ኢሳይያስ 1 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 1:1-31

1በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን፣ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ፤

እንቢተኛ ሕዝብ

2ሰማያት ሆይ፤ ስሙ! ምድር ሆይ፤ አድምጪ!

እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሯልና፤

“ልጆች ወለድሁ፣ አሳደግኋቸውም፤

እነርሱ ግን ዐመፁብኝ።

3በሬ ጌታውን፣

አህያ የባለቤቱን ጋጥ ያውቃል፤

እስራኤል ግን አላወቀም፤

ሕዝቤም አላስተዋለም።”

4እናንተ ኀጢአተኛ ሕዝብ፣

በደል የሞላበት ወገን፣

የክፉ አድራጊ ዘር፣

ምግባረ ብልሹ ልጆች ወዮላችሁ!

እግዚአብሔርን ትተዋል፤

የእስራኤልን ቅዱስ አቃልለዋል፤

ጀርባቸውንም በእርሱ ላይ አዙረዋል።

5ለምን ዳግመኛ ትመታላችሁ?

ለምንስ በዐመፅ ትጸናላችሁ?

ራሳችሁ በሙሉ ታምሟል፤

ልባችሁ ሁሉ ታውኳል።

6ከእግር ጥፍራችሁ እስከ ራስ ጠጕራችሁ

ጤና የላችሁም፤

ቍስልና ዕባጭ እንዲሁም እዥ ብቻ ነው፤

አልታጠበም፤ አልታሰረም፤

በዘይትም አልለዘበም።

7አገራችሁ ባድማ፣

ከተሞቻችሁ በእሳት የተቃጠሉ ይሆናሉ፤

ዐይናችሁ እያየ፣

መሬታችሁ በባዕድ ይነጠቃል፤

ጠፍም ይሆናል።

8የጽዮን ሴት ልጅ

በወይን አትክልት ውስጥ እንዳለ ዳስ፣

በዱባ ተክል ወስጥ እንደሚገኝ ጐጆ፣

እንደ ተከበበም ከተማ ተተወች።

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፣

እንደ ሰዶም በሆን፣

ገሞራንም በመሰልን ነበር።

10እናንተ የሰዶም ገዦች፤

የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

እናንተ የገሞራ ሰዎች፤

የእግዚአብሔርን ሕግ አድምጡ።

11“የመሥዋዕታችሁ ብዛት

ለእኔ ምኔ ነው?” ይላል እግዚአብሔር

“የሚቃጠለውን የአውራ በግና

የሠቡ እንስሳትን ሥብ ጠግቤአለሁ፤

በበሬ፣ በበግ ጠቦትና በፍየል ደም ደስ

አልሰኝም።

12በፊቴ ለመቅረብ ስትመጡ፣

ይህን ሁሉ እንድታመጡ፣

የመቅደሴን ደጅ እንድትረግጡ ማን ጠየቃችሁ?

13ከንቱውን መባ አታቅርቡ፤

ዕጣናችሁን እጸየፋለሁ፤

የወር መባቻ በዓላችሁን፣

ሰንበቶቻችሁን፣ ጉባኤያችሁንና

በክፋት የተሞላውን ስብሰባችሁን መታገሥ

አልቻልሁም።

14የወር መባቻችሁንና የተደነገጉ በዓሎቻችሁን

ነፍሴ ጠልታለች፤

ሸክም ሆነውብኛል፤

መታገሥም አልቻልሁም።

15እጆቻቸሁን ለጸሎት ወደ እኔ ስትዘረጉ፣

ዐይኖቼን ከእናንተ እሰውራለሁ፤

አብዝታችሁ ብትጸልዩም እንኳ አልሰማችሁም፤

እጆቻችሁ በደም ተበክለዋል፤

16ታጠቡ፤ ራሳችሁንም አንጹ፤

ክፉ ሥራችሁን ከፊቴ አርቁ፤

ክፉ ማድረጋችሁን ተዉ፤

17መልካም ማድረግን ተማሩ፤

ፍትሕን እሹ፣

የተገፉትን አጽናኑ1፥17 ወይም፣ ጨቋኙን ገሥጹ ማለት ነው።

አባት ለሌላቸው ቁሙላቸው፤

ለመበለቶችም ተሟገቱ።

18“ኑና እንዋቀሥ”

ይላል እግዚአብሔር

“ኀጢአታችሁ እንደ ዐለላ ቢቀላ፣

እንደ በረዶ ይነጣል፤

እንደ ደም ቢቀላም፣

እንደ ባዘቶ ነጭ ይሆናል።

19እሺ ብትሉ፣ ብትታዘዙም

የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤

20እንቢ ብላችሁ ብታምፁ ግን

ሰይፍ ይበላችኋል።”

የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና።

21ታማኝ የነበረችው ከተማ

እንዴት አመንዝራ እንደ ሆነች ተመልከቱ፤

ቀድሞ ፍትሕ የሞላባት፣

ጽድቅ የሰፈነባት ነበረች፤

አሁን ግን የነፍሰ ገዳዮች ማደሪያ ሆነች

22ብርሽ ዝጓል፣

ምርጥ የወይን ጠጅሽ ውሃ ገባው፤

23ገዥዎችሽ ዐመፀኞችና

የሌባ ግብረ ዐበሮች ናቸው፤

ሁሉም ጕቦን ይወድዳሉ፤

እጅ መንሻንም በብርቱ ይፈልጋሉ፤

አባት ለሌላቸው አይቆሙም፤

የመበለቶችንም አቤቱታ አይሰሙም።

24ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

የእስራኤል ኀያል እንዲህ ይላል፤

“በባላንጣዎቼ ላይ ቍጣዬን እገልጣለሁ፤

ጠላቶቼንም እበቀላለሁ።

25እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፤

ዝገትሽን ፈጽሜ አጠራለሁ፤

ጕድፍሽንም ሁሉ አስወግዳለሁ።

26ፈራጆችሽን እንደ ጥንቱ፣

አማካሪዎችሽንም እንደ ቀድሞው እመልሳለሁ፤

ከዚያም የጽድቅ መዲና፣

የታመነች ከተማ

ተብለሽ ትጠሪያለሽ።”

