ዘኍል 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘኍል 1:1-54

የሕዝብ ቈጠራ

1እስራኤላውያን ከግብፅ በወጡ በሁለተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን በሲና ምድረ በዳ ሳሉ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ተናገረው፤ እንዲህም አለው፤ 2“የወንዶቹን ስም አንድ በአንድ በመዘርዘር መላውን የእስራኤል ማኅበረ ሰብ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው ቍጠሯቸው። 3በመላው እስራኤል ያሉትን ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያም በላይ ሆኖ ለውጊያ ብቁ የሆኑትን ወንዶች ሁሉ አንተና አሮን በየምድባቸው ቍጠሯቸው። 4ከየነገዱ የአባቶች ቤት ተጠሪ የሆነ አንድ ሰው ከእናንተ ጋር ይሁን።

5“የሚረዷችሁም ሰዎች ስም የሚከተለው ነው፤

“ከሮቤል የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር፤

6ከስምዖን የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል፤

7ከይሁዳ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን፤

8ከይሳኮር የሶገር ልጅ ናትናኤል፤

9ከዛብሎን የኬሎን ልጅ ኤልያብ፤

10ከዮሴፍ ልጆች ከኤፍሬም የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ፤

ከምናሴ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል፤

11ከብንያም የጋዴዮን ልጅ አቢዳን፤

12ከዳን የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር፤

13ከአሴር የኤክራን ልጅ ፋግኤል፤

14ከጋድ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ፤

15ከንፍታሌም የዔናን ልጅ አኪሬ።”

16እነዚህ ከማኅበረ ሰቡ የተመረጡ የየነገዱ አለቆች ሲሆኑ እነርሱም የእስራኤል ጐሣዎች መሪዎች ነበሩ።

17ሙሴና አሮን ስማቸው የተጠቀሰውን እነዚህን ሰዎች ወሰዱ፤ 18ከዚያም በሁለተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ማኅበረ ሰቡን በሙሉ በአንድነት ሰበሰቧቸው። የተሰበሰቡትም በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የትውልድ ሐረጋቸውን ተናገሩ፤ 19እግዚአብሔር ሙሴን ባዘዘው መሠረት ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ የሆነ ወንዶች ስማቸው አንድ በአንድ ተመዘገበ። እንዲህ አድርጎም በሲና ምድረ በዳ ቈጠራቸው።

20ከእስራኤል የበኵር ልጅ ከሮቤል ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያ በላይ ሆኖ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 21ከሮቤል ነገድ የተቈጠሩት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

22ከስምዖን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 23ከስምዖን ነገድ የተቈጠሩት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነበሩ።

24ከጋድ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 25ከጋድ ነገድ የተቈጠሩትም አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነበሩ።

26ከይሁዳ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 27ከይሁዳ ነገድ የተቈጠሩትም ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነበሩ።

28ከይሳኮር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 29ከይሳኮር ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

30ከዛብሎን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 31ከዛብሎን ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

32ከዮሴፍ ልጆች፦

ከኤፍሬም ዝርያ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 33ከኤፍሬም ነገድ የተቈጠሩትም አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

34ከምናሴ ዝርያዎች፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 35ከምናሴ ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነበሩ።

36ከብንያም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ፤ 37ከብንያም ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

38ከዳን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 39ከዳን ነገድ የተቈጠሩትም ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነበሩ።

40ከአሴር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 41ከአሴር ነገድ የተቈጠሩት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

42ከንፍታሌም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 43ከንፍታሌም ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

44በሙሴና በአሮን፣ እያንዳንዳቸውም ቤተ ሰባቸውን በወከሉት በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል አለቆች የተቈጠሩት ወንዶች እነዚህ ናቸው። 45ስለዚህ እስራኤላውያን ሁሉ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ በእስራኤል ሰራዊት ውስጥ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት በየቤተ ሰባቸው ተቈጠሩ፤ 46ጠቅላላ ቍጥራቸውም ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ነበር።

