สร้างของท่าน32:6 หรือพระบิดาผู้ซื้อท่านมา

ผู้ทรงก่อร่างสร้างท่านขึ้นมาหรือ?

7จงระลึกถึงวันคืนเก่าก่อน

คิดถึงชั่วอายุตั้งแต่อดีตนานมา

ถามบิดาของท่านดูเถิด เขาจะบอกท่านได้

ถามบรรดาผู้อาวุโสเถิด พวกเขาจะอธิบายให้ฟัง

8เมื่อองค์ผู้สูงสุดประทานกรรมสิทธิ์แก่ชนชาติต่างๆ

เมื่อทรงแยกมวลมนุษยชาติ

พระองค์ทรงกำหนดเขตชนชาติทั้งหลาย

ตามจำนวนบุตรของอิสราเอล32:8 หรือตามจำนวนบุตรของพระเจ้า

9ส่วนขององค์พระผู้เป็นเจ้าคือประชากรของพระองค์

ยาโคบคือส่วนกรรมสิทธิ์ของพระองค์

10พระองค์ทรงพบเขาในถิ่นกันดารอันเริศร้าง

และเต็มไปด้วยเสียงโหยหวน

พระองค์ทรงปกป้องและดูแลเขา

พระองค์ทรงพิทักษ์เขาดั่งแก้วพระเนตรของพระองค์

11เหมือนนกอินทรีตะกุยรังของมัน

และบินร่อนอยู่เหนือลูกอ่อน

กางปีกออกรองรับ

ประคับประคองพาลูกบินไป

12องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้เดียวทรงนำเขาไป

ไม่มีพระต่างด้าวอยู่กับเขา

13พระองค์ทรงทำให้เขาทะยานไปตามเบื้องสูงแห่งแผ่นดิน

และทรงเลี้ยงดูเขาด้วยผลผลิตจากท้องทุ่ง

ทรงบำรุงเลี้ยงเขาด้วยน้ำผึ้งจากศิลา

และด้วยน้ำมันจากหินผา

14ด้วยน้ำนมและนมข้นจากฝูงสัตว์

และด้วยแพะแกะอ้วนพี

กับแกะผู้ชั้นเยี่ยมแห่งบาชาน

และข้าวสาลีที่ดีที่สุด

เขาดื่มน้ำองุ่นสีแดงก่ำที่มีฟอง

15เยชูรุน32:15 แปลว่า ผู้เที่ยงธรรม คือ อิสราเอล อ้วนพีขึ้นก็พยศ

ครั้นอิ่มหนำก็อ้วนใหญ่ ขนเป็นมันปลาบ

เขาทอดทิ้งพระเจ้าผู้ทรงสร้างเขา

ปฏิเสธพระศิลาพระผู้ช่วยให้รอดของตน

16พวกเขายั่วยุให้พระองค์อิจฉาด้วยพระต่างด้าวทั้งปวงของเขา

และยั่วยุพระพิโรธของพระองค์ด้วยรูปเคารพอันน่าชิงชังทั้งหลาย

17พวกเขาเซ่นสังเวยแก่ภูตผีปีศาจซึ่งไม่ใช่พระเจ้า

เป็นพระซึ่งเขาไม่เคยรู้จัก

พระซึ่งเพิ่งปรากฏ

พระซึ่งบรรพบุรุษของท่านไม่เกรงกลัว

18ท่านได้ทอดทิ้งพระศิลาผู้ให้กำเนิดท่าน

ท่านลืมพระเจ้าผู้ทรงให้ท่านเกิดมา

19องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเห็นเช่นนี้และทรงละทิ้งเขา