27ጽዮን በፍትሕ፣

በንስሓ የሚመለሱ ነዋሪዎቿም በጽድቅ ይዋጃሉ።

28ዐመፀኞችና ኀጢአተኞች ግን በአንድነት ይደቅቃሉ፤

እግዚአብሔርንም የሚተዉ ይጠፋሉ።

29“ደስ በተሰኛችሁባቸው የአድባር ዛፎች

ታፍራላችሁ፤

በመረጣችኋቸውም የአትክልት ቦታዎች

ትዋረዳላችሁ።

30ቅጠሉ እንደ ጠወለገ ወርካ፣

ውሃም እንደሌለው የአትክልት ቦታ ትሆናላችሁ።

31ብርቱ ሰው እንደ ገለባ፣

ሥራውም እንደ ብልጭታ ይሆናል፤

ሁለቱም አብረው ይቃጠላሉ፤

እሳቱንም የሚያጠፋው የለም።”

King James Version

Isaiah 1:1-31

1The vision of Isaiah the son of Amoz, which he saw concerning Judah and Jerusalem in the days of Uzziah, Jotham, Ahaz, and Hezekiah, kings of Judah.

2Hear, O heavens, and give ear, O earth: for the LORD hath spoken, I have nourished and brought up children, and they have rebelled against me. 3The ox knoweth his owner, and the ass his master’s crib: but Israel doth not know, my people doth not consider. 4Ah sinful nation, a people laden with iniquity, a seed of evildoers, children that are corrupters: they have forsaken the LORD, they have provoked the Holy One of Israel unto anger, they are gone away backward.1.4 laden: Heb. of heaviness1.4 gone…: Heb. alienated, or, separated

5¶ Why should ye be stricken any more? ye will revolt more and more: the whole head is sick, and the whole heart faint.1.5 revolt…: Heb. increase revolt 6From the sole of the foot even unto the head there is no soundness in it; but wounds, and bruises, and putrifying sores: they have not been closed, neither bound up, neither mollified with ointment.1.6 ointment: or, oil 7Your country is desolate, your cities are burned with fire: your land, strangers devour it in your presence, and it is desolate, as overthrown by strangers.1.7 overthrown…: Heb. the overthrow of 8And the daughter of Zion is left as a cottage in a vineyard, as a lodge in a garden of cucumbers, as a besieged city. 9Except the LORD of hosts had left unto us a very small remnant, we should have been as Sodom, and we should have been like unto Gomorrah.

10¶ Hear the word of the LORD, ye rulers of Sodom; give ear unto the law of our God, ye people of Gomorrah. 11To what purpose is the multitude of your sacrifices unto me? saith the LORD: I am full of the burnt offerings of rams, and the fat of fed beasts; and I delight not in the blood of bullocks, or of lambs, or of he goats.1.11 he goats: Heb. great he goats 12When ye come to appear before me, who hath required this at your hand, to tread my courts?1.12 to appear: Heb. to be seen 13Bring no more vain oblations; incense is an abomination unto me; the new moons and sabbaths, the calling of assemblies, I cannot away with; it is iniquity, even the solemn meeting.1.13 iniquity: or, grief 14Your new moons and your appointed feasts my soul hateth: they are a trouble unto me; I am weary to bear them. 15And when ye spread forth your hands, I will hide mine eyes from you: yea, when ye make many prayers, I will not hear: your hands are full of blood.1.15 make…: Heb. multiply prayer1.15 blood: Heb. bloods

16¶ Wash you, make you clean; put away the evil of your doings from before mine eyes; cease to do evil; 17Learn to do well; seek judgment, relieve the oppressed, judge the fatherless, plead for the widow.1.17 relieve: or, righten 18Come now, and let us reason together, saith the LORD: though your sins be as scarlet, they shall be as white as snow; though they be red like crimson, they shall be as wool. 19If ye be willing and obedient, ye shall eat the good of the land: 20But if ye refuse and rebel, ye shall be devoured with the sword: for the mouth of the LORD hath spoken it.

21¶ How is the faithful city become an harlot! it was full of judgment; righteousness lodged in it; but now murderers. 22Thy silver is become dross, thy wine mixed with water: 23Thy princes are rebellious, and companions of thieves: every one loveth gifts, and followeth after rewards: they judge not the fatherless, neither doth the cause of the widow come unto them. 24Therefore saith the Lord, the LORD of hosts, the mighty One of Israel, Ah, I will ease me of mine adversaries, and avenge me of mine enemies:

25¶ And I will turn my hand upon thee, and purely purge away thy dross, and take away all thy tin:1.25 purely: Heb. according to pureness 26And I will restore thy judges as at the first, and thy counsellors as at the beginning: afterward thou shalt be called, The city of righteousness, the faithful city. 27Zion shall be redeemed with judgment, and her converts with righteousness.1.27 her…: or, they that return of her

28¶ And the destruction of the transgressors and of the sinners shall be together, and they that forsake the LORD shall be consumed.1.28 destruction: Heb. breaking 29For they shall be ashamed of the oaks which ye have desired, and ye shall be confounded for the gardens that ye have chosen. 30For ye shall be as an oak whose leaf fadeth, and as a garden that hath no water. 31And the strong shall be as tow, and the maker of it as a spark, and they shall both burn together, and none shall quench them.1.31 maker…: or, and his work