ማርቆስ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 9:1-50

1ቀጥሎም፣ “እውነት እላችኋለሁ፤ እዚህ ከቆሙት መካከል የእግዚአብሔር መንግሥት በኀይል ስትመጣ እስከሚያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ” አላቸው።

የኢየሱስ መልክ አበራ

9፥2-8 ተጓ ምብ – ሉቃ 9፥28-36

9፥2-13 ተጓ ምብ – ማቴ 17፥1-13

2ከስድስት ቀን በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን አስከትሎ ወደ አንድ ረዥም ተራራ ይዟቸው ወጣ፤ ብቻቸውንም ነበሩ፤ በፊታቸውም ተለወጠ፤ 3ልብሱም በምድር ላይ ማንም ዐጣቢ ዐጥቦ ሊያነጣው በማይችልበት ሁናቴ እጅግ ነጭ ሆነ። 4ኤልያስና ሙሴም ከኢየሱስ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።

5ጴጥሮስም ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ እዚህ ብንኖር ለእኛ መልካም ነው፤ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ የሚሆኑ ሦስት ዳሶች እንሥራ” አለው። 6እጅግ ስለ ፈሩ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።

7ከዚያም ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ፣ “ይህ የምወድደው ልጄ ነው፤ እርሱን ስሙት!” የሚል ድምፅ መጣ።

8ወዲያውም ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከኢየሱስ በቀር ማንም አብሯቸው አልነበረም።

9ከተራራው ላይ በሚወርዱበትም ጊዜ፣ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሣ ድረስ ያዩትን ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው። 10እነርሱም የተናገራቸውን ቃል በልባቸው አሳደሩት፤ ነገር ግን፣ “ከሙታን መነሣት” ምን ማለት እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።

11ከዚያም፣ “ጸሐፍት አስቀድሞ መምጣት ያለበት ኤልያስ ነው ለምን ይላሉ?” ሲሉ ጠየቁት።

12ኢየሱስም፣ እንዲህ አላቸው፤ “ኤልያስ በርግጥ አስቀድሞ መጥቶ ሁሉን ነገር እንደ ነበረ ያደርጋል፤ ታዲያ፣ የሰው ልጅ ብዙ መከራ መቀበልና መናቅ እንዳለበት የተጻፈው ለምን ይመስላችኋል? 13ነገር ግን እላችኋለሁ፤ ኤልያስማ መጥቶ ነበር፤ እነርሱም ስለ እርሱ በተጻፈው መሠረት ያሻቸውን ሁሉ አድርገውበታል።”

ርኩስ መንፈስ ያለበት ልጅ ተፈወሰ

9፥14-283032 ተጓ ምብ – ማቴ 17፥14-1922-23ሉቃ 9፥37-45

14ወደ ቀሩት ደቀ መዛሙርት ተመልሰው ሲመጡ፣ ብዙ ሕዝብ ከብበዋቸው፣ ጸሐፍት ከእነርሱ ጋር ሲከራከሩ አዩ። 15ሕዝቡ ሁሉ ሲያዩት ወዲያው ተደንቀው እጅ ሊነሡት ወደ እርሱ ሮጡ።

16እርሱም፣ “ከእነርሱ ጋር የምትከራከሩት ስለ ምን ጕዳይ ነበር” ሲል ጠየቃቸው።

17ከሕዝቡ መካከል አንድ ሰው እንዲህ አለው፤ “መምህር ሆይ፤ ርኩስ መንፈስ ዐድሮበት ድዳ የሆነውን ልጄን ወደ አንተ አምጥቼዋለሁ፤ 18በተነሣበት ጊዜ ሁሉ ይጥለዋል፤ ዐረፋ ይደፍቃል፤ ጥርሱንም ያፋጫል፤ ሰውነቱም ይደርቃል፤ ርኩስ መንፈሱን እንዲያስወጡት ደቀ መዛሙርትህን ጠየቅኋቸው፤ እነርሱ ግን አልቻሉም።”

19ኢየሱስም መልሶ፣ “የማታምን ትውልድ ሆይ፤ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ልጁን ወደ እኔ አምጡት!” አላቸው።

20ሰዎቹም ወደ እርሱ አመጡት፤ ርኩስ መንፈሱም ኢየሱስን ባየው ጊዜ ልጁን ወዲያውኑ አንዘፈዘፈው፤ እርሱም መሬት ላይ ወድቆ በመንፈራገጥም ዐረፋ ይደፍቅ ጀመር።

