尼希米記 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

尼希米記 1:1-11

尼希米的禱告

1以下是哈迦利亞的兒子尼希米的記述。

波斯亞達薛西二十年基斯流月1·1 基斯流月」即希伯來曆的九月,陽曆是十一月中旬到十二月中旬。,我在書珊城裡。 2猶大來了我的一個兄弟哈拿尼和一些人,我問他們有關從流亡之地歸回的猶太餘民和耶路撒冷的情況。 3他們回答說:「那些從流亡之地歸回猶大省的人深陷苦難,飽受凌辱。耶路撒冷的城牆已經倒塌,城門也被燒毀。」

4我一聽見這消息,就坐下痛哭,悲傷了好幾天。我在天上的上帝面前禁食禱告,說:

5「天上的上帝耶和華啊,你是偉大而可畏的上帝,你向愛你、守你誡命的人守約,施慈愛。 6僕人在你面前晝夜為你的眾僕人以色列民祈禱,求你睜眼察看,側耳傾聽。我承認以色列人向你所犯的罪,以及我和我的家族所犯的罪。 7我們行事敗壞,沒有遵守你賜給你僕人摩西的誡命、律例和典章。 8求你顧念你對你僕人摩西所說的話,『如果你們不忠,我必把你們驅散到列邦中。 9但如果你們轉向我,謹遵我的誡命,即使你們流落天涯,我也必從那裡把你們召集到我選為我名所在之地。』 10我們是你的僕人、你的子民,是你用大能大力救贖的。 11主啊,求你側耳聽你僕人的禱告,垂聽那些喜愛敬畏你名的眾僕人的祈求,使你僕人今天亨通,在王面前蒙恩。」

我是王的侍酒總管。

New Amharic Standard Version

ነህምያ 1:1-11

የነህምያ ጸሎት

1የሐካልያ ልጅ የነህምያ ቃል፤

በሃያኛው ዓመት ካሴሉ በተባለው ወር በሱሳ ግንብ ሳለሁ፣ 2ከወንድሞቼ አንዱ የሆነው አናኒ፣ ከሌሎች ጥቂት ሰዎች ጋር ከይሁዳ መጣ፤ እኔም ከምርኮ ስለ ተረፉት የአይሁድ ቅሬታዎችና ስለ ኢየሩሳሌም ጠየቅኋቸው።

3እነርሱም፣ “በሕይወት ተርፈው ከምርኮ ወደ አገራቸው የተመለሱት ሰዎች በታላቅ መከራና ውርደት ላይ ይገኛሉ፤ የኢየሩሳሌም ቅጥር ፈራርሷል፤ በሮቿም በእሳት ተቃጥለዋል” አሉኝ።

4ይህን ነገር በሰማሁ ጊዜ አያሌ ቀናት ዐዘንሁ፤ ጾምሁ፤ ጸለይሁም። 5ከዚያም እንዲህ አልሁ፤

“ለሚወድዱህና ትእዛዝህን ለሚያከብሩ የፍቅርህን ቃል ኪዳን የምትጠብቅ ታላቅና የተፈራህ አምላክ፣ የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ 6ባሪያህ ስለ አገልጋዮችህ ስለ እስራኤል ሕዝብ ቀንና ሌሊት በፊትህ የሚጸልየውን ጸሎት ለመስማት ጆሮህ ይንቃ፤ ዐይንህም ይከፈት። እኔንና የአባቴን ቤት ጨምሮ እኛ እስራኤላውያን አንተን በመበደል የሠራነውን ኀጢአት እናዘዛለሁ። 7በአንተ ላይ እጅግ ክፉ ሥራ ሠርተናል፤ ለባሪያህም ለሙሴ የሰጠኸውን ትእዛዝ፣ ሥርዐትና ሕግ አልