ሚልክያስ 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሚልክያስ 1:1-14

1በሚልክያስ1፥1 ሚልክያስ የስሙ ትርጕም መልእክተኛዬ ማለት ነው። በኩል ወደ እስራኤል የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ንግር ይህ ነው፤

ያዕቆብ ተወደደ፤ ዔሳው ተጠላ

2“እኔ ወድጃችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “እናንተ ግን፣ ‘እንዴት ወደድኸን?’ ትላላችሁ።”

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ዔሳው የያዕቆብ ወንድም አልነበረምን? ያዕቆብን ወደድሁት፤ 3ዔሳውን ግን ጠላሁት፤ ተራሮቹን ባድማ አደረግሁ፤ ርስቱንም ለምድረ በዳ ቀበሮዎች ሰጠሁበት።”

4ኤዶምያስ፣ “ብንደመሰስም እንኳ የፈረሰውን መልሰን እንሠራዋለን” ይል ይሆናል። እግዚአብሔር ጸባኦት ግን እንዲህ ይላል፤ “እነርሱ ይሠሩ ይሆናል፤ እኔ ግን አፈርስባቸዋለሁ፤ ክፉ ምድር፣ እግዚአብሔርም ለዘላለም የተቈጣው ሕዝብ ተብለው ይጠራሉ። 5ይህንም በገዛ ዐይናችሁ ታያላችሁ፤ እናንተም፣ ‘ከእስራኤል ዳርቻ ወዲያ እንኳ እግዚአብሔር ታላቅ ነው!’ ትላላችሁ።

እንከን ያለበት መሥዋዕት

6“ልጅ አባቱን፣ ባሪያም ጌታውን ያከብራል፤ እኔ አባት ከሆንሁ፣ መከበሬ የት አለ? ጌታስ ከሆንሁ መፈራቴ የት አለ?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ካህናት ሆይ፤ ስሜን የምታቃልሉት እናንተ ናችሁ።

“እናንተ ግን፣ ‘ስምህን ያቃለልነው እንዴት ነው?’ ትላላችሁ።

7“በመሠዊያዬ ላይ የረከሰ ምግብ ታስቀምጣላችሁ።

“እናንተ ግን፣ ‘ያረከስንህ እንዴት ነው?’ አላችሁ።

የእግዚአብሔር ገበታ የተናቀ ነው በማለታችሁ ነው። 8የታወረውን እንስሳ ለመሥዋዕት ስታቀርቡ፣ ያ በደል አይደለምን? ዐንካሳውን ወይም በሽተኛውን እንስሳ መሥዋዕት አድርጋችሁ ስታቀርቡ፣ ያስ በደል አይደለምን? ያንኑ ለገዣችሁ ብታቀርቡ፣ በእናንተ ደስ ይለዋልን? ወይስ ይቀበለዋልን?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

9“አሁን ግን እንዲራራልን እግዚአብሔርን ለምኑ፤ እንደዚህ ዐይነቱን መሥዋዕት ይዛችሁ ስትቀርቡ ይቀበላችኋልን?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 10“በመሠዊያዬ ላይ ከንቱ እሳት እንዳታነድዱ፣ ምነው ከእናንተ አንዱ የቤተ መቅደሱን ደጅ በዘጋ ኖሮ! እኔ በእናንተ ደስ አይለኝም፤ ከእጃችሁም ምንም ዐይነት ቍርባን አልቀበልም” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 11“ከፀሓይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ፣ ስሜ በሕዝቦች መካከል የከበረ ይሆናል፤ በየስፍራውም ሁሉ ለስሜ ዕጣንና ንጹሕ ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በሕዝቦች መካከል የከበረ ይሆናልና” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

12“እናንተ ግን የእግዚአብሔር ገበታ፣ ‘ርኩስ ነው’ ምግቡም፣ ‘የተናቀ ነው’ በማለት ታቃልላላችሁ። 13ደግሞም፣ ‘ይህ ድካም ነው’ በማለት በንቀት ጢቅ አላችሁበት” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

“በቅሚያ የመጣውን፣ ዐንካሳውንና የታመመውን እንስሳ ቍርባን አድርጋችሁ ስታቀርቡ ከእጃችሁ መቀበል ይገባኛልን?” ይላል እግዚአብሔር14“በመንጋው ውስጥ ተቀባይነት ያለው ተባዕት በግ ኖሮት ይህንኑ ሊሰጥ ተስሎ ሳለ፣ በማታለል ነውር ያለበትን እንስሳ ለጌታ የሚሠዋ ርጉም ይሁን፤ እኔ ታላቅ ንጉሥ ነኝ፤ ስሜም በሕዝቦች ዘንድ ሊፈራ የሚገባ ነውና” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

瑪拉基書 1:1-14

1以下是耶和華藉瑪拉基以色列人的宣告。

耶和華愛以色列

2耶和華說:「我曾愛你們。」你們卻說:「你在何事上愛我們呢?」耶和華說:「以掃不是雅各的哥哥嗎?但我卻愛雅各3厭惡以掃。我使以掃的山嶺荒涼,把他的地業留給曠野的豺狼。」 4也許以掃的後代以東人會說:「我們現在雖然被毀,但我們要重建毀壞之處。」萬軍之耶和華卻這樣說:「他們儘管建造,但我必拆毀。他們的土地要被稱為『罪惡之地』,他們要被稱為『耶和華永遠惱怒之民。』」 5以色列人啊,你們必親眼看見這事,也必說:「願耶和華在以色列境外受尊崇!」

斥責祭司

6萬軍之耶和華對祭司說:「兒子應當尊敬父親,僕人應當敬畏主人。我是你們的父親,但你們對我的尊敬在哪裡呢?我是你們的主人,但你們對我的敬畏在哪裡呢?你們藐視我的名,卻狡辯說,『我們在何事上藐視過你的名呢?』 7你們把污穢的食物獻在我的祭壇上,還說,『我們在何事上玷污了你呢?』你們說耶和華的桌子是可藐視的。 8你們拿瞎眼、瘸腿和有病的牲畜來獻祭,難道這不是罪過嗎?你試試把這樣的東西送給你的省長,看他會不會悅納你、恩待你。這是萬軍之耶和華說的。」

9現在,你們祈求上帝向我們施恩吧!然而,你們獻上這樣的祭物,祂怎會垂聽你們的祈求呢? 10萬軍之耶和華說:「我真希望你們當中有人把殿門關上,免得你們在我祭壇上枉然點火。因為我不喜悅你們,也不接納你們的祭物。」 11萬軍之耶和華說:「從日出之地到日落之處,列國必尊崇我的名。世上每個角落都有人向我焚香,獻上潔淨的供物。因為我的名必受列國尊崇。 12可是,你們卻褻瀆我的名,竟然說我的桌子是污穢的,上面的祭物是可藐視的。 13你們不屑地說,『哼!這些事真麻煩!』這是萬軍之耶和華說的。你們把搶來的、瘸腿的、有病的獻給我,我豈能接納呢?這是耶和華說的。 14許願時說要獻上羊群中的公羊,後來卻拿傷殘的來獻給主,這種人該受咒詛!因為我是大君王,就是外族人也敬畏我的名。這是萬軍之耶和華說的。」