21ኢየሱስም የልጁን አባት፣ “ከያዘው ስንት ጊዜው ነው?” ብሎ ጠየቀው።

እርሱም እንዲህ አለው፤ “ከሕፃንነቱ ጀምሮ ነው፤ 22ሊገድለው ፈልጎ ብዙ ጊዜ እሳትም ውስጥ ውሃም ውስጥ፣ ይጥለዋል፤ የሚቻልህ ከሆነ ራራልን፤ ርዳንም።”

23ኢየሱስም፣ “የሚቻልህ ከሆነ አልህ? ለሚያምን ሰው ሁሉም ነገር ይቻላል” አለው።

24ወዲያውኑ የልጁ አባት፣ “አምናለሁ፤ አለማመኔን ርዳው!” በማለት ጮኸ።

25ኢየሱስም ሕዝቡ ወደዚያ እየተንጋጋ በሩጫ መምጣቱን ባየ ጊዜ፣ “አንተ ደንቈሮና ድዳ መንፈስ ከእርሱ ውጣ! ከእንግዲህም ተመልሰህ እንዳትገባበት አዝዝሃለሁ” ብሎ ርኩሱን9፥25 ወይም ክፉ መንፈስ ገሠጸው።

26ርኩሱም መንፈስ እየጮኸ ክፉኛ ካንፈራገጠው በኋላ ከልጁ ወጣ፤ ብዙዎቹ “ሞቷል” እስኪሉ ድረስ ልጁ እንደ በድን ሆነ። 27ኢየሱስ ግን እጁን ይዞ አስነሣው፤ ልጁም ተነሥቶ ቆመ።

28ኢየሱስ ወደ ቤት ከገባ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው፣ “እኛ ልናስወጣው ያልቻልነው ለምንድን ነው?” ብለው ጠየቁት።

29እርሱም፣ “የዚህ ዐይነቱ ሊወጣ የሚችለው በጸሎትና በጾም9፥29 አንዳንድ ቅጆች በጾም የሚለው የላቸውም። ብቻ ነው” አላቸው።

30ከዚያም ተነሥተው በገሊላ በኩል ዐለፉ፤ ኢየሱስም ያሉበትን ስፍራ ማንም እንዲያውቅ አልፈለገም፤ 31ለደቀ መዛሙርቱ፣ “የሰው ልጅ በሰዎች እጅ ዐልፎ ይሰጣል፤ እነርሱም ይገድሉታል፤ ከሦስት ቀንም በኋላ ይነሣል” እያለ ያስተምራቸው ነበር። 32እነርሱ ግን የሚላቸው አልገባቸውም፤ እንዳይጠይቁትም ፈሩ።

ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው?

9፥33-37 ተጓ ምብ – ማቴ 18፥1-5ሉቃ 9፥46-48

33ከዚህ በኋላ ወደ ቅፍርናሆም መጡ። ቤት ከገባ በኋላም፣ “በመንገድ ላይ የምትከራከሩት ስለ ምን ነበር?” ብሎ ጠየቃቸው። 34እነርሱ ግን በመንገድ ላይ የተከራከሩት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው በሚል ስለ ነበር ዝም አሉ።

35ከተቀመጠ በኋላ ዐሥራ ሁለቱን ጠርቶ፣ “መጀመሪያ ለመሆን የሚፈልግ፣ ከሁሉ መጨረሻና የሁሉም አገልጋይ ይሁን” አላቸው።

36ትንሽ ልጅ አምጥቶም በመካከላቸው አቆመ፤ ዐቅፎትም፣ 37“ከእነዚህ ሕፃናት አንዱን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበለኝ ሁሉ የሚቀበለው እኔን ሳይሆን የላከኝን ነው” አላቸው።

የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነው

9፥38-40 ተጓ ምብ – ሉቃ 9፥4950

38ዮሐንስም፣ “መምህር ሆይ፤ አንድ ሰው በስምህ አጋንንት ሲያወጣ አየን፣ እኛን ስለማይከተልም ከለከልነው” አለው።

39ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ፤ “አትከልክሉት፤ ማንም በስሜ ታምር ሠርቶ ወዲያውኑ በእኔ ላይ ክፉ መናገር አይችልም፤ 40የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነውና፤ 41እውነት እላችኋለሁ፣ የክርስቶስ በመሆናችሁ በስሜ አንድ ኩባያ ውሃ የሚሰጣችሁ ሁሉ ዋጋውን አያጣም።

