ኤርምያስ 51 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 51:1-64

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በባቢሎንና51፥1 ሌብ ካማይ የከላውዴዎን ማለትም የባቢሎን ስም ነው። በምድሯ ላይ፣

የሚያጠፋ ነፋስ አስነሣለሁ።

2እንዲያበጥሯትና እንዲያወድሟት፣

ባዕዳንን በባቢሎን ላይ እልካለሁ፤

በመከራዋም ቀን፣

ከብበው ያስጨንቋታል።

3ቀስተኛው ቀስቱን እስኪገትር፣

የጦር ልብሱንም እስኪለብስ ፋታ አትስጡት፤

ለወጣቶቿ አትዘኑ፤

ሰራዊቷንም ፈጽማችሁ አጥፉ።51፥3 አጥፉ ለሚለው የዕብራይስጡ ቃል የሚያመለክተው ነገሮችን ወይም ሰዎችን ዳግም ላይመለሱ ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ መስጠት ነው።

4በባቢሎን51፥4 ወይም ከላውዴዎን ምድር ታርደው፣

በአደባባዮቿም እስከ ሞት ቈስለው ይወድቃሉ።

5ምድራቸው51፥5 ወይም የባቢሎናውያን ምድር በእስራኤል ቅዱስ ፊት፣

በበደል የተሞላች ብትሆንም፣

እስራኤልንና ይሁዳን አምላካቸው

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አልጣላቸውም።

6“ከባቢሎን ሸሽታችሁ ውጡ!

ፈጥናችሁም ሕይወታችሁን አትርፉ!

በኀጢአቷ ምክንያት አትጥፉ።

የእግዚአብሔር የበቀል ጊዜ ነው፤

እርሱም የሥራዋን ይከፍላታል።

7ባቢሎን በእግዚአብሔር እጅ የወርቅ ጽዋ ነበረች፤

ምድርንም ሁሉ አሰከረች።

ሕዝቦች ከወይን ጠጇ ጠጡ፤

ስለዚህ አሁን አብደዋል።

8ባቢሎን በድንገት ወድቃ ትሰበራለች፤

ዋይ በሉላት!

ምናልባት ልትፈወስ ስለምትችል፣

ለቍስሏ የሚቀባ መድኀኒት ፈልጉላት።

9“ ‘ባቢሎንን ለመፈወስ ሞክረን ነበር፤

እርሷ ግን ልትፈወስ አትችልም፤

ፍርዷ እስከ ሰማይ ስለ ደረሰ፣

እስከ ደመናም ድረስ ከፍ ስላለ፣

ትተናት ወደየአገራችን እንሂድ።’

10“ ‘እግዚአብሔር ቅንነታችንን መሰከረ፤

ኑ፤ አምላካችን እግዚአብሔር ያደረገውን፣

በጽዮን እንናገር።’