เพราะว่าบุตรชายบุตรสาวของพระองค์ทำให้พระองค์ทรงพระพิโรธ

20พระองค์ตรัสว่า “เราจะซ่อนหน้าจากพวกเขา

และดูว่าบั้นปลายของเขาจะเป็นเช่นใด

เพราะเขาเป็นคนรุ่นที่นอกลู่นอกรอย

ลูกหลานผู้ไม่ซื่อสัตย์

21เขาทำให้เราอิจฉาสิ่งที่ไม่ใช่พระ

และยั่วโทสะเราด้วยรูปเคารพอันไร้ค่า

เราจะทำให้เขาอิจฉาผู้ที่ไม่ใช่ชนชาติ

เราจะยั่วโทสะเขาด้วยประชาชาติที่ไม่มีความเข้าใจ

22เพราะโทสะของเราจุดเปลวไฟ

ซึ่งเผาถึงก้นบึ้งของแดนมรณา

ไฟนั้นจะเผาผลาญโลกและพืชผลทั้งปวง

และบันดาลให้ภูเขาทั้งหลายลุกเป็นไฟ

23“เราจะสุมหายนะลงเหนือพวกเขา

และยิงธนูเข้าใส่พวกเขา

24เราจะส่งการกันดารอาหารมาต่อสู้พวกเขา

ส่งโรคระบาดอันล้างผลาญและภัยพิบัติร้ายแรงมาเล่นงานพวกเขา

เราจะส่งเขี้ยวเล็บของสัตว์ป่ามาทำร้ายพวกเขา

ส่งพิษของงูร้ายซึ่งเลื้อยมาในผงคลี

25ตามท้องถนนมีคมดาบปลิดชีวิตลูกหลานของพวกเขา

ภายในบ้านมีความหวาดหวั่นพรั่นพรึง

ชายหนุ่มและหญิงสาวจะพินาศ

ทั้งทารกและคนสูงอายุ

26เราพูดแล้วว่าเราจะกระจายพวกเขาออกไป

และลบพวกเขาให้เลือนหายไปจากความทรงจำของมนุษยชาติ

27แต่เราหวั่นคำถากถางของศัตรู

เกรงว่าปฏิปักษ์จะเข้าใจผิด

และพูดว่า ‘มือของเราพิชิตชัยชนะ

องค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ทรงทำอะไรเลย’ ”

28พวกเขาเป็นชนชาติที่ไร้ความคิด

ขาดความฉลาดหลักแหลม

29ถ้าเพียงแต่พวกเขาฉลาดและเข้าใจ

และมองออกว่าบั้นปลายของตนจะเป็นเช่นใด!

30คนคนเดียวจะไล่คนเป็นพันได้อย่างไร?

หรือสองคนทำให้คนเป็นหมื่นหนีเตลิดได้อย่างไร?

ถ้าไม่ใช่เพราะพระศิลาของพวกเขาได้ขายพวกเขาเสียแล้ว

ถ้าไม่ใช่เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบพวกเขาไว้แล้ว

31เพราะศิลาของชนชาติอื่นๆ ไม่เหมือนพระศิลาของเรา

แม้ศัตรูของเราก็ยอมรับเช่นนั้น

32เทือกเถาของพวกเขามาจากเทือกเถาแห่งโสโดม

และจากท้องทุ่งแห่งโกโมราห์

ผลองุ่นของพวกเขาเต็มไปด้วยยาพิษ

พวงองุ่นของพวกเขามีแต่ความขมขื่น

33เหล้าองุ่นของพวกเขาคือพิษงูร้าย

เป็นพิษร้ายของงูเห่า

34“เราเก็บงำเรื่องนี้

และประทับตราเก็บไว้ในคลังของเราไม่ใช่หรือ?

35การแก้แค้นเป็นหน้าที่ของเราเอง เราจะคืนสนอง

เมื่อถึงเวลาเท้าของพวกเขาจะลื่นไถล

วันแห่งหายนะของพวกเขาใกล้เข้ามาแล้ว

และความย่อยยับจะถาโถมเข้าใส่พวกเขา”

36องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงพิพากษาประชากรของพระองค์

และทรงสงสารเอ็นดูผู้รับใช้ของพระองค์

เมื่อพระองค์ทอดพระเนตรเห็นพละกำลังของพวกเขาเสื่อมลง

และไม่มีใครหลงเหลืออยู่ ไม่ว่าทาสหรือไท

37พระองค์จะตรัสว่า “พระทั้งหลายของพวกเขาไปไหนเสียเล่า

ศิลาที่พวกเขาลี้ภัยไปไหนเสียแล้ว

38ไหนล่ะพระที่กินไขมันของเครื่องบูชา

และดื่มเหล้าองุ่นของเครื่องดื่มบูชาของพวกเขา?

ให้พระเหล่านั้นลุกขึ้นมาช่วยพวกเจ้าสิ!

