ማቴዎስ 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 1:1-25

የኢየሱስ የትውልድ ሐረግ

1፥1-17 ተጓ ምብ – ሉቃ 3፥23-38

1፥3-6 ተጓ ምብ – ሩት 4፥18-22

1፥7-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 3፥10-17

1የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ሐረግ የሚከተለው ነው።

2አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤

ይስሐቅ ያዕቆብን ወለደ፤

ያዕቆብ ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፤

3ይሁዳ ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤

ፋሬስ ኤስሮምን ወለደ፤

ኤስሮምም አራምን ወለደ፤

4አራም አሚናዳብን ወለደ፤

አሚናዳብ ነአሶንን ወለደ፤

ነአሶን ሰልሞንን ወለደ፤

5ሰልሞን ቦዔዝን ከረዓብ ወለደ፤

ቦዔዝ ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤

ኢዮቤድ እሴይን ወለደ፤

6እሴይ ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።

ዳዊት የኦርዮ ሚስት ከነበረችው ሰሎሞንን ወለደ፤

7ሰሎሞን ሮብዓምን ወለደ፤

ሮብዓም አቢያን ወለደ፤

አቢያም አሣፍን ወለደ፤

8አሣፍ ኢዮሣፍጥን ወለደ፤

ኢዮሣፍጥ ኢዮሆራምን ወለደ፤

ኢዮሆራም ዖዝያንን ወለደ፤

9ዖዝያን ኢዮአታምን ወለደ፤

ኢዮአታም አካዝን ወለደ፤

አካዝ ሕዝቅያስን ወለደ፤

10ሕዝቅያስ ምናሴን ወለደ፤

ምናሴ አሞንን ወለደ፤

አሞንም ኢዮስያስን ወለደ፤ 11ኢዮስያስ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ፣

ኢኮንያንንና1፥11 ዮአኪን ማለት ነው፤ 12 ይመ ወንድሞቹን ወለደ።

12ከባቢሎን ምርኮ በኋላ፣

ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤

ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ፤

13ዘሩባቤል አብዩድን ወለደ፤

አብዩድ ኤልያቄምን ወለደ፤

ኤልያቄም አዛርን ወለደ፤

14አዛር ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ አኪምን ወለደ፤

አኪምም ኤልዩድን ወለደ፤

15ኤልዩድ አልዓዛርን ወለደ፤

አልዓዛር ማታንን ወለደ፤

ማታን ያዕቆብን ወለደ፤

16ያዕቆብ ዮሴፍን ወለደ፤ ዮሴፍም የኢየሱስ ክርስቶስ እናት የማርያም ዕጮኛ ነበር።

17እንግዲህ ከአብርሃም እስከ ዳዊት ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከዳዊት እስከ ባቢሎን ምርኮ ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከባቢሎን ምርኮ እስከ ክርስቶስ1፥17 ወይም መሲሕ “ክርስቶስ” (በግሪክ) እና “መሲሕ” (በዕብራይስጥ) ሁለቱም “የተቀባው” የሚል ትርጕም አላቸው። ልደት ዐሥራ አራት ትውልድ ይሆናል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት

18የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ታሪክ እንዲህ ነው፤ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። 19ዕጮኛዋ ዮሴፍ ጻድቅ ሰው ስለ ነበርና ማርያምን በሰው ፊት ሊያጋልጣት ስላልፈለገ በስውር ሊተዋት ወሰነ።

20በዚህ ሐሳብ ሳለ፣ የጌታ መልአክ በሕልም ተገለጠለት፤ እንዲህም አለው፤ “የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፤ ዕጮኛህን ማርያምን ወደ ቤትህ ለመውሰድ አትፍራ፤ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነውና። 21ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ1፥21 ኢየሱስ በግሪኩ ሲሆን በዕብራይስጡ ኢያሱ ነው፤ ትርጕሙም እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና።”

22ጌታ በነቢዩ እንዲህ ሲል የተናገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆነ፤ 23“እነሆ፤ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል ይሉታል፤” ትርጕሙም፣ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ማለት ነው።

24ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቃ፤ ከዚያም የጌታ መልአክ እንዳዘዘው ማርያምን ወደ ቤቱ ወሰዳት።1፥24 ወደ ቤቱ ወሰዳት የሚለው የግሪኩ ቃል ሚስቱ እንድትሆን ወሰዳት ይለዋል። 25ይሁን እንጂ የበኵር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፤ የተወለደውንም ሕፃን፣ “ኢየሱስ” ብሎ ጠራው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

馬太福音 1:1-25

耶穌基督的家譜

1耶穌基督是亞伯拉罕的子孫、大衛的後裔,以下是祂的家譜:

2亞伯拉罕以撒

以撒雅各

雅各猶大和他的兄弟,

3猶大她瑪法勒斯謝拉

法勒斯希斯崙1·3 」希臘文是「亞蘭」。

希斯崙

4亞米拿達

亞米拿達拿順

拿順撒門

5撒門喇合波阿斯

波阿斯路得俄備得

俄備得耶西

6耶西大衛王。

大衛烏利亞的妻子生所羅門

7所羅門羅波安

羅波安亞比雅

亞比雅亞撒

8亞撒約沙法

約沙法約蘭

約蘭烏西雅

9烏西雅約坦

約坦亞哈斯

亞哈斯希西迦

10希西迦瑪拿西

瑪拿西亞們

亞們約西亞

11約西亞耶哥尼雅和他的兄弟,

那時以色列人被擄往巴比倫

12被擄到巴比倫以後,

耶哥尼雅撒拉鐵

撒拉鐵所羅巴伯

13所羅巴伯亞比玉

亞比玉以利亞敬

以利亞敬亞所

14亞所撒督

撒督亞金

亞金以律

15以律以利亞撒

以利亞撒馬但

馬但雅各

16雅各約瑟

約瑟就是瑪麗亞的丈夫,

那被稱為基督1·16 基督」意思是「受膏者」。的耶穌就是瑪麗亞生的。

17這樣,從亞伯拉罕大衛共有十四代,從大衛到被擄至巴比倫也是十四代,從被擄至巴比倫到基督降生也是十四代。

耶穌的降生

18以下是耶穌基督降生的經過。

耶穌的母親瑪麗亞約瑟訂了婚,還沒有成親就從聖靈懷了孕。 19約瑟是個義人,不願公開地羞辱她,便決定暗中和她解除婚約。 20他正在考慮這事的時候,主的一位天使在夢中向他顯現,說:「大衛的後裔約瑟,不要怕,把瑪麗亞娶過來,因為她所懷的孕是從聖靈來的。 21她將生一個兒子,你要給祂取名叫耶穌1·21 耶穌」意思是「救主」。,因為祂要把自己的子民從罪惡中救出來。」

22這一切應驗了主藉著先知所說的話: 23「必有童貞女懷孕生子,祂的名字要叫以馬內利,意思是『上帝與我們同在』。」 24約瑟醒來,就遵從主的天使的吩咐和瑪麗亞結婚, 25只是在她生下孩子之前沒有與她同房。約瑟給孩子取名叫耶穌。