11“ፍላጾችን ሳሉ፤

ጋሻዎችን አዘጋጁ፤

የእግዚአብሔር ሐሳብ ባቢሎንን ለማጥፋት ስለሆነ፣

የሜዶንን ነገሥታት አነሣሥቷል፤

እግዚአብሔር ይበቀላል፤

ስለ ቤተ መቅደሱ ይበቀላል።

12በባቢሎን ቅጥር ላይ ዐላማ አንሡ

ጥበቃውን አጠናክሩ፤

ዘብ ጠባቂዎችን አቁሙ፤

ደፈጣ ተዋጊዎችን አዘጋጁ

እግዚአብሔር በባቢሎን ሕዝብ ላይ የወሰነውን፣

ዐላማውን ያከናውናል።

13አንቺ በብዙ ውሃ አጠገብ የምትኖሪ፣

በሀብትም የበለጸግሽ ሆይ፤

የምትወገጂበት ጊዜ ወጥቷል፤

ፍጻሜሽ ደርሷል።

14የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል በራሱ ምሏል፤

ብዛቱ እንደ አንበጣ መንጋ የሆነ ሰራዊት ያጥለቀልቅሻል፤

እነርሱም በድል አድራጊነት በላይሽ ያቅራራሉ።

15“ምድርን በኀይሉ የሠራ፣

ዓለምን በጥበቡ የመሠረተ፣

ሰማያትንም በማስተዋሉ የዘረጋ እርሱ ነው።

16ድምፁን ባንጐደጐደ ጊዜ በሰማይ ውሆች ይናወጣሉ፤

ጉሙን ከምድር ዳርቻ ወደ ላይ እንዲወጣ ያደርገዋል፤

መብረቅን ከዝናብ ጋር ይልካል፤

ነፋስንም ከግምጃ ቤቱ ያወጣል።

17“እያንዳንዱ ሰው ጅልና ዕውቀት የለሽ ነው፤

የወርቅ አንጥረኛው ሁሉ በሠራው በጣዖቱ ዐፍሯል፤

የቀረጻቸው ምስሎቹ የሐሰት ናቸው፤

እስትንፋስ የላቸውም።

18እነርሱ ከንቱ የፌዝ ዕቃዎች ናቸው፣

ፍርድ ሲመጣባቸው ይጠፋሉ።

19የያዕቆብ ዕድል ፈንታ የሆነው ግን እንደ እነዚህ አይደለም፤

እርሱ የሁሉ ነገር ፈጣሪ ነውና፤

እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነው።

ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው።

20“አንቺ የእኔ ቈመጥ፣

የጦር መሣሪያዬ ነሽ፤

በአንቺ ሕዝቦችን እሰባብራለሁ፤

በአንቺ መንግሥታትን አጠፋለሁ፤

21በአንቺ ፈረሱንና ፈረሰኛውን እሰባብራለሁ፤

በአንቺ ሠረገላውንና ሠረገላ ነጂውን እሰባብራለሁ፤

22በአንቺ ወንዱንና ሴቱን እሰባብራለሁ፤

በአንቺ ሽማግሌውንና ወጣቱን እሰባብራለሁ።

በአንቺ ጐረምሳውንና ኰረዳዪቱን እሰባብራለሁ።

23በአንቺ እረኛውንና መንጋውን እሰባብራለሁ፣

በአንቺ ገበሬውንና በሬውን እሰባብራለሁ፤

በአንቺ ገዦችንና ባለሥልጣኖችን እሰባብራለሁ።

24“በጽዮን ላይ ስላደረሱት ጥፋት ሁሉ ለባቢሎንና በባቢሎን51፥24 ወይም ከላውዴዎን፤ 35 ይመ። ለሚኖሩት ሁሉ ዐይናችሁ እያየ ዋጋቸውን እከፍላቸዋለሁ” ይላል እግዚአብሔር

25“አንቺ ምድርን ሁሉ ያጠፋሽ፣

አጥፊ ተራራ ሆይ፤ እኔ በአንቺ ላይ ነኝ፣”

ይላል እግዚአብሔር

“እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፤

ከገመገም ቍልቍል አንከባልልሻለሁ፤

የተቃጠለም ተራራ አደርግሻለሁ።

26ከአንቺ ለማእዘን የሚሆን ድንጋይ፣

ለመሠረትም የሚሆን ዐለት አይወሰድም፤

ለዘላለም ባድማ ትሆኛለሽ፤”

ይላል እግዚአብሔር

27“በምድር ሁሉ ላይ ሰንደቅ ዐላማ አንሡ!

በሕዝቦች መካከል መለከትን ንፉ!