ለሌላው መሰናክል መሆን

42“በእኔ ከሚያምኑት ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ ከባድ የወፍጮ ድንጋይ በዐንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይሻለዋል። 43ስለዚህ እጅህ ብታሰናክልህ ቍረጣት፤ ሁለት እጅ ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመሄድ፣ ጕንድሽ ሆነህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል፤ 44በገሃነም ትሉ አይሞትም፤ እሳቱ አይጠፋምና9፥44 እነዚህ ጥቅሶች በአንዳንድ ቅጆች አይገኙም። 45እግርህ ብታሰናክልህ ቍረጣት፤ ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመጣል፣ ዐንካሳ ሆነህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል፤ 46በገሃነም ትሉ አይሞትም፤ እሳቱ አይጠፋምና9፥46 እነዚህ ጥቅሶች በአንዳንድ ቅጆች አይገኙም። 47ዐይንህ ብታሰናክልህ ጐልጕለህ አውጣት፤ ሁለት ዐይን ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመጣል፣ አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት ይሻልሃል፤

48“በገሃነም ትሉ አይሞትም፤

እሳቱ አይጠፋምና፤

49ሰው ሁሉ በእሳት ይቀመማልና።

50“ጨው መልካም ነው፤ ነገር ግን ጨው ጨውነቱን ቢያጣ እንዴት መልሳችሁ ጣዕም እንዲኖረው ታደርጉታላችሁ? ጨው በውስጣችሁ ይኑራችሁ፤ እርስ በርሳችሁም ተስማሙ።”

Thai New Contemporary Bible

มาระโก 9:1-50

1และพระองค์ตรัสกับเขาว่า “เราบอกความจริงแก่ท่านว่าบางคนซึ่งยืนอยู่ที่นี่ยังไม่ทันจะได้ลิ้มรสความตายก็ได้เห็นอาณาจักรของพระเจ้ามาถึงพร้อมด้วยฤทธิ์อำนาจแล้ว”

ทรงจำแลงพระกาย

(มธ.17:1-13; ลก.9:28-36)

2หกวันต่อมาพระเยซูทรงพาเปโตร ยากอบ และยอห์นขึ้นไปบนภูเขาสูงตามลำพัง พระวรกายก็เปลี่ยนไปต่อหน้าพวกเขาที่นั่น 3ฉลองพระองค์ก็ขาวเป็นมันระยับ จะหาใครในโลกฟอกให้ขาวปานนั้นไม่มีเลย 4และโมเสสกับเอลียาห์ก็ปรากฏกายต่อหน้าพวกเขาและสนทนากับพระเยซู

5เปโตรทูลพระเยซูว่า “พระอาจารย์ ดีจริงที่พวกข้าพระองค์ได้มาอยู่ที่นี่ ให้เราสร้างเพิงขึ้นสามหลัง สำหรับพระองค์หลังหนึ่ง สำหรับโมเสสหลังหนึ่ง และสำหรับเอลียาห์อีกหลังหนึ่ง” 6(เขาไม่รู้ว่าจะพูดอะไรดีเพราะพวกเขาตกใจกลัวมาก)

7แล้วก็มีเมฆปรากฏขึ้นปกคลุมพวกเขาและมีพระสุรเสียงจากเมฆว่า “คนนี้คือลูกที่รักของเรา จงเชื่อฟังเขาเถิด!”

8ทันใดนั้นพวกเขามองไปรอบๆ ก็ไม่เห็นใครอื่นนอกจากพระเยซู

9ขณะลงจากภูเขาพระเยซูทรงกำชับพวกเขาไม่ให้เล่าเหตุการณ์ที่ได้เห็นให้ใครฟังจนกว่าบุตรมนุษย์จะเป็นขึ้นจากตายแล้ว 10ทั้งสามเก็บเรื่องนี้ไว้กับตัวโดยหารือกันถึงความหมายของคำว่า “เป็นขึ้นจากตาย”

11และพวกเขาทูลถามพระองค์ว่า “ทำไมพวกธรรมาจารย์จึงบอกว่าเอลียาห์จะต้องมาก่อน?”

12พระเยซูทรงตอบว่า “ถูกแล้ว เอลียาห์มาก่อนจริงๆ และทำให้ทุกอย่างคืนสู่สภาพเดิม แล้วเหตุใดจึงมีเขียนไว้ว่าบุตรมนุษย์จะต้องทนทุกข์แสนสาหัสและถูกปฏิเสธ? 13แต่เราบอกพวกท่านว่าเอลียาห์มาแล้วและคนเหล่านั้นทำกับเขาตามใจชอบทุกอย่างเหมือนที่มีเขียนไว้เกี่ยวกับเขา”

ทรงรักษาเด็กผู้ชายที่ถูกวิญญาณชั่วสิง

(มธ.17:14-19,22,23; ลก.9:37-45)

14เมื่อพระเยซูกับสาวกทั้งสามคนมาหาสาวกคนอื่นๆ ก็เห็นฝูงชนกลุ่มใหญ่ห้อมล้อมคนเหล่านั้นอยู่และกลุ่มธรรมาจารย์กำลังถกเถียงกับเหล่าสาวก 15ทันทีที่ประชาชนทั้งปวงเห็นพระเยซู พวกเขาก็แปลกใจยิ่งนักและวิ่งเข้ามาทักทายพระองค์

16พระองค์ตรัสถามว่า “พวกท่านกำลังถกเถียงเรื่องอะไรกันหรือ?”

