ማርቆስ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 8:1-38

ኢየሱስ አራት ሺሕ ሰዎች መገበ

8፥1-9 ተጓ ምብ – ማቴ 15፥32-39

8፥1-9 ተጓ ምብ – ማር 6፥32-44

8፥11-21 ተጓ ምብ – ማቴ 16፥1-12

1በዚያን ጊዜ፣ እንደ ገና ብዙ ሕዝብ ተሰበሰበ። የሚበሉት ምንም ምግብ ስላልነበራቸው ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፣ እንዲህ አላቸው፤ 2“ከእኔ ጋር ሦስት ቀን ስለ ቈዩና የሚበሉትም ስለሌላቸው እነዚህ ሰዎች ያሳዝኑኛል፤ 3እንዲህ እንደ ተራቡ ወደ ቤታቸው ብሰድዳቸው አንዳንዶቹ ከሩቅ የመጡ ስለ ሆኑ በመንገድ ላይ ዝለው ይወድቃሉ።”

4ደቀ መዛሙርቱም መልሰው፣ “በዚህ ምድረ በዳ እነዚህን ለመመገብ የሚያስችል እንጀራ ከወዴት ይገኛል?” አሉት።

5እርሱም፣ “ስንት እንጀራ አላችሁ?” ብሎ ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “ሰባት” አሉት።

6እርሱም፣ መሬት ላይ እንዲቀመጡ ሕዝቡን አዘዘ፤ ሰባቱን እንጀራ ይዞ ካመሰገነ በኋላ ቈርሶ ለሰዎቹ እንዲያድሉ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፤ እነርሱም ለሕዝቡ ዐደሉት። 7እንዲሁም ትንንሽ ዓሣዎች ነበሯቸው፤ እርሱም ዓሣዎቹን ባርኮ እንዲያድሏቸው አዘዘ። 8ሕዝቡም በልተው ጠገቡ፤ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ የተረፈውን ቍርስራሽ ሰባት መሶብ ሙሉ አነሡ። 9በዚያም አራት ሺሕ ያህል ሰዎች ነበሩ፤ ካሰናበታቸውም በኋላ፣ 10ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ዳልማኑታ ወደ ተባለ ስፍራ ሄደ።

11ፈሪሳውያንም ወጥተው ከኢየሱስ ጋር ይከራከሩ ጀመር። ሊፈትኑትም ፈልገው ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ጠየቁት። 12እርሱም በመንፈሱ እጅግ በመቃተት፣ “ይህ ትውልድ ምልክት የሚፈልገው ለምንድን ነው? እውነት እላችኋለሁ፤ ለዚህ ትውልድ ምንም ምልክት አይሰጠውም!” አለ። 13ከዚያም ትቷቸው በጀልባ ወደ ማዶ ተሻገረ።

የፈሪሳውያንና የሄሮድስ እርሾ

14ደቀ መዛሙርቱ እንጀራ መያዝ ስለ ረሱ፣ ከአንድ እንጀራ በቀር በጀልባ ውስጥ ምንም አልነበራቸውም። 15ኢየሱስም፣ “ተጠንቀቁ፤ ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ እርሾ ተጠበቁ” ብሎ አዘዛቸው።

16እነርሱም እርስ በርሳቸው፣ “እንዲህ የሚለን እኮ እንጀራ ስለሌለን ነው” ተባባሉ።

17ኢየሱስም ሐሳባቸውን ዐውቆ፣ እንዲህ አላቸው፤ “እንጀራ ስለሌለን ነው በማለት ምን ያነጋግራችኋል? አሁንም አታስተውሉምን? ልብስ አትሉምን? ወይስ ልባችሁ ደንድኗል? 18ዐይን እያላችሁ አታዩምን? ጆሮ እያላችሁ አትሰሙምን? አታስታውሱምን? 19አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺሕ ሰው በቈረስሁ ጊዜ ስንት መሶብ ሙሉ ትርፍራፊ አነሣችሁ?”

