ዘኍል 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

กันดารวิถี 2:1-34

การจัดตั้งค่ายของเผ่าต่างๆ

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสและอาโรนว่า 2“ชนอิสราเอลจะตั้งค่ายรอบเต็นท์นัดพบ ให้ห่างจากเต็นท์นัดพบระยะหนึ่ง แต่ละคนอยู่ภายใต้ธงประจำกองของเขาพร้อมกับธงประจำครอบครัว”

3ด้านตะวันออกของพลับพลาเป็นที่ตั้งค่ายของหมู่เหล่ายูดาห์ภายใต้ธงประจำกองของพวกเขา ผู้นำคือนาห์โชนบุตรอัมมีนาดับ 4จำนวนพล 74,600 คน

5ถัดมาเป็นที่ตั้งค่ายของเผ่าอิสสาคาร์ ผู้นำคือเนธันเอลบุตรศุอาร์ 6จำนวนพล 54,400 คน

7จากนั้นได้แก่เผ่าเศบูลุน ผู้นำคือเอลีอับบุตรเฮโลน 8จำนวนพล 57,400 คน

9รวมพลแนวรบด้านเผ่ายูดาห์ตามหมู่เหล่าของพวกเขาได้ 186,400 คน กลุ่มนี้จะเคลื่อนกำลังออกไปเป็นกลุ่มแรก

10ด้านใต้ของพลับพลาเป็นที่ตั้งค่ายของหมู่เหล่ารูเบนภายใต้ธงประจำกองของพวกเขา ผู้นำคือเอลีซูร์บุตรเชเดเออร์ 11จำนวนพล 46,500 คน

12ถัดมาคือเผ่าสิเมโอน ผู้นำคือเชลูมิเอลบุตรศูริชัดดัย 13จำนวนพล 59,300 คน

14ถัดมาคือเผ่ากาด ผู้นำคือเอลียาสาฟบุตรเดอูเอล2:14 สำเนา MT. บางฉบับว่าเรอูเอล 15จำนวนพล 45,650 คน

16รวมพลแนวรบด้านเผ่ารูเบนตามหมู่เหล่าของพวกเขาได้ 151,450 คน กลุ่มนี้จะเคลื่อนกำลังเป็นกลุ่มที่สอง

17ส่วนเต็นท์นัดพบและค่ายของเผ่าเลวีจะตั้งอยู่กลางค่าย พวกเขาจะเคลื่อนออกตามลำดับเดียวกับการตั้งค่าย แต่ละกลุ่มอยู่ในตำแหน่งของตนเองภายใต้ธงประจำกองของตน

18ด้านตะวันตกของพลับพลาเป็นที่ตั้งค่ายของหมู่เหล่าเอฟราอิมภายใต้ธงประจำกองของพวกเขา ผู้นำคือเอลีชามาบุตรอัมมีฮูด 19จำนวนพล 40,500 คน

20ถัดมาคือเผ่ามนัสเสห์ ผู้นำคือกามาลิเอลบุตรเปดาซูร์ 21จำนวนพล 32,200 คน

22ถัดมาคือเผ่าเบนยามิน ผู้นำคืออาบีดันบุตรกิเดโอนี 23จำนวนพล 35,400 คน

24รวมพลในแนวรบด้านเผ่าเอฟราอิมตามหมู่เหล่าของพวกเขาได้ 108,100 คน พวกเขาจะเคลื่อนพลเป็นกลุ่มที่สาม

25ด้านเหนือของพลับพลาเป็นที่ตั้งค่ายของหมู่เหล่าดานภายใต้ธงประจำกองของพวกเขา ผู้นำคืออาหิเยเซอร์บุตรอัมมีชัดดัย 26จำนวนพล 62,700 คน

27ถัดมาคือเผ่าอาเชอร์ ผู้นำคือปากีเอลบุตรโอคราน 28จำนวนพล 41,500 คน

29ถัดมาคือเผ่านัฟทาลี ผู้นำคืออาหิราบุตรเอนัน 30จำนวนพล 53,400 คน

31รวมพลในแนวรบด้านเผ่าดานได้ 157,600 คน เวลาเดินทางจะอยู่รั้งท้ายขบวนภายใต้ธงประจำกองของพวกเขา

32ทั้งหมดนี้คือชนอิสราเอลนับตามครอบครัวของพวกเขาที่อยู่ในค่าย ตามหมู่เหล่ามีจำนวนทั้งสิ้น 603,550 คน 33ทั้งนี้ไม่นับคนเลวีรวมกับชนอิสราเอลอื่นๆ ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาแก่โมเสส

34ดังนั้นประชากรอิสราเอลจึงได้ทำทุกสิ่งตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งโมเสสคือ แต่ละคนพร้อมกับตระกูลและครอบครัวของตนได้ตั้งค่ายพักแรมภายใต้ธงประจำกองของพวกเขาและเคลื่อนพลตามที่กำหนดไว้