ሕዝቦችን ለጦርነት በእርሷ ላይ አዘጋጁ፤

የአራራትን፣ የሚኒንና የአስከናዝን መንግሥታት፣

ጠርታችሁ በእርሷ ሰብስቧቸው፤

የጦር አዝማች ሹሙባት፤

ፈረሶችንም እንደ አንበጣ መንጋ ስደዱባት።

28የሜዶንን ነገሥታት፣

ገዦቿንና ባለሥልጣኖቿን ሁሉ፣

በግዛታቸው ሥር ያሉትን አገሮች ሁሉ፣

እነዚህን ሕዝቦች ለጦርነት አዘጋጁባት።

29ሰው በዚያ መኖር እስከማይችል ድረስ፣

የባቢሎንን ምድር ባድማ ለማድረግ፣

እግዚአብሔር በባቢሎን ላይ ያቀደው ስለሚጸና፣

ምድር ትናወጣለች፤ በሥቃይም ትወራጫለች።

30የባቢሎን ጦረኞች መዋጋት ትተዋል፤

በምሽጎቻቸው ውስጥ ተቀምጠዋል፤

ኀይላቸው ተሟጥጧል፤

እንደ ሴት ሆነዋል፤

በማደሪያዎቿም እሳት ተለኵሷል፤

የደጇም መወርወሪያ ተሰብሯል።

31ከተማዪቱ ሙሉ በሙሉ መያዟን፣

ለባቢሎን ንጉሥ ለመንገር፣

አንዱ ወሬኛ ሌላውን ወሬኛ፣

አንዱ መልእክተኛ ሌላውን መልእክተኛ ወዲያው ወዲያው ይከተላል፤

32መልካዎቿ እንደ ተያዙ፣

የወንዝ ዳር ምሽጎቿ እንደ ተቃጠሉ፣

ወታደሮቿም እንደ ተደናገጡ ሊነግሩት ይሯሯጣሉ።”

33የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የባቢሎን ሴት ልጅ በመረገጥ ላይ እንዳለ፣

የእህል መውቂያ አውድማ ናት፤

የመከር ወራቷም ፈጥኖ ይደርስባታል።”

34“የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በላን፣

አድቅቆ ፈጨን፤

እንደ ባዶ ማድጋ አደረገን፤

እንደ ዘንዶ ዋጠን፣

እንደ ጣፋጭ በልቶን ሆዱን ሞላ፤

በኋላም አንቅሮ ተፋን፤

35የጽዮን ነዋሪዎች፣ እንዲህ ይላሉ፤

በሥጋችን51፥35 ወይም በእኛና በልጃችን ላይ የተፈጸመው ላይ የተፈጸመው ግፍ በባቢሎን ላይ ይሁን፤”

ኢየሩሳሌም እንዲህ ትላለች፤

“ደማችን በባቢሎን ምድር በሚኖሩት ላይ ይሁን።”

36ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ እሟገትልሻለሁ፣

በቀልሽንም እኔ እበቀልልሻለሁ፤

ባሕሯን አደርቃለሁ፣

የምንጮቿንም ውሃ።

37ባቢሎን የፍርስራሽ ክምር፣

የቀበሮዎች መፈንጫ፣

የድንጋጤና የመሣለቂያ ምልክት ትሆናለች፤

የሚኖርባትም አይገኝም።

38ሕዝቦቿ ሁሉ እንደ ደቦል አንበሳ ያገሣሉ፤

እንደ አንበሳ ግልገልም ያጕረመርማሉ።

ጕረሯቸው በደረቀ ጊዜ

ድግስ አዘጋጅላቸዋለሁ፤

እንዲሰክሩም አደርጋቸውና

39በሣቅ እየፈነደቁ፣

ለዘላለም ላይነቁ ይተኛሉ።”

ይላል እግዚአብሔር

40“እንደ ጠቦት፣

እንደ አውራ በግና እንደ ፍየል፣

ወደ መታረድ አወርዳቸዋለሁ።

41“ሼሻክ51፥41 ሼሻክ የባቢሎን ስውር ስም ነው። እንዴት ተማረከች!

የምድር ሁሉ ትምክሕትስ እንዴት ተያዘች!