እነርሱም፣ “ዐሥራ ሁለት” አሉት።

20“ሰባቱንስ እንጀራ ለአራት ሺሕ በቈረስሁ ጊዜ ስንት መሶብ ሙሉ ትርፍራፊ አነሣችሁ?” አላቸው።

እነርሱም፣ “ሰባት” አሉት።

21እርሱም፣ “እስከ አሁን አላስተዋላችሁም ማለት ነውን?” አላቸው።

በቤተ ሳይዳ የተፈወሰው ዐይነ ስውር

22ከዚያም ወደ ቤተ ሳይዳ መጡ፤ ጥቂት ሰዎችም አንድ ዐይነ ስውር ወደ ኢየሱስ አምጥተው እንዲዳስሰው ለመኑት። 23እርሱም የዐይነ ስውሩን እጅ ይዞ ከሰፈር ውጭ አወጣው፤ በዐይኖቹም ላይ እንትፍ ብሎበት፣ እጁንም በላዩ ጭኖ፣ “ምን የሚታይህ ነገር አለ?” ሲል ጠየቀው።

24እርሱም ቀና ብሎ አይቶ፣ “ሰዎች እንደ ዛፍ ሲንቀሳቀሱ አያለሁ” አለ።

25ኢየሱስም እንደ ገና እጆቹን በሰውየው ዐይኖች ላይ ጫነ፤ በዚህ ጊዜ ዐይኖቹ በሩ፤ ብርሃኑም ተመለሰለት፤ ሁሉንም ነገር አጥርቶ ማየት ቻለ። 26ከዚያም፣ “ወደ መንደሩ አትግባ! በመንደሩም ለማንም አትናገር8፥26 አንዳንድ ቅጆች በመንደሩም፤ ለማንም አትናገር! የሚለው የላቸውም። ብሎ ወደ ቤቱ ሰደደው።

ጴጥሮስ ስለ ኢየሱስ የነበረው ግንዛቤ

8፥27-29 ተጓ ምብ – ማቴ 16፥13-16ሉቃ 9፥18-20

27ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ፊልጶስ ቂሳርያ መንደሮች ሄደ፤ በመንገድ ላይ ሳሉም ደቀ መዛሙርቱን፣ “ሰዎች እኔን ማን ይሉኛል?” ብሎ ጠየቃቸው።

28እነርሱም፣ “መጥምቁ ዮሐንስ የሚሉህ አሉ፤ ሌሎች ኤልያስ ነው ይሉሃል፤ ሌሎች ደግሞ ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ” ብለው ነገሩት።

29ቀጥሎም፣ “እናንተሳ ማን ትሉኛላችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

ጴጥሮስም፤ “አንተ ክርስቶስ8፥29 በግሪኩ ክርስቶስ፣ በዕብራይስጡ መሲሕ የሁለቱም ቃላት ትርጕም የተቀባው ማለት ነው። ነህ” አለው።

30ኢየሱስም ስለ እርሱ ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቃቸው።

ኢየሱስ ስለ ሞቱ አስቀድሞ ተናገረ

8፥31–9፥1 ተጓ ምብ – ማቴ 16፥21-28ሉቃ 9፥22-27

31ከዚያም የሰው ልጅ ብዙ መከራ እንደሚቀበል፣ በሽማግሌዎች፣ በካህናት አለቆችና በጸሐፍት እንደሚናቅ፣ እንደሚገደል፣ ከሦስት ቀንም በኋላ እንደሚነሣ ያስተምራቸው ጀመር።

32እርሱም ይህን በግልጽ ነገራቸው። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስን ለብቻው ወስዶ ይገሥጸው ጀመር።

33ኢየሱስ ግን ዘወር ብሎ ደቀ መዛሙርቱን እያየ ጴጥሮስን፣ “አንተ ሰይጣን፣ ወደ ኋላዬ ሂድ! አንተ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን ነገር አታስብምና” በማለት ገሠጸው።

34ከዚህ በኋላ፣ ሕዝቡን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ራሱን ይካድ፤ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። 35ነፍሱን8፥35 የግሪኩ ቃል ሕይወት ወይም ነፍስ ማለት ይሆናል። ለማዳን የሚወድድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋት ሁሉ ግን ያድናታል። 36ሰው ዓለሙ ሁሉ የእርሱ ቢሆንና ነፍሱን ቢያጣ ምን ይጠቅመዋል? 37ለመሆኑ፣ ሰው ለነፍሱ ምን መተኪያ አለው? 38በዚህ ዘማዊና ኀጢአተኛ ትውልድ መካከል በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፣ የሰው ልጅም በአባቱ ግርማ፣ ከቅዱሳን መላእክት ጋር ሲመጣ ያፍርበታል።”

Thai New Contemporary Bible

มาระโก 8:1-38

พระเยซูทรงเลี้ยงคนสี่พันคน

(มธ.15:32-39; 16:1-12)

