ኤርምያስ 50 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 50:1-46

ስለ ባቢሎን የተነገረ መልእክት

51፥15-19 ተጓ ምብ – ኤር 10፥12-16

1እግዚአብሔር ስለ ባቢሎንና ስለ ባቢሎናውያን50፥1 ወይም ከለዳውያን፤ በ8፡25፡35 እና 45 ይመ። ምድር፣ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2“በሕዝቦች መካከል ተናገሩ፤ አስታውቁም፤

ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤ ዐውጁ፤

አንዳች ሳታስቀሩ፣ እንዲህ በሉ፤

‘ባቢሎን ትያዛለች፤

ቤል ይዋረዳል፤

ሜሮዳክ በሽብር ይሞላል፤

ጣዖቶቿ ይዋረዳሉ፤

አማልክቷም ይሸበራሉ።’

3ከሰሜን አንድ መንግሥት መጥቶ ይወጋታል፤

ምድሯንም ባድማ ያደርጋል፤

የሚኖርባትም አይገኝም፤

ሰዎችና እንስሳትም ሸሽተው ይሄዳሉ።

4“በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜም፤”

ይላል እግዚአብሔር

“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ በአንድነት ይመጣሉ፤

አምላካቸውንም እግዚአብሔርን በመፈለግ እያለቀሱ ይመጣሉ።

5ወደ ጽዮን የሚወስደውን መንገድ ይጠይቃሉ፤

ፊታቸውንም ወደዚያ ያቀናሉ።

መጥተውም ከቶ በማይረሳ፣

በዘላለም ቃል ኪዳን፣

ከእግዚአብሔር ጋር ይጣበቃሉ።

6“ሕዝቤ የጠፉ በጎች ሆነዋል፤

እረኞቻቸው አሳቷቸው፤

በተራሮችም ላይ እንዲቅበዘበዙ አደረጓቸው፤

በተራራና በኰረብታ ላይ ተንከራተቱ፤

ማደሪያቸውንም ረሱ።

7ያገኛቸው ሁሉ ይውጣቸዋል፤

ጠላቶቻቸውም፣ ‘እኛ በደለኞች አይደለንም፤

እነርሱ የአባቶቻቸውን ተስፋ እግዚአብሔርን፣

እውነተኛ ማደሪያቸው የሆነውን እግዚአብሔርን በድለዋል’ አሉ።

8“ከባቢሎን ሽሹ፤

የባቢሎናውያንን ምድር ልቀቁ፤

መንጋ እንደሚመራ የፍየል አውራ ሁኑ።

9የታላላቅ መንግሥታትን ማኅበር፣

ከሰሜን በባቢሎን ላይ አስነሣለሁ፤

እነርሱም በእርሷ ላይ ይሰለፋሉ፤

መጥተውም ይይዟታል።

ቀስቶቻቸው ባዶ እጃቸውን እንደማይመለሱ፣

እንደ ሥልጡን ተዋጊዎች ናቸው።

10የባቢሎን ምድር50፥10 ወይም ከላውዴዎን ትዘረፋለች፤

የሚዘርፏትም ሁሉ እስኪበቃቸው ይመዘብሯታል፤”