17คนหนึ่งในฝูงชนทูลว่า “พระอาจารย์ข้าพระองค์พาลูกชายมาหาพระองค์ เขาถูกผีสิงทำให้เป็นใบ้ 18เวลาผีเข้าสิงมันก็ทำให้ล้มลงที่พื้น น้ำลายฟูมปาก กัดฟันแน่น ตัวแข็ง ข้าพระองค์ขอให้สาวกของพระองค์ขับผีนี้ออกแต่พวกเขาก็ทำไม่ได้”

19พระเยซูตรัสตอบว่า “โอ คนในยุคที่ขาดความเชื่อ เราจะอยู่กับพวกท่านนานเท่าใด? เราจะทนพวกท่านนานเท่าใด? จงพาเด็กนั้นมาหาเรา”

20พวกเขาจึงพามา เมื่อผีที่สิงอยู่เห็นพระเยซู ทันใดนั้นมันก็ทำให้เด็กชัก ล้มลงกลิ้งไปมาที่พื้น น้ำลายฟูมปาก

21พระเยซูตรัสถามพ่อของเด็กว่า “เขาเป็นอย่างนี้มานานเท่าใด?”

เขาทูลว่า “ตั้งแต่เด็ก 22มันทำให้เขาตกน้ำตกไฟบ่อยๆ เพื่อฆ่าเขา แต่ถ้าพระองค์ทรงช่วยได้ขอโปรดสงสารเราและช่วยเราด้วยเถิด”

23พระเยซูตรัสว่า “ ‘ถ้าช่วยได้’ น่ะหรือ? ทุกสิ่งเป็นไปได้สำหรับคนที่เชื่อ”

24พ่อของเด็กร้องทูลทันทีว่า “ข้าพระองค์เชื่อ ที่ยังขาดความเชื่ออยู่นั้นขอทรงช่วยให้เชื่อด้วยเถิด!”

25พระเยซูทรงเห็นฝูงชนกรูกันเข้ามาจึงตรัสสำทับวิญญาณชั่ว9:25 ภาษากรีกว่าโสโครกว่า “เจ้าผีใบ้หูหนวก เราสั่งให้เจ้าออกมาจากเขาและอย่ากลับเข้าไปสิงเขาอีก”

26ผีนั้นก็หวีดร้องทำให้เด็กชักดิ้นอย่างรุนแรงแล้วออกมา เด็กนั้นแน่นิ่งเหมือนคนตายจนหลายคนพูดว่า “เขาตายแล้ว” 27แต่พระเยซูทรงจับมือของเขาและพยุงขึ้น เขาก็ลุกขึ้นยืน

28หลังจากพระเยซูทรงเข้าไปในบ้าน เหล่าสาวกมาเข้าเฝ้าพระองค์เป็นการส่วนตัวและทูลถามว่า “เหตุใดพวกข้าพระองค์จึงไม่สามารถขับผีนั้นได้?”

29พระองค์ตรัสว่า “ผีแบบนี้จะขับออกได้ก็โดยการอธิษฐานเท่านั้น9:29 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าอธิษฐานและอดอาหารเท่านั้น

30พระเยซูกับสาวกออกจากที่นั่นผ่านไปทางแคว้นกาลิลี พระองค์ไม่ทรงประสงค์ให้ใครรู้ว่าทรงอยู่ที่ไหน 31เพราะทรงสั่งสอนพวกสาวกอยู่ พระองค์ตรัสกับพวกเขาว่า “บุตรมนุษย์จะถูกทรยศให้ตกอยู่ในมือมนุษย์ พวกเขาจะฆ่าพระองค์ และหลังจากนั้นสามวันพระองค์จะเป็นขึ้นจากตาย” 32แต่เหล่าสาวกไม่เข้าใจว่าทรงหมายความว่าอย่างไรและไม่กล้าทูลถามพระองค์

ผู้ใดเป็นใหญ่ที่สุด

(มธ.18:1-5; ลก.9:46-48)