1ครั้งนั้นมีฝูงชนกลุ่มใหญ่อีกกลุ่มหนึ่งมาชุมนุมกัน เนื่องจากพวกเขาไม่มีอาหารรับประทาน พระเยซูจึงทรงเรียกเหล่าสาวกมาและตรัสว่า 2“เราสงสารคนเหล่านี้ พวกเขามาอยู่กับเราสามวันแล้วและไม่มีอะไรกิน 3ถ้าให้เขากลับไปทั้งที่ยังหิวอยู่กลัวว่าจะหมดแรงกลางทางเพราะบางคนก็มาไกล”

4เหล่าสาวกทูลว่า “แต่ในที่ห่างไกลแบบนี้จะหาขนมปังที่ไหนมาพอเลี้ยงพวกเขา?”

5พระเยซูตรัสถามว่า “พวกท่านมีขนมปังกี่ก้อน?”

เขาทูลว่า “เจ็ดก้อน”

6พระองค์ทรงบอกฝูงชนให้นั่งลงที่พื้น เมื่อทรงรับขนมปังเจ็ดก้อนและขอบพระคุณพระเจ้าแล้ว พระองค์ก็ทรงหักขนมปังส่งให้เหล่าสาวกแจกประชาชน 7พวกเขามีปลาเล็กๆ สองสามตัวด้วย พระองค์ก็ทรงขอบพระคุณพระเจ้าสำหรับปลาเหล่านี้และทรงให้เหล่าสาวกนำไปแจกเช่นกัน 8ประชาชนได้รับประทานจนอิ่มหนำ หลังจากนั้นเหล่าสาวกเก็บเศษที่เหลือได้เจ็ดตะกร้าเต็ม 9มีผู้ชายราวสี่พันคนที่นั่น และเมื่อทรงให้พวกเขากลับไปแล้ว 10พระองค์ก็เสด็จลงเรือกับเหล่าสาวกไปยังเขตเมืองดาลมานูธา

11พวกฟาริสีมาหาพระเยซูและเริ่มซักถามพระองค์ พวกเขาขอให้ทรงแสดงหมายสำคัญจากสวรรค์เพื่อทดสอบพระองค์ 12พระองค์ทรงถอนพระทัยยาวและตรัสว่า “ทำไมคนในยุคนี้ถามหาหมายสำคัญ? เราบอกความจริงแก่ท่านว่าคนในยุคนี้จะไม่ได้รับหมายสำคัญใดๆ เลย” 13แล้วพระองค์ก็ทรงละจากพวกเขา เสด็จลงเรือ และข้ามฟากไป

เชื้อของพวกฟาริสีและเฮโรด

14เหล่าสาวกลืมเอาขนมปังมาด้วยและในเรือก็มีขนมปังอยู่เพียงก้อนเดียว 15พระเยซูได้ตรัสเตือนพวกเขาว่า “จงระวังเชื้อของพวกฟาริสีและเฮโรด”

16พวกเขาจึงหารือกันและพูดว่า “ที่พระองค์ตรัสเช่นนี้เพราะเราไม่มีขนมปัง”

17พระเยซูทรงทราบจึงตรัสว่า “ทำไมพวกท่านจึงพูดกันเรื่องไม่มีขนมปัง? พวกท่านยังไม่เห็นไม่เข้าใจหรือ? ใจท่านแข็งกระด้างใช่ไหม? 18หรือท่านมีตาแต่มองไม่เห็น มีหูแต่ไม่ได้ยินหรือ? และท่านจำไม่ได้หรือ? 19เมื่อเราหักขนมปังห้าก้อนให้คนห้าพันคน พวกท่านเก็บที่เหลือได้กี่ตะกร้า?”

พวกเขาทูลว่า “สิบสองตะกร้า”

20พระองค์ทรงถามว่า “และเมื่อเราหักขนมปังเจ็ดก้อนให้คนสี่พันคน พวกท่านเก็บได้กี่ตะกร้า?”

พวกเขาทูลว่า “เจ็ดตะกร้า”

21พระองค์ตรัสกับพวกเขาว่า “พวกท่านยังไม่เข้าใจอีกหรือ?”