ይላል እግዚአብሔር

11“እናንተ ርስቴን የበዘበዛችሁ ሆይ፤

ደስ ስላላችሁና ሐሤትም ስላደረጋችሁ፣

በመስክ እንዳለች ጊደር ስለ ፈነጫችሁ፤

እንደ ድንጉላ ፈረስ ስለ አሽካካችሁ፤

12እናታችሁ እጅግ ታፍራለች፤

የወለደቻችሁም ትዋረዳለች።

እርሷም ምድረ በዳ፣ ደረቅ ምድርና በረሓ፣

ከመንግሥታትም ሁሉ ያነሰች ትሆናለች።

13ከእግዚአብሔር ቍጣ የተነሣ ባድማ ትሆናለች እንጂ፣

የሚኖርባት አይገኝም፤

በቍስሎቿም ሁሉ ምክንያት፣

በባቢሎን የሚያልፍ ሁሉ ይገረማል፤ ያፌዝባታልም።

14“እናንተ ቀስት የምትገትሩ ሁሉ፣

በባቢሎን ዙሪያ ተሰለፉ፤

አንዳች ሳታስቀሩ ፍላጾችን ስደዱባት፤

በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአት ሠርታለችና።

15ከየአቅጣጫው ጩኹባት፤

እጇን ትሰጣለች፤ ምሽጓም ይወድቃል፤

ቅጥሮቿ ይፈርሳሉ።

ይህ የእግዚአብሔር በቀል ነውና፣

እርሷን ተበቀሏት፤

በሌሎቹ ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

16ከባቢሎን ዘር የሚዘራውን፣

በመከር ጊዜ ማጭድ የጨበጠውንም ዐጫጅ አጥፉት፤

ከአጥፊው ሰይፍ የተነሣ፣

እያንዳንዱ ወደ ገዛ ሕዝቡ ይመለስ፤

ወደ ገዛ ምድሩም ይሽሽ።

17“እስራኤል አንበሶች ያሳደዱት፣

የተበተነ መንጋ ነው፤

መጀመሪያ የአሦር ንጉሥ፣

ቦጫጭቆ በላው፤

በኋላም የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣

ዐጥንቱን ቈረጣጠመው።”

18ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የአሦርን ንጉሥ እንደ ቀጣሁት ሁሉ፣

የባቢሎንን ንጉሥና ምድሩን እቀጣለሁ።

19እስራኤልንም ወደ መሰማሪያው እመልሰዋለሁ፤

በቀርሜሎስና በባሳን ላይ ይሰማራል፤

በኤፍሬም ተራሮችና በገለዓድም ላይ፣

እስኪጠግብ ይመገባል።

20በእነዚያ ጊዜያት፣ በዚያ ዘመን፣”

ይላል እግዚአብሔር

“የእስራኤል በደል ይፈለጋል፤

አንዳችም አይገኝም፤

የይሁዳም ኀጢአት ይፈለጋል፤

ከቶም የለም፤

እንዲተርፉ ያደረግኋቸውን ቅሬታዎች እምራለሁና።

21“የምራታይምን ምድር፣

የፋቁድ ነዋሪዎችንም፣

አሳድዷቸው፤ ግደሏቸው፤ ፈጽማችሁም አጥፏቸው፤”50፥21 አጥፏቸው ለሚለው የሚተካው የዕብራይስጡ ቃል የሚያመለክተው ነገሮችን ወይም ሰዎችን ዳግም ላይመለሱ ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ መስጠትን ነው፤ 26 ይመ።

ይላል እግዚአብሔር

“ያዘዝኋችሁንም ሁሉ አድርጉ።

22በምድሪቱ የጦርነት ውካታ፣

የታላቅ ጥፋት ድምፅ ተሰማ።

23የምድር ሁሉ መዶሻ፣

እንዴት ተሰበረ! እንዴትስ ደቀቀ!

በሕዝቦች መካከል፣

ባቢሎን እንዴት ባድማ ሆነች!

24ባቢሎን ሆይ፤ ወጥመድ ዘርግቼልሻለሁ፤

አንቺም ሳታውቂ ተይዘሻል፤

እግዚአብሔርን ተገዳድረሻልና፣

ተገኘሽ፤ ተያዝሽም።

25እግዚአብሔር የመሣሪያ ግምጃ ቤቱን ከፍቷል፤

የቍጣውን የጦር ዕቃ አውጥቷል፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በባቢሎናውያን ምድር ሥራ አለውና።

26ከሩቅ መጥታችሁ በእርሷ ላይ ውጡ፤

ጐተራዎቿን አፈራርሱ፤

እንደ እህል ክምር ከምሯት፤

ፈጽማችሁ አጥፏት፤

ምኗም አይቅር።

27ወይፈኖቿን ሁሉ ዕረዱ፤

ወደ መታረጃም ይውረዱ!

የሚቀጡበት ጊዜ፣

ቀናቸው ደርሷልና ወዮላቸው!