47የሌዊ ነገድ ቤተ ሰቦች ግን ከሌሎች ጋር አብረው አልተቈጠሩም፤ 48እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ ብሎት ነበርና፤ 49“የሌዊን ነገድ አትቍጠር፤ በእስራኤላውያንም ቈጠራ ውስጥ አታስገባው፤ 50በዚህ ፈንታ ሌዋውያንን በምስክሩ ማደሪያ፣ በውስጡ ባሉት በመገልገያ ዕቃዎች ሁሉ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዙ በማናቸውም ነገሮች ላይ ኀላፊዎች ይሁኑ፤ ማደሪያውንና በውስጡ ያሉትን የመገልገያ ዕቃዎች ይሸከሙ፤ በውስጡ ያገልግሉ፤ ድንኳናቸውንም በዙሪያው ይትከሉ። 51ማደሪያው በሚነሣበት ጊዜ ሌዋውያን ይንቀሉት፤ ማደሪያው በሚተከልበትም ጊዜ ሌዋውያን ያቁሙት፤ ሌላ ሰው ቢቀርብ ግን ይገደል። 52እስራኤላውያን በየምድባቸው ድንኳናቸውን ይትከሉ፤ እያንዳንዱም ሰው በየሰፈሩና በየዐርማው ሥር ይስፈር። 53ሌዋውያን ግን በእስራኤላውያን ማኅበረ ሰብ ላይ ቍጣ እንዳይወርድ ድንኳኖቻቸውን በምስክሩ ማደሪያ ዙሪያ ይትከሉ፤ የምስክሩ ማደሪያ ድንኳን ኀላፊዎች ሌዋውያን ናቸው።”

54እስራኤላውያንም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ይህን ሁሉ አደረጉ።

Thai New Contemporary Bible

กันดารวิถี 1:1-54

สำมะโนประชากร

1วันที่หนึ่งเดือนที่สองของปีที่สอง หลังจากชาวอิสราเอลออกจากประเทศอียิปต์ องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสในเต็นท์นัดพบที่ถิ่นกันดารซีนายว่า 2“จงสำรวจสำมะโนประชากรชุมชนอิสราเอลทั้งหมด แยกเป็นรายตระกูลและครอบครัว ให้ทำบัญชีรายชื่อผู้ชายทุกคน 3เจ้ากับอาโรนจะต้องนับจำนวนผู้ชายในอิสราเอลที่มีอายุยี่สิบปีขึ้นไปซึ่งสามารถทำหน้าที่ในกองทัพได้ โดยแยกพวกเขาออกเป็นหมู่เหล่า 4ผู้นำจากแต่ละเผ่า เผ่าละหนึ่งคนจะเป็นผู้ช่วยของเจ้า 5ต่อไปนี้เป็นรายชื่อของผู้นำที่จะมาช่วยเจ้าได้แก่

จากเผ่ารูเบนคือ เอลีซูร์บุตรเชเดเออร์

6จากเผ่าสิเมโอนคือ เชลูมิเอลบุตรศูริชัดดัย

7จากเผ่ายูดาห์คือ นาห์โชนบุตรอัมมีนาดับ

8จากเผ่าอิสสาคาร์คือ เนธันเอลบุตรศุอาร์

9จากเผ่าเศบูลุนคือ เอลีอับบุตรเฮโลน

10จากบุตรของโยเซฟคือ

จากเผ่าเอฟราอิมคือ เอลีชามาบุตรอัมมีฮูด

จากเผ่ามนัสเสห์คือ กามาลิเอลบุตรเปดาซูร์

11จากเผ่าเบนยามินคือ อาบีดันบุตรกิเดโอนี

12จากเผ่าดานคือ อาหิเยเซอร์บุตรอัมมีชัดดัย

13จากเผ่าอาเชอร์คือ ปากีเอลบุตรโอคราน

14จากเผ่ากาดคือ เอลียาสาฟบุตรเดอูเอล

15จากเผ่านัฟทาลีคือ อาหิราบุตรเอนัน”

16คนเหล่านี้ได้รับการแต่งตั้งจากชุมชนให้เป็นผู้นำเผ่าต่างๆ ตามบรรพบุรุษ พวกเขาเป็นหัวหน้าตระกูลต่างๆ ของอิสราเอล