ทรงรักษาคนตาบอดที่เบธไซดา

22เมื่อมาถึงเมืองเบธไซดามีคนพาชายตาบอดมาทูลอ้อนวอนให้พระเยซูทรงแตะต้อง 23พระองค์ทรงจูงมือคนตาบอดออกไปนอกหมู่บ้าน ทรงบ้วนน้ำลายลงที่ตาของคนนั้น และวางพระหัตถ์เหนือเขาและตรัสถามว่า “ท่านเห็นอะไรบ้างไหม?”

24เขาเงยหน้าขึ้นมองและทูลว่า “ข้าพเจ้าเห็นคนเหมือนต้นไม้เดินไปเดินมา”

25พระเยซูทรงวางพระหัตถ์ที่ตาของเขาอีกครั้งหนึ่ง แล้วตาของเขาก็เปิด สายตากลับเป็นปกติ และมองเห็นทุกอย่างชัดเจน 26พระเยซูจึงทรงให้เขากลับบ้านโดยกำชับว่า “อย่าเข้าไปในหมู่บ้าน8:26 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าอย่าไปเล่าให้ใครๆในหมู่บ้านฟัง

เปโตรรับว่าพระเยซูเป็นพระคริสต์

(มธ.16:13-16; ลก.9:18-20)

27พระเยซูกับเหล่าสาวกไปยังหมู่บ้านต่างๆ แถบซีซารียาฟีลิปปี ระหว่างทางพระองค์ทรงถามสาวกว่า “ผู้คนเขาพูดกันว่าเราเป็นใคร?”

28สาวกทูลว่า “บางคนก็ว่าเป็นยอห์นผู้ให้บัพติศมา บางคนก็ว่าเป็นเอลียาห์ และบางคนก็ว่าเป็นผู้เผยพระวจนะคนหนึ่ง”

29พระองค์ตรัสถามว่า “แล้วพวกท่านเล่า? พวกท่านว่าเราเป็นใคร?”

เปโตรทูลว่า “พระองค์ทรงเป็นพระคริสต์8:29 หรือพระเมสสิยาห์

30พระเยซูทรงเตือนพวกเขาไม่ให้บอกใคร

พระเยซูทรงทำนายถึงการสิ้นพระชนม์

(มธ.16:21-28; ลก.9:22-27)

31นับแต่นั้นมาพระองค์ทรงเริ่มสั่งสอนเหล่าสาวกว่าบุตรมนุษย์ต้องทนทุกข์หลายประการ บรรดาผู้อาวุโส พวกหัวหน้าปุโรหิต กับเหล่าธรรมาจารย์จะไม่ยอมรับพระองค์ และพระองค์จะต้องถูกประหารและในวันที่สามจะทรงเป็นขึ้นมาอีก 32พระองค์ตรัสเรื่องนี้อย่างชัดแจ้ง ฝ่ายเปโตรดึงพระองค์เลี่ยงไปอีกทางหนึ่งและทูลติติงพระองค์

33แต่เมื่อพระเยซูทรงหันมามองดูเหล่าสาวก พระองค์ทรงตำหนิเปโตรว่า “ถอยไปเจ้าซาตาน! เจ้าไม่ได้มีความคิดอย่างพระเจ้าแต่คิดอย่างมนุษย์”

34แล้วพระองค์ทรงเรียกฝูงชนกับเหล่าสาวกเข้ามาและตรัสว่า “หากผู้ใดต้องการจะตามเรามา เขาต้องปฏิเสธตัวเอง รับกางเขนของตนแบก และตามเรามา 35เพราะผู้ใดต้องการเอาชีวิต8:35 ภาษากรีกหมายถึงชีวิตหรือจิตวิญญาณเช่นเดียวกับข้อ 36รอดผู้นั้นจะเสียชีวิต แต่ผู้ใดพลีชีวิตเพื่อเราและข่าวประเสริฐผู้นั้นจะได้ชีวิตรอด 36จะมีประโยชน์อะไรที่คนๆ หนึ่งจะได้โลกนี้ทั้งโลกแต่ต้องสูญเสียจิตวิญญาณของตน? 37หรือใครจะเอาอะไรมาแลกกับจิตวิญญาณของตนได้? 38ในชั่วอายุที่บาปหนาและเอาใจออกห่างจากพระเจ้านี้ ถ้าผู้ใดอับอายในตัวเราและถ้อยคำของเรา บุตรมนุษย์ก็จะอับอายในตัวเขาเมื่อพระองค์เสด็จมาด้วยพระเกียรติสิริแห่งพระบิดาพร้อมกับเหล่าทูตสวรรค์ผู้บริสุทธิ์”