28እግዚአብሔር አምላካችን የተበቀለውን፣

ስለ ቤተ መቅደሱ የተበቀለውን በቀል፣

ከባቢሎን የመጡ ኰብላዮችና ስደተኞች፣

በጽዮን የሚናገሩትን ስሟቸው።

29“ቀስት የሚገትሩትን፣

ቀስተኞችን ሁሉ በባቢሎን ላይ ጥሩ፤

አንድም ሰው እንዳያመልጥ፣

ዙሪያውን ሁሉ መሽጉ፤

የእስራኤልን ቅዱስ፣

እግዚአብሔርን አቃልላለችና፣

እንደ ሥራዋ መጠን መልሱላት፤

በሌሎች ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

30ስለዚህ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤

በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

31“አንተ ትዕቢተኛ፤ እነሆ፤ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

“የምትቀጣበት ጊዜ፣

ቀንህ ደርሷልና።

32ትዕቢተኛው ይሰናከላል፤ ይወድቃልም፤

የሚያነሣውም የለም፤

በዙሪያው ያሉትን ሁሉ የሚበላ እሳት፣

በከተሞቹ ውስጥ አስነሣለሁ።”

33የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣

በአንድነት ተጨቍነዋል፤

የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤

ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።

34ነገር ግን ቤዛቸው ብርቱ ነው፤

ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤

ለምድራቸው ዕረፍትን ለመስጠት፤

ተግቶ ይሟገትላቸዋል፤

በባቢሎን የሚኖሩትን ግን ዕረፍት ይነሣቸዋል።

35“ሰይፍ በባቢሎናውያን ላይ መጣ!”

ይላል እግዚአብሔር

“በባቢሎን ነዋሪዎች ላይ፤

በባለሥልጣኖቿና በጥበበኞቿም ላይ ተመዘዘ!

36ሰይፍ በሐሰተኞች ነቢያቷ ላይ መጣ!

እነርሱም ሞኞች ይሆናሉ፤

ሰይፍ በጦረኞቿ ላይ ተመዘዘ፤

እነርሱም ይሸበራሉ።

37ሰይፍ በፈረሰኞቿና በሠረገሎቿ ላይ፣

በመካከሏ ባሉት ባዕዳን ወታደሮች ሁሉ ላይ መጣ!

እነርሱም እንደ ሴቶች ይሆናሉ፤

ሰይፍ በሀብት ንብረቷ ላይ መጣ!

ለዝርፊያም ይሆናሉ።

38ድርቅ50፥38 ወይም ሰይፍ በውሆቿ ላይ መጣ!

እነሆ፤ ይደርቃሉ፤

ምድሪቱ በፍርሀት በሚሸበሩ አማልክት፣

በጣዖትም ብዛት ተሞልታለችና።

39“ስለዚህ የምድረ በዳ አራዊትና የጅብ መኖሪያ፣

የጕጕትም ማደሪያ ትሆናለች፤

ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አይኖርባትም፤

ከትውልድ እስከ ትውልድም የሚቀመጥባት አይገኝም።

40እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን፣

በዙሪያቸውም የነበሩትን ከተሞች ያለ ነዋሪ እንዳስቀራቸው”

ይላል እግዚአብሔር

“እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም አይገኝም።

41“እነሆ፤ ሰራዊት ከሰሜን ይመጣል፤

አንድ ኀያል መንግሥትና ብዙ ነገሥታት፣

ከምድር ዳርቻ ተነሣሥተዋል።

42ቀስትና ጦር ይዘዋል፤

ጨካኞች ናቸው፤ ምሕረትም አያደርጉም፤

በፈረሳቸው እየጋለቡ ሲመጡ፣

ድምፃቸው እንደ ባሕር ሞገድ ይተምማል፤ ያስገመግማል።

አንቺ የባቢሎን ሴት ልጅ ሆይ፤

ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ተዋጊዎች ይመጡብሻል።

43የባቢሎን ንጉሥ ስለ እነርሱ ሰማ፤

እጆቹም በድን ሆኑ፤

ጭንቀት ይዞታል፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት ታምሟል።

44አንበሳ ከዮርዳኖስ ደኖች ድንገት ወጥቶ፣

ወደ ግጦሽ ሜዳ ብቅ እንደሚል፣

እኔም ባቢሎንን ሳይታሰብ ከምድሯ አባርራታለሁ፤

የመረጥሁትንም በእርሷ ላይ እሾማለሁ፤

እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ማንስ ሊገዳደረኝ ይችላል?