ባቢሎን በሕዝብ ሁሉ ዘንድ፣

ምንኛ አስደንጋጭ ሆነች።

42ባሕር በባቢሎን ላይ ይወጣል፤

ሞገዱም እየተመመ ይሸፍናታል።

43ከተሞቿ ሰው የማይኖርባቸው፣

ዝርም የማይልባቸው፣

ደረቅና በረሓማ ቦታ፣

ባድማ ምድርም ይሆናሉ።

44ቤልን በባቢሎን ውስጥ እቀጣለሁ፤

የዋጠውን አስተፋዋለሁ፤

ሕዝቦች ከእንግዲህ ወደ እርሱ አይጐርፉም፤

የባቢሎንም ቅጥር ይወድቃል።

45“ሕዝቤ ሆይ፤ ከመካከሏ ውጡ!

ሕይወታችሁን አትርፉ!

ከአስፈሪው የእግዚአብሔር ቍጣ አምልጡ።

46ወሬ በምድሪቱ ሲሰማ፣

ተስፋ አትቍረጡ፤ አትፍሩም፤

ገዥ በገዥ ላይ ስለ መነሣቱ፣

ዐመፅም በምድሪቱ ስለ መኖሩ፣

አንድ ወሬ ዘንድሮ፣ ሌላውም ለከርሞ ይመጣል፤

47የባቢሎንን ጣዖታት የምቀጣበት ጊዜ፣

በርግጥ ይመጣልና።

ምድሯ በሙሉ ትዋረዳለች፤

የታረዱትም በሙሉ በውስጧ ይወድቃሉ።

48ሰማይና ምድር በውስጣቸውም ያለው ሁሉ፣

በባቢሎን ላይ እልል ይላሉ፤

አጥፊዎች ከሰሜን ወጥተው፣

እርሷን ይወጓታልና፤”

ይላል እግዚአብሔር

49“በምድር ሁሉ የታረዱት፣

በባቢሎን ምክንያት እንደ ወደቁ፣

ባቢሎንም በእስራኤል በታረዱት ምክንያት መውደቅ ይገባታል።

50ከሰይፍ ያመለጣችሁ ሆይ፤

ሂዱ! ጊዜ አትፍጁ፤

በሩቅ ምድር ያላችሁ እግዚአብሔርን አስታውሱ፤

ኢየሩሳሌምንም አስቧት።”

51“ባዕዳን ሰዎች ወደ ተቀደሰው፣

ወደ እግዚአብሔር ቤት ስለ ገቡ፣

እኛ ተሰድበናል፤

ዕፍረትም ፊታችንን ሸፍኗል፤

ውርደትም ተከናንበናል።”

52“እንግዲህ ጣዖቶቿን የምቀጣበት ዘመን ይመጣል፤”

ይላል እግዚአብሔር

“በምድሯም ሁሉ፤

ቍስለኞች ያቃስታሉ።

53ባቢሎን ወደ ሰማይ ብትወጣም፣

ከፍ ያለ ምሽጓን ብታጠናክርም፣

አጥፊዎች እሰድድባታለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

54“ከባቢሎን ጩኸት፣

ከባቢሎናውያንም51፥54 ወይም ከለዳውያን ምድር፣

የታላቅ ጥፋት ድምፅ ይሰማል።

55እግዚአብሔር ባቢሎንን ያጠፋታል፤

ታላቅ ጩኸቷንም ጸጥ ያደርጋል።

ሞገዳቸው እንደ ታላቅ ውሃ ይተምማል፤

ጩኸታቸውም ያስተጋባል።

56በባቢሎን ላይ አጥፊ ይመጣል፤

ጦረኞቿ ይማረካሉ፤

ቀስታቸውም ይሰበራል፤

እግዚአብሔር ግፍን የሚበቀል፣

ተገቢውንም ሁሉ የሚከፍል አምላክ ነውና።

57ባለሥልጣኖቿንና ጥበበኞቿን፣

ገዦቿንና መኳንንቷን፣ ጦረኞቿንም አሰክራለሁ፤

ለዘላለም ይተኛሉ፤ አይነቁምም፤”

