歷代志下 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志下 1:1-17

所羅門王求智慧

1大衛的兒子所羅門鞏固了自己的王位。因為他的上帝耶和華與他同在,使他極其偉大。

2所羅門召集所有以色列人,包括千夫長、百夫長、審判官、首領和族長, 3與他們一起去基遍的邱壇,因為那裡有上帝的會幕,是耶和華的僕人摩西在曠野製造的。 4大衛已經把上帝的約櫃從基列·耶琳搬到耶路撒冷,因為他在那裡為約櫃搭了一個帳篷。 5戶珥的孫子、烏利的兒子比撒列造的銅壇在基遍耶和華的會幕前,所羅門和會眾就在那裡求問耶和華。 6所羅門上到耶和華會幕前的銅壇那裡,獻上一千頭祭牲作為燔祭。

7當天晚上,上帝向所羅門顯現,問他:「你要我給你什麼?只管求吧。」 8所羅門回答說:「你厚待我父大衛,並讓我繼位。 9耶和華上帝啊,求你成就你給我父大衛的應許。你立我為王,使我統治這多如地上塵土的百姓。 10現在,求你賜我智慧和知識以帶領他們。不然,誰能治理這麼多的百姓呢?」 11上帝對所羅門說:「你既然有此心願,不為自己求富貴、資財、尊榮、長壽,也沒有求滅絕你的敵人,只求智慧和知識以治理我的子民——我交在你王權之下的百姓, 12我必賜你智慧和知識,並且我還要賜你空前絕後的富貴、資財和尊榮。」

13於是,所羅門基遍邱壇的會幕前回到耶路撒冷治理以色列

所羅門王的兵力和財富

14所羅門組建了戰車和騎兵,有一千四百輛戰車、一萬二千名騎兵,駐紮在屯車城和他所在的耶路撒冷15王使耶路撒冷的金銀多如石頭,使香柏木多如丘陵的無花果樹。 16所羅門的馬匹都是由王室商隊從埃及古厄按定價買來的。 17他們從埃及買來的車馬,每輛車六百塊銀子,每匹馬一百五十塊銀子,他們也把車馬賣給人諸王和亞蘭諸王。

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 1:1-17

ሰሎሞን ጥበብ እንዲሰጠው ጠየቀ

1፥2-13 ተጓ ምብ – 3፥4-15

1፥14-17 ተጓ ምብ – 1ነገ 10፥26-292ዜና 9፥25-28

1አምላኩ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ እጅግም ስላገነነው፣ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በመንግሥቱ ላይ ተደላድሎ ተቀመጠ።

2ከዚያም ሰሎሞን ለመላው እስራኤል፣ ለሻለቆች፣ ለመቶ አለቆች፣ ለዳኞች፣ ለእስራኤል መሪዎች ሁሉ እንዲሁም ለየቤተ ሰቡ አለቆች ተናገረ። 3የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ በምድረ በዳ የሠራው የአምላክ የመገናኛ ድንኳን በዚያ ስለ ነበር፣ ሰሎሞንና መላው ጉባኤ በገባዖን ወዳለው ኰረብታ ሄዱ። 4በዚያ ጊዜ ዳዊት የአምላክን ታቦት ከቂሪያት ይዓሪም በኢየሩሳሌም ድንኳን ተክሎ ወዳዘጋጀለት ስፍራ አምጥቶት ነበር፤ 5ይሁን እንጂ የሆር ልጅ፣ የኡሪ ልጅ ባስልኤል የሠራው መሠዊያ በገባዖን በእግዚአብሔር ማደሪያ ድንኳን ፊት ለፊት ይገኝ ነበር፤ ስለዚህ ሰሎሞንና ጉባኤው ይህንኑ ፈለጉ። 6ሰሎሞንም በእግዚአብሔር ፊት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ወዳለው ወደ ናሱ መሠዊያ ወጥቶ በላዩ ላይ አንድ ሺሕ የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረበ።

7በዚያ ሌሊት እግዚአብሔር ለሰሎሞን ተገልጦ፣ “እንድሰጥህ የምትፈልገውን ሁሉ ጠይቀኝ” አለው።

8ሰሎሞን እግዚአብሔርን እንዲህ አለው፤ “ለአባቴ ለዳዊት ታላቅ በጎነት አድርገህለታል፤ እኔንም በእግሩ ተክተህ አንግሠኸኛል። 9አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ ያነገሥኸኝ ብዛቱ እንደ ትቢያ በሆነ ሕዝብ ላይ ስለሆነ፣ ለአባቴ ለዳዊት የሰጠኸው ተስፋ ይጽና። 10ይህን ሕዝብ ለመምራት እንድችል፣ ጥበብና ዕውቀትን ስጠኝ፤ ይህ ካልሆነ ይህን ታላቅ ሕዝብህን ማን ሊገዛ ይችላል?”

11እግዚአብሔርም ሰሎሞንን እንዲህ አለው፤ “የልብህ መሻት ይህ ስለሆነ፣ ብልጽግናና ሀብት ወይም የጠላቶችህን ነፍስ ወይም ረዥም ዕድሜ ስላልጠየቅህ፣ ነገር ግን ባነገሥሁህ ሕዝቤ ላይ የምትገዛበትን ጥበብና ዕውቀት ስለ ጠየቅህ፣ 12ጥበብና ዕውቀት ይሰጥሃል፤ እንዲሁም ከአንተ በፊት የነበረ ማንኛውም ንጉሥ ያላገኘውን፣ ከአንተ በኋላም የሚነሣው የማያገኘውን ብልጽግና፣ ሀብትና ክብር እሰጥሃለሁ።”

13ሰሎሞንም የመገናኛው ድንኳን ካለበት ከገባዖን ኰረብታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፤ በእስራኤልም ላይ ነገሠ።

14ሰሎሞን ሠረገሎችንና1፥14 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል። ፈረሶችን ሰበሰበ፤ እርሱም አንድ ሺሕ አራት መቶ ሠረገሎችና ዐሥራ ሁለት ሺሕ ፈረሶች ነበሩት፤ እነርሱንም በሠረገላ ከተሞችና እርሱ ባለበት በኢየሩሳሌም ከተማ አኖራቸው። 15ንጉሡም ወርቁና ብሩ በኢየሩሳሌም እንደ ተራ ድንጋይ እንዲበዛ፣ ዝግባውም በየኰረብታው ግርጌ እንደሚገኝ የሾላ ዛፍ እንዲበዛ አደረገ። 16የሰሎሞንም ፈረሶች የመጡት ከግብፅና ከቀዌ1፥16 ምናልባት ኪልቂያ ናት ነበር፤ ከቀዌ የገዟቸውም የንጉሡ ነጋዴዎች ነበሩ። 17ከግብፅ ያስገቧቸውም አንዱን ሠረገላ በስድስት መቶ ሰቅል1፥17 7 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር፣ አንዱን ፈረስ በአንድ መቶ አምሳ ሰቅል1፥17 1.7 ኪሎ ግራም ነው። ብር ገዝተው ነው። እነዚህንም ደግሞ ለኬጢያውያንና ለሶርያውያን ነገሥታት ሁሉ ይሸጡላቸው ነበር።