የትኛውስ እረኛ ሊቋቋመኝ ይችላል?”

45ስለዚህ እግዚአብሔር በባቢሎን ላይ ያቀደውን፣

በባቢሎናውያንም ምድር ላይ ያሰበውን ስሙ፤

ከመንጋው ታናናሹ ተጐትቶ ይወሰዳል፤

በእነርሱም ምክንያት መሰማሪያቸውን ፈጽሞ ያጠፋል።

46በባቢሎን ውድቀት ድምፅ ትናወጣለች፤

ጩኸቷም በሕዝቦች መካከል ያስተጋባል።

King James Version

Jeremiah 50:1-46

1The word that the LORD spake against Babylon and against the land of the Chaldeans by Jeremiah the prophet.50.1 by…: Heb. by the hand of Jeremiah 2Declare ye among the nations, and publish, and set up a standard; publish, and conceal not: say, Babylon is taken, Bel is confounded, Merodach is broken in pieces; her idols are confounded, her images are broken in pieces.50.2 set up: Heb. lift up 3For out of the north there cometh up a nation against her, which shall make her land desolate, and none shall dwell therein: they shall remove, they shall depart, both man and beast.

4¶ In those days, and in that time, saith the LORD, the children of Israel shall come, they and the children of Judah together, going and weeping: they shall go, and seek the LORD their God. 5They shall ask the way to Zion with their faces thitherward, saying, Come, and let us join ourselves to the LORD in a perpetual covenant that shall not be forgotten. 6My people hath been lost sheep: their shepherds have caused them to go astray, they have turned them away on the mountains: they have gone from mountain to hill, they have forgotten their restingplace.50.6 restingplace: Heb. place to lie down in 7All that found them have devoured them: and their adversaries said, We offend not, because they have sinned against the LORD, the habitation of justice, even the LORD, the hope of their fathers. 8Remove out of the midst of Babylon, and go forth out of the land of the Chaldeans, and be as the he goats before the flocks.

9¶ For, lo, I will raise and cause to come up against Babylon an assembly of great nations from the north country: and they shall set themselves in array against her; from thence she shall be taken: their arrows shall be as of a mighty expert man; none shall return in vain.50.9 expert…: or, destroyer 10And Chaldea shall be a spoil: all that spoil her shall be satisfied, saith the LORD. 11Because ye were glad, because ye rejoiced, O ye destroyers of mine heritage, because ye are grown fat as the heifer at grass, and bellow as bulls;50.11 fat: Heb. big, or, corpulent50.11 bellow…: or, neigh as steeds 12Your mother shall be sore confounded; she that bare you shall be ashamed: behold, the hindermost of the nations shall be a wilderness, a dry land, and a desert. 13Because of the wrath of the LORD it shall not be inhabited, but it shall be wholly desolate: every one that goeth by Babylon shall be astonished, and hiss at all her plagues. 14Put yourselves in array against Babylon round about: all ye that bend the bow, shoot at her, spare no arrows: for she hath sinned against the LORD. 15Shout against her round about: she hath given her hand: her foundations are fallen, her walls are thrown down: for it is the vengeance of the LORD: take vengeance upon her; as she hath done, do unto her. 16Cut off the sower from Babylon, and him that handleth the sickle in the time of harvest: for fear of the oppressing sword they shall turn every one to his people, and they shall flee every one to his own land.50.16 sickle: or, scythe

17¶ Israel is a scattered sheep; the lions have driven him away: first the king of Assyria hath devoured him; and last this Nebuchadrezzar king of Babylon hath broken his bones. 18Therefore thus saith the LORD of hosts, the God of Israel; Behold, I will punish the king of Babylon and his land, as I have punished the king of Assyria. 19And I will bring Israel again to his habitation, and he shall feed on Carmel and Bashan, and his soul shall be satisfied upon mount Ephraim and Gilead. 20In those days, and in that time, saith the LORD, the iniquity of Israel shall be sought for, and there shall be none; and the sins of Judah, and they shall not be found: for I will pardon them whom I reserve.