ይላል ስሙ የሰራዊት ጌታ

እግዚአብሔር የሆነው ንጉሥ።

58የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ወፍራሙ የባቢሎን ቅጥር ፈጽሞ ይፈርሳል፤

ከፍ ያሉት ደጆቿም በእሳት ይቃጠላሉ፤

ሰዎቹ በከንቱ ይደክማሉ፤

የሕዝቡም ልፋት ለእሳት ይሆናል።”

59የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ በነገሠ በአራተኛው ዓመት፣ የንጉሡ የግቢ አስከልካይ የነበረው የመሕሤያ ልጅ የኔርያ ልጅ ሠራያ ከንጉሡ ጋር ወደ ባቢሎን በሄደ ጊዜ፣ ነቢዩ ኤርምያስ የሰጠው መልእክት ይህ ነው። 60ኤርምያስ ስለ ባቢሎን ጽፎ ያስቀመጠውን ሁሉ፣ በባቢሎን ላይ የሚመጣውን ጥፋት ሁሉ በብራና ጥቅልል ላይ ጻፈው። 61ለሠራያም እንዲህ አለው፤ “ባቢሎን በደረስህ ጊዜ፣ ይህን ቃል ሁሉ ድምፅህን ከፍ አድርገህ ማንበብ አትዘንጋ። 62እንዲህም በል፤ ‘እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህችን ስፍራ ሰውም ሆነ እንስሳ እስከማይኖርባት ድረስ ለዘላለም ባድማ አደርጋታለሁ ብለሃል።’ 63ይህን ብራና አንብበህ ከጨረስህ በኋላ፣ ድንጋይ አስረህበት ኤፍራጥስ ወንዝ ውስጥ ጣለው፤ 64እንዲህም በል፤ ‘ባቢሎንም እኔ ከማመጣባት ጥፋት የተነሣ፣ እንደዚሁ ትሰጥማለች፤ ከእንግዲህም አትነሣም፤ ሕዝቧም ይወድቃል።’ ”