17โมเสสและอาโรนได้นำชายเหล่านี้ตามบัญชีรายชื่อที่ให้ไว้มา 18และได้เรียกประชุมประชากรทั้งหมดในวันที่หนึ่งเดือนที่สอง ประชาชนได้ระบุบรรพบุรุษของตนตามตระกูลและครอบครัว และได้ขึ้นบัญชีรายชื่อผู้ชายที่มีอายุยี่สิบปีขึ้นไปทีละคน 19ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาโมเสส ดังนั้นเขาจึงนับจำนวนคนเหล่านี้ในถิ่นกันดารซีนาย

20จากวงศ์วานของรูเบนบุตรชายหัวปีของอิสราเอล

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อทีละคนตามตระกูลและตามครอบครัว 21จำนวนพลจากเผ่ารูเบน 46,500 คน

22จากวงศ์วานของสิเมโอน

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อทีละคนตามตระกูลและตามครอบครัว 23จำนวนพลจากเผ่าสิเมโอน 59,300 คน

24จากวงศ์วานของกาด

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 25จำนวนพลจากเผ่ากาด 45,650 คน

26จากวงศ์วานของยูดาห์

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 27จำนวนพลจากเผ่ายูดาห์ 74,600 คน

28จากวงศ์วานของอิสสาคาร์

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 29จำนวนพลจากเผ่าอิสสาคาร์ 54,400 คน

30จากวงศ์วานของเศบูลุน

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 31จำนวนพลจากเผ่าเศบูลุน 57,400 คน

32จากวงศ์วานของเอฟราอิมบุตรโยเซฟ

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 33จำนวนพลจากเผ่าเอฟราอิม 40,500 คน

34จากวงศ์วานของมนัสเสห์บุตรโยเซฟ

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 35จำนวนพลจากเผ่ามนัสเสห์ 32,200 คน

36จากวงศ์วานของเบนยามิน

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 37จำนวนพลจากเผ่าเบนยามิน 35,400 คน

38จากวงศ์วานของดาน

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 39จำนวนพลจากเผ่าดาน 62,700 คน

40จากวงศ์วานของอาเชอร์

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 41จำนวนพลจากเผ่าอาเชอร์ 41,500 คน

42จากวงศ์วานของนัฟทาลี

ผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ออกรบได้ ขึ้นบัญชีรายชื่อตามตระกูลและตามครอบครัว 43จำนวนพลจากเผ่านัฟทาลี 53,400 คน

44ทั้งหมดนี้คือจำนวนผู้ชายที่โมเสส อาโรนและผู้นำทั้งสิบสองเผ่าของอิสราเอลได้นับไว้ แต่ละคนเป็นตัวแทนครอบครัวของเขา 45คือผู้ชายอิสราเอลอายุยี่สิบปีขึ้นไปทุกคนที่ร่วมทัพได้ ได้ถูกนับไว้ตามครอบครัวของเขา 46รวมทั้งสิ้น 603,550 คน

47แต่จำนวนนี้ไม่รวมคนเผ่าเลวี 48องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสกับโมเสสไว้ว่า 49“ยกเว้นเผ่าเลวี ไม่ต้องลงจำนวนในสำมะโนประชากรของอิสราเอล 50แต่จงตั้งคนเลวีให้รับผิดชอบงานเกี่ยวกับพลับพลาแห่งพันธสัญญา พวกเขาต้องเคลื่อนย้ายพลับพลา ดูแลเครื่องใช้และทุกสิ่งที่อยู่ในพลับพลา พวกเขาต้องตั้งเต็นท์อาศัยอยู่รอบพลับพลา 51เมื่อใดก็ตามที่มีการเคลื่อนย้ายพลับพลา คนเลวีจะเป็นผู้ปลดพลับพลาลงหรือตั้งขึ้นใหม่ ผู้อื่นที่เข้าใกล้พลับพลาจะต้องถูกประหารชีวิต 52ชาวอิสราเอลจะต้องตั้งเต็นท์ของตนเป็นหมู่เหล่า แต่ละคนอยู่ในค่ายของตนภายใต้ธงประจำกอง 53ส่วนคนเลวีจะต้องตั้งเต็นท์รอบพลับพลาแห่งพันธสัญญาเพื่อพระพิโรธของพระเจ้าจะไม่ตกแก่ชุมชนอิสราเอล ให้คนเลวีรับผิดชอบดูแลพลับพลาแห่งพันธสัญญา”

54ประชากรอิสราเอลก็ปฏิบัติตามทุกสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งโมเสส