21¶ Go up against the land of Merathaim, even against it, and against the inhabitants of Pekod: waste and utterly destroy after them, saith the LORD, and do according to all that I have commanded thee.50.21 of Merathaim: or, of the rebels50.21 Pekod: or, Visitation 22A sound of battle is in the land, and of great destruction. 23How is the hammer of the whole earth cut asunder and broken! how is Babylon become a desolation among the nations! 24I have laid a snare for thee, and thou art also taken, O Babylon, and thou wast not aware: thou art found, and also caught, because thou hast striven against the LORD. 25The LORD hath opened his armoury, and hath brought forth the weapons of his indignation: for this is the work of the Lord GOD of hosts in the land of the Chaldeans. 26Come against her from the utmost border, open her storehouses: cast her up as heaps, and destroy her utterly: let nothing of her be left.50.26 from…: Heb. from the end50.26 cast…: or, tread her 27Slay all her bullocks; let them go down to the slaughter: woe unto them! for their day is come, the time of their visitation. 28The voice of them that flee and escape out of the land of Babylon, to declare in Zion the vengeance of the LORD our God, the vengeance of his temple. 29Call together the archers against Babylon: all ye that bend the bow, camp against it round about; let none thereof escape: recompense her according to her work; according to all that she hath done, do unto her: for she hath been proud against the LORD, against the Holy One of Israel. 30Therefore shall her young men fall in the streets, and all her men of war shall be cut off in that day, saith the LORD. 31Behold, I am against thee, O thou most proud, saith the Lord GOD of hosts: for thy day is come, the time that I will visit thee.50.31 most…: Heb. pride 32And the most proud shall stumble and fall, and none shall raise him up: and I will kindle a fire in his cities, and it shall devour all round about him.50.32 the…: Heb. pride

33¶ Thus saith the LORD of hosts; The children of Israel and the children of Judah were oppressed together: and all that took them captives held them fast; they refused to let them go. 34Their Redeemer is strong; the LORD of hosts is his name: he shall throughly plead their cause, that he may give rest to the land, and disquiet the inhabitants of Babylon.

35¶ A sword is upon the Chaldeans, saith the LORD, and upon the inhabitants of Babylon, and upon her princes, and upon her wise men. 36A sword is upon the liars; and they shall dote: a sword is upon her mighty men; and they shall be dismayed.50.36 liars: or, chief stays: Heb. bars 37A sword is upon their horses, and upon their chariots, and upon all the mingled people that are in the midst of her; and they shall become as women: a sword is upon her treasures; and they shall be robbed. 38A drought is upon her waters; and they shall be dried up: for it is the land of graven images, and they are mad upon their idols. 39Therefore the wild beasts of the desert with the wild beasts of the islands shall dwell there, and the owls shall dwell therein: and it shall be no more inhabited for ever; neither shall it be dwelt in from generation to generation. 40As God overthrew Sodom and Gomorrah and the neighbour cities thereof, saith the LORD; so shall no man abide there, neither shall any son of man dwell therein. 41Behold, a people shall come from the north, and a great nation, and many kings shall be raised up from the coasts of the earth. 42They shall hold the bow and the lance: they are cruel, and will not shew mercy: their voice shall roar like the sea, and they shall ride upon horses, every one put in array, like a man to the battle, against thee, O daughter of Babylon. 43The king of Babylon hath heard the report of them, and his hands waxed feeble: anguish took hold of him, and pangs as of a woman in travail. 44Behold, he shall come up like a lion from the swelling of Jordan unto the habitation of the strong: but I will make them suddenly run away from her: and who is a chosen man, that I may appoint over her? for who is like me? and who will appoint me the time? and who is that shepherd that will stand before me?50.44 appoint me…: or, convent me to plead? 45Therefore hear ye the counsel of the LORD, that he hath taken against Babylon; and his purposes, that he hath purposed against the land of the Chaldeans: Surely the least of the flock shall draw them out: surely he shall make their habitation desolate with them. 46At the noise of the taking of Babylon the earth is moved, and the cry is heard among the nations.