33เมื่อพวกเขามาถึงเมืองคาเปอรนาอุม ขณะพระองค์อยู่ในบ้านพระองค์ทรงถามพวกเขาว่า “ระหว่างทางพวกท่านถกเถียงกันเรื่องอะไร?” 34แต่พวกเขานิ่งอยู่เพราะระหว่างทางพวกเขาเถียงกันเรื่องใครเป็นใหญ่ที่สุด

35พระเยซูประทับนั่งแล้วทรงเรียกสาวกทั้งสิบสองคนมาและตรัสว่า “หากผู้ใดอยากเป็นที่หนึ่งเขาต้องเป็นคนสุดท้ายและเป็นคนรับใช้ของคนทั้งปวง”

36พระองค์ทรงนำเด็กเล็กๆ คนหนึ่งมายืนท่ามกลางพวกเขา ทรงอุ้มเด็กนั้นไว้แล้วตรัสกับพวกเขาว่า 37“ผู้ใดต้อนรับเด็กน้อยเช่นนี้ในนามของเราก็ต้อนรับเรา และผู้ที่ต้อนรับเราก็ไม่ได้ต้อนรับเราเท่านั้นแต่ต้อนรับพระองค์ผู้ทรงส่งเรามาด้วย”

ผู้ที่ไม่ได้ต่อต้านเราก็อยู่ฝ่ายเรา

(ลก.9:49,50)

38ยอห์นทูลว่า “พระอาจารย์ พวกข้าพระองค์เห็นชายคนหนึ่งขับผีออกในพระนามของพระองค์ พวกข้าพระองค์จึงห้ามเขาเพราะเขาไม่ได้อยู่ในกลุ่มของเรา”

39พระเยซูตรัสว่า “อย่าห้ามเขาเลย ไม่มีใครหรอกที่ทำการอัศจรรย์ในนามของเราแล้วครู่ต่อมาก็พูดไม่ดีเกี่ยวกับเรา 40เพราะผู้ใดไม่ได้ต่อต้านเราก็อยู่ฝ่ายเรา 41เราบอกความจริงแก่ท่านว่าผู้ใดเอาน้ำเย็นถ้วยหนึ่งให้ท่านในนามของเราเนื่องจากท่านเป็นคนของพระคริสต์ ผู้นั้นจะไม่ขาดบำเหน็จอย่างแน่นอน”

ต้นเหตุให้ทำบาป

42“และหากผู้ใดเป็นเหตุให้ผู้เล็กน้อยเหล่านี้ที่เชื่อในเราสักคนหนึ่งทำบาป ให้เอาหินโม่ผูกคอผู้นั้นแล้วโยนเขาลงทะเลก็ยังจะดีกว่า 43หากมือของท่านเป็นเหตุให้ทำบาปจงตัดทิ้งเสีย ซึ่งจะเข้าสู่ชีวิตทั้งๆ ที่มือด้วนก็ยังดีกว่ามีสองมือครบแต่ต้องตกนรกซึ่งมีไฟไม่รู้ดับ9:43 สำเนาต้นฉบับบางสำเนามีข้อ 44 ว่าที่ซึ่ง / “ ‘หนอนของคนเหล่านั้นไม่มีวันตาย / และไฟก็ไม่รู้ดับ’ 45และหากเท้าของท่านเป็นเหตุให้ทำบาปจงตัดทิ้งเสีย ซึ่งจะเข้าสู่ชีวิตทั้งๆ ที่ขาพิการยังดีกว่ามีสองเท้าครบแต่ต้องถูกโยนลงนรก9:45 สำเนาต้นฉบับบางสำเนามีข้อ 46 ว่าที่ซึ่ง / “ ‘หนอนของคนเหล่านั้นไม่มีวันตาย / และไฟก็ไม่รู้ดับ’ 47และหากตาของท่านเป็นเหตุให้ทำบาปจงควักทิ้งเสีย ซึ่งจะเข้าสู่อาณาจักรของพระเจ้าโดยมีตาข้างเดียวก็ยังดีกว่ามีสองตาแต่ต้องถูกโยนลงนรก 48ที่ซึ่ง

“ ‘หนอนของคนเหล่านั้นไม่มีวันตาย

และไฟก็ไม่รู้ดับ’9:48 อสย.66:24

49ทุกคนจะถูกเคล้าเกลือชำระด้วยไฟ

50“เกลือเป็นสิ่งที่ดี แต่ถ้ามันหมดความเค็มแล้วจะทำให้กลับเค็มอีกได้อย่างไร? ท่านจงมีเกลืออยู่ในตัวและอยู่ร่วมกันอย่างสงบสุข”