以斯拉記 9 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以斯拉記 9:1-15

以斯拉的禱告

1這些事以後,眾首領來告訴我說:「以色列民眾、祭司和利未人還沒有與當地各族分開,他們仍隨從迦南人、人、比利洗人、耶布斯人、亞捫人、摩押人、埃及人和亞摩利人的可憎行為。 2他們為自己和自己的兒子娶這些人的女兒為妻,使聖潔的民族與當地的人混雜。首領和官員是這種不忠之事的罪魁。」 3一聽到這些,我便撕裂衣服和外袍,拔掉頭髮和鬍鬚,驚懼地坐下。 4聽了以色列上帝的話而戰抖的人都聚集在我周圍,因為流亡歸來的人不忠。我驚懼地坐在那裡,直到獻晚祭的時候。

5獻晚祭的時候,我滿懷憂傷地起來,穿著那撕裂的衣服和外袍,雙膝跪下,向我的上帝耶和華伸出雙手, 6說:「我的上帝啊,我羞愧難當,不敢抬頭看你,因為我們的惡行滅頂,我們的罪惡滔天。 7從我們的祖先開始到現在,我們罪惡深重。由於我們的罪惡,我們、我們的君王和祭司都落在外邦君王的手中,被他們殺害、俘虜、搶掠和羞辱,如同今天的光景。 8但如今我們的上帝耶和華暫且施恩於我們,為我們存留一些餘民,使我們安然住在這聖潔之地。你使我們眼睛明亮,在我們受奴役時賜給我們一點生機。 9雖然我們是奴隸,我們的上帝卻沒有離棄受奴役的我們,祂在波斯眾王面前施恩於我們,使我們復興、得以重建毀壞的上帝的殿,讓我們在猶大耶路撒冷有護牆。

10「如今,我們的上帝啊,事已至此,我們還能說什麼呢?因為我們背棄了你的誡命, 11就是你藉著你的僕人——眾先知給我們的吩咐,『你們將要佔領的那片土地被當地人的污穢玷污,他們的可憎行徑使那裡充滿污穢。 12所以不要讓你們的女兒嫁給他們的兒子,也不要讓你們的兒子娶他們的女兒。永不可為他們謀求平安和好處。這樣,你們就可強盛,吃那裡的美好出產,也可將那地方留給你們的子孫作為永久的產業。』

13「雖然因為我們的惡行和大罪,這一切事情臨到我們,但我們的上帝啊,你給我們的懲罰比我們該受的輕多了,你還施恩給我們留下這些餘民。 14我們豈能再違背你的誡命,與這些行為可憎的人通婚?若我們這樣行,你豈不發怒毀滅我們,使我們無一倖免嗎? 15以色列的上帝耶和華啊,你是公義的,所以我們這些餘民今天才得以倖存。看啊,我們在你面前身負罪惡,因而無人能在你面前站立得住。」

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 9:1-15

ከባዕዳን ጋር ስለ ተደረገው ጋብቻ የዕዝራ ጸሎት

1እነዚህ ነገሮች ከተፈጸሙ በኋላ መሪዎቹ ወደ እኔ መጥተው እንዲህ አሉኝ፤ “ካህናቱንና ሌዋውያኑን ጨምሮ የእስራኤል ሕዝብ ከጎረቤቶቻቸው ከከነዓናውያን፣ ከኬጢያውያን፣ ከፌርዛውያን፣ ከኢያቡሳውያን፣ ከአሞናውያን ርኩሰት ራሳቸውን አልለዩም። 2ሴቶቻቸውን ለራሳቸውና ለልጆቻቸው ሚስት አድርገው ወስደዋል፤ የተቀደሰውንም ዘር ከምድር ሕዝቦች ጋር ደባልቀዋል፤ በዚህ በደል ዋነኛ የሆኑትም መሪዎቹና ሹማምቱ ናቸው።”

3እኔም ይህን በሰማሁ ጊዜ፣ መጐናጸፊያዬንና ካባዬን ቀደድሁ፤ የራሴን ጠጕርና ጢሜን ነጨሁ፤ እጅግ ደንግጬም ተቀመጥሁ። 4በደል ከፈጸሙት ምርኮኞች የተነሣም በእስራኤል አምላክ ቃል የተንቀጠቀጡት ሁሉ በዙሪያዬ ተሰበሰቡ፤ እኔም እስከ ሠርክ መሥዋዕት ድረስ እጅግ እንደ ደነገጥሁ በዚያው ተቀመጥሁ።