King James Version

Jeremiah 51:1-64

1Thus saith the LORD; Behold, I will raise up against Babylon, and against them that dwell in the midst of them that rise up against me, a destroying wind;51.1 midst: Heb. heart 2And will send unto Babylon fanners, that shall fan her, and shall empty her land: for in the day of trouble they shall be against her round about. 3Against him that bendeth let the archer bend his bow, and against him that lifteth himself up in his brigandine: and spare ye not her young men; destroy ye utterly all her host. 4Thus the slain shall fall in the land of the Chaldeans, and they that are thrust through in her streets. 5For Israel hath not been forsaken, nor Judah of his God, of the LORD of hosts; though their land was filled with sin against the Holy One of Israel. 6Flee out of the midst of Babylon, and deliver every man his soul: be not cut off in her iniquity; for this is the time of the LORD’s vengeance; he will render unto her a recompence. 7Babylon hath been a golden cup in the LORD’s hand, that made all the earth drunken: the nations have drunken of her wine; therefore the nations are mad. 8Babylon is suddenly fallen and destroyed: howl for her; take balm for her pain, if so be she may be healed. 9We would have healed Babylon, but she is not healed: forsake her, and let us go every one into his own country: for her judgment reacheth unto heaven, and is lifted up even to the skies. 10The LORD hath brought forth our righteousness: come, and let us declare in Zion the work of the LORD our God. 11Make bright the arrows; gather the shields: the LORD hath raised up the spirit of the kings of the Medes: for his device is against Babylon, to destroy it; because it is the vengeance of the LORD, the vengeance of his temple.51.11 bright: Heb. pure 12Set up the standard upon the walls of Babylon, make the watch strong, set up the watchmen, prepare the ambushes: for the LORD hath both devised and done that which he spake against the inhabitants of Babylon.51.12 ambushes: Heb. liers in wait 13O thou that dwellest upon many waters, abundant in treasures, thine end is come, and the measure of thy covetousness. 14The LORD of hosts hath sworn by himself, saying, Surely I will fill thee with men, as with caterpillers; and they shall lift up a shout against thee.51.14 by himself: Heb. by his soul51.14 lift up: Heb. utter 15He hath made the earth by his power, he hath established the world by his wisdom, and hath stretched out the heaven by his understanding. 16When he uttereth his voice, there is a multitude of waters in the heavens; and he causeth the vapours to ascend from the ends of the earth: he maketh lightnings with rain, and bringeth forth the wind out of his treasures.51.16 multitude: or, noise 17Every man is brutish by his knowledge; every founder is confounded by the graven image: for his molten image is falsehood, and there is no breath in them.51.17 is brutish…: or, is more brutish than to know 18They are vanity, the work of errors: in the time of their visitation they shall perish. 19The portion of Jacob is not like them; for he is the former of all things: and Israel is the rod of his inheritance: the LORD of hosts is his name. 20Thou art my battle axe and weapons of war: for with thee will I break in pieces the nations, and with thee will I destroy kingdoms;51.20 with thee: or, in thee, or, by thee 21And with thee will I break in pieces the horse and his rider; and with thee will I break in pieces the chariot and his rider; 22With thee also will I break in pieces man and woman; and with thee will I break in pieces old and young; and with thee will I break in pieces the young man and the maid; 23I will also break in pieces with thee the shepherd and his flock; and with thee will I break in pieces the husbandman and his yoke of oxen; and with thee will I break in pieces captains and rulers. 24And I will render unto Babylon and to all the inhabitants of Chaldea all their evil that they have done in Zion in your sight, saith the LORD. 25Behold, I am against thee, O destroying mountain, saith the LORD, which destroyest all the earth: and I will stretch out mine hand upon thee, and roll thee down from the rocks, and will make thee a burnt mountain. 26And they shall not take of thee a stone for a corner, nor a stone for foundations; but thou shalt be desolate for ever, saith the LORD.51.26 desolate…: Heb. everlasting desolations 27Set ye up a standard in the land, blow the trumpet among the nations, prepare the nations against her, call together against her the kingdoms of Ararat, Minni, and Ashchenaz; appoint a captain against her; cause the horses to come up as the rough caterpillers. 28Prepare against her the nations with the kings of the Medes, the captains thereof, and all the rulers thereof, and all the land of his dominion. 29And the land shall tremble and sorrow: for every purpose of the LORD shall be performed against Babylon, to make the land of Babylon a desolation without an inhabitant. 30The mighty men of Babylon have forborn to fight, they have remained in their holds: their might hath failed; they became as women: they have burned her dwellingplaces; her bars are broken. 31One post shall run to meet another, and one messenger to meet another, to shew the king of Babylon that his city is taken at one end, 32And that the passages are stopped, and the reeds they have burned with fire, and the men of war are affrighted. 