ให้พระเหล่านั้นมาให้ที่พักพิงแก่พวกเจ้าสิ!

39“จงดูเถิด เราเองนี่แหละคือผู้นั้น!

ไม่มีพระอื่นใดนอกจากเรา

เราทำให้ตายและเราให้ชีวิต

เราทำให้บาดเจ็บและเราจะรักษาให้หาย

และไม่มีผู้ใดช่วยให้พ้นมือของเราไปได้

40เราชูมือขึ้นฟ้าและประกาศว่า

เราดำรงอยู่นิรันดร์ฉันใด

41เมื่อเราลับดาบอันวาววับของเรา

และเมื่อเรากุมการพิพากษาไว้ในมือ

เราจะแก้แค้นศัตรูของเรา

และตอบแทนผู้ที่เกลียดชังเราฉันนั้น

42เราจะทำให้ลูกศรของเราดื่มเลือดจนเมามาย

ส่วนดาบของเราจะกินเนื้อ

คือเลือดเนื้อของผู้ถูกสังหารและเชลย

ศีรษะของบรรดาผู้นำของศัตรู”

43ประชาชาติทั้งหลายเอ๋ย จงชื่นชมยินดีร่วมกับประชากรของพระองค์เถิด32:43 หรือประชาชาติทั้งหลายเอ๋ย จงทำให้ประชากรของพระองค์ชื่นชมยินดี32:43 ฉบับ DSS. (ดูฉบับ LXX. ด้วย) ว่าประชากรของพระองค์เถิด / และขอให้ทูตสวรรค์ทั้งหมดนมัสการพระองค์

เพราะพระองค์จะทรงแก้แค้นให้แก่โลหิตของผู้รับใช้ของพระองค์

พระองค์จะล้างแค้นศัตรูของพระองค์

และลบมลทินบาปให้แก่ดินแดนและประชากรของพระองค์

44โมเสสมากับโยชูวา32:44 ภาษาฮีบรูว่าโฮเชยาเป็นอีกรูปหนึ่งของโยชูวาบุตรนูน กล่าวเนื้อเพลงทั้งบทนี้ให้ประชาชนฟัง 45เมื่อโมเสสท่องข้อความให้อิสราเอลทั้งปวงฟังจบแล้ว 46ก็กล่าวแก่พวกเขาว่า “จงจำใส่ใจทุกถ้อยคำที่ข้าพเจ้าได้ประกาศแก่ท่านอย่างหนักแน่นในวันนี้ เพื่อท่านจะกำชับบุตรหลานให้ใส่ใจปฏิบัติตามทุกถ้อยคำในบทบัญญัตินี้ 47บทบัญญัตินี้ไม่ได้เป็นเพียงถ้อยคำที่พูดไปเปล่าๆ แต่เป็นชีวิตของท่าน โดยบทบัญญัตินี้ท่านจะมีชีวิตอยู่ยาวนานในดินแดนซึ่งท่านกำลังจะข้ามแม่น้ำจอร์แดนไปครอบครอง”

โมเสสจะสิ้นชีวิตบนภูเขาเนโบ

48ในวันเดียวกันนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า 49“จงขึ้นไปบนภูเขาเนโบในเทือกเขาอาบาริม ในโมอับตรงข้ามเมืองเยรีโค และมองดูคานาอัน ดินแดนซึ่งเรายกให้เป็นกรรมสิทธิ์แก่ชนอิสราเอล 50บนภูเขาที่เจ้าขึ้นไปนั้น เจ้าจะตายไปอยู่ร่วมกับญาติพี่น้องของเจ้า เช่นเดียวกับอาโรนพี่ชายของเจ้าซึ่งตายที่ภูเขาโฮร์และถูกรวบไปอยู่กับญาติพี่น้องของเขา 51เพราะเจ้าทั้งสองไม่ได้ให้เกียรติเราต่อหน้าชนอิสราเอลที่สายน้ำแห่งเมรีบาห์คาเดชในถิ่นกันดารศิน และไม่ได้เชิดชูความบริสุทธิ์ของเราในหมู่ชนอิสราเอล 52ฉะนั้นเจ้าจะเห็นดินแดนนั้นแต่ไกล เจ้าจะไม่ได้เข้าไปในดินแดนซึ่งเราจะยกให้ประชากรอิสราเอล”