5ከዚያም፣ የሠርክ መሥዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ፣ የተቀደደውን መጐናጸፊያዬንና ካባዬን እንደ ለበስሁ በሐዘን ከተቀመጥሁበት ተነሣሁ፤ በጕልበቴም ተንበርክኬ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር እጆቼን በመዘርጋት፣ 6እንዲህ ስል ጸለይሁ፤

“አምላኬ ሆይ፤ ኀጢአታችን ከራሳችን በላይ ሆኗል፤ በደላችንም እስከ ሰማያት ደርሷል፤ አምላኬ ሆይ፤ ፊቴን ወደ አንተ ቀና ለማድረግ ፈራሁ፤ እጅግም ፈራሁ። 7ከአባቶቻችን ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በደላችን ታላቅ ነው። ከኀጢአታችንም የተነሣ፣ ዛሬ እንደ ሆነው ሁሉ እኛም ሆንን፣ ነገሥታቶቻችንና ካህናቶቻችን በባዕዳን ነገሥታት እጅ ወድቀን ለሰይፍ፣ ለምርኮ፣ ለብዝበዛና ለውርደት ተዳርገናል።

8“አሁን ግን እግዚአብሔር አምላካችን ቅሬታ ይተውልን ዘንድ፣ በመቅደሱም ውስጥ ጽኑ ስፍራ ይሰጠን ዘንድ፣ ለጥቂት ጊዜ ቸርነቱን አሳይቶናል፤ ስለዚህ አምላካችን ለዐይናችን ብርሃን ሰጠን፤ በባርነትም ሳለን ለጥቂት ጊዜ ዕረፍት ሰጠን። 9ባሮች ብንሆንም፣ አምላካችን ግን ባሮች ሆነን እንድንቀር አልተወንም፤ ነገር ግን በፋርስ ነገሥታት ፊት ቸርነቱን አሳየን፤ የአምላካችንን ቤት እንደ ገና እንድንሠራና ፍርስራሾቿን እንድንጠግን አዲስ ሕይወት ሰጠን፤ በይሁዳና በኢየሩሳሌምም የመከላከያ ቅጥር ሰጠን።

10“አሁን ግን አምላካችን ሆይ፤ ከዚህ በኋላ ምን እንላለን? ትእዛዞችህን አቃልለናልና፤ 11ያቃለልነውም በባሮችህ በነቢያት አማካይነት፣ ‘ለመውረስ የምትገቡባት ምድር በሕዝቦቿ ርኩሰት ተበክላለች፤ ከዳር እስከ ዳርም በአጸያፊ ድርጊታቸውና በርኩሰታቸው ተሞልታለች፤ 12ስለዚህ ሴቶች ልጆቻችሁን ለወንዶች ልጆቻቸው አትስጡ፤ ሴቶች ልጆቻቸውንም ለወንዶች ልጆቻችሁ አትውሰዱ። ብርቱዎች እንድትሆኑ፣ የምድሪቱን መልካም ነገር እንድትበሉና ለልጆቻችሁም የዘላለም ርስት እንድታወርሱ ከእነርሱ ጋር ምንም ዐይነት ውል አታድርጉ’ ብለህ የሰጠኸውን ትእዛዝ ነው።

13“ይህ ሁሉ የደረሰብን በክፉ ሥራችንና በብዙ በደላችን ምክንያት ነው፤ አምላካችን ሆይ፤ አንተ ግን እንደ በደላችን ብዛት አልቀጣኸንም፤ ይልቁንም ቅሬታን ተውህልን። 14ታዲያ ትእዛዞችህን እንደ ገና ተላልፈን እንዲህ ያለውን አስጸያፊ ድርጊት ከሚፈጽሙ ሕዝቦች ጋር መጋባት ተገቢ ነውን? አንተስ ቅሬታ እስከማይኖር ወይም አንድም ሰው እስከማይድን ድረስ ተቈጥተህ አታጠፋንምን? 15የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ እኛም በዚህ ዕለት ተርፈን በሕይወት አለን። እነሆ፣ በፊትህ ከነበደላችን ቀርበናል፤ ከበደላችን የተነሣ ግን በፊትህ ሊቆም የሚችል ማንም የለም።”