33For thus saith the LORD of hosts, the God of Israel; The daughter of Babylon is like a threshingfloor, it is time to thresh her: yet a little while, and the time of her harvest shall come.51.33 it is…: or, in the time that he thresheth her 34Nebuchadrezzar the king of Babylon hath devoured me, he hath crushed me, he hath made me an empty vessel, he hath swallowed me up like a dragon, he hath filled his belly with my delicates, he hath cast me out. 35The violence done to me and to my flesh be upon Babylon, shall the inhabitant of Zion say; and my blood upon the inhabitants of Chaldea, shall Jerusalem say.51.35 The violence…: Heb. My violence51.35 flesh: or, remainder51.35 inhabitant: Heb. inhabitress 36Therefore thus saith the LORD; Behold, I will plead thy cause, and take vengeance for thee; and I will dry up her sea, and make her springs dry. 37And Babylon shall become heaps, a dwellingplace for dragons, an astonishment, and an hissing, without an inhabitant. 38They shall roar together like lions: they shall yell as lions’ whelps.51.38 yell: or, shake themselves 39In their heat I will make their feasts, and I will make them drunken, that they may rejoice, and sleep a perpetual sleep, and not wake, saith the LORD. 40I will bring them down like lambs to the slaughter, like rams with he goats. 41How is Sheshach taken! and how is the praise of the whole earth surprised! how is Babylon become an astonishment among the nations! 42The sea is come up upon Babylon: she is covered with the multitude of the waves thereof. 43Her cities are a desolation, a dry land, and a wilderness, a land wherein no man dwelleth, neither doth any son of man pass thereby. 44And I will punish Bel in Babylon, and I will bring forth out of his mouth that which he hath swallowed up: and the nations shall not flow together any more unto him: yea, the wall of Babylon shall fall. 45My people, go ye out of the midst of her, and deliver ye every man his soul from the fierce anger of the LORD. 46And lest your heart faint, and ye fear for the rumour that shall be heard in the land; a rumour shall both come one year, and after that in another year shall come a rumour, and violence in the land, ruler against ruler.51.46 lest: or, let not 47Therefore, behold, the days come, that I will do judgment upon the graven images of Babylon: and her whole land shall be confounded, and all her slain shall fall in the midst of her.51.47 do…: Heb. visit upon 48Then the heaven and the earth, and all that is therein, shall sing for Babylon: for the spoilers shall come unto her from the north, saith the LORD. 49As Babylon hath caused the slain of Israel to fall, so at Babylon shall fall the slain of all the earth.51.49 As…: or, Both Babylon is to fall, O ye slain of Israel, and with Babylon, etc51.49 the earth: or, the country 50Ye that have escaped the sword, go away, stand not still: remember the LORD afar off, and let Jerusalem come into your mind. 51We are confounded, because we have heard reproach: shame hath covered our faces: for strangers are come into the sanctuaries of the LORD’s house. 52Wherefore, behold, the days come, saith the LORD, that I will do judgment upon her graven images: and through all her land the wounded shall groan. 53Though Babylon should mount up to heaven, and though she should fortify the height of her strength, yet from me shall spoilers come unto her, saith the LORD. 54A sound of a cry cometh from Babylon, and great destruction from the land of the Chaldeans: 55Because the LORD hath spoiled Babylon, and destroyed out of her the great voice; when her waves do roar like great waters, a noise of their voice is uttered: 56Because the spoiler is come upon her, even upon Babylon, and her mighty men are taken, every one of their bows is broken: for the LORD God of recompences shall surely requite. 57And I will make drunk her princes, and her wise men, her captains, and her rulers, and her mighty men: and they shall sleep a perpetual sleep, and not wake, saith the King, whose name is the LORD of hosts. 58Thus saith the LORD of hosts; The broad walls of Babylon shall be utterly broken, and her high gates shall be burned with fire; and the people shall labour in vain, and the folk in the fire, and they shall be weary.51.58 The broad…: or, The walls of broad Babylon51.58 broken: or, made naked

59¶ The word which Jeremiah the prophet commanded Seraiah the son of Neriah, the son of Maaseiah, when he went with Zedekiah the king of Judah into Babylon in the fourth year of his reign. And this Seraiah was a quiet prince.51.59 with: or, on the behalf of51.59 quiet…: or, prince of Menucha, or, chief chamberlain 60So Jeremiah wrote in a book all the evil that should come upon Babylon, even all these words that are written against Babylon. 61And Jeremiah said to Seraiah, When thou comest to Babylon, and shalt see, and shalt read all these words; 62Then shalt thou say, O LORD, thou hast spoken against this place, to cut it off, that none shall remain in it, neither man nor beast, but that it shall be desolate for ever.51.62 desolate: Heb. desolations 63And it shall be, when thou hast made an end of reading this book, that thou shalt bind a stone to it, and cast it into the midst of Euphrates: 64And thou shalt say, Thus shall Babylon sink, and shall not rise from the evil that I will bring upon her: and they shall be weary. Thus far are the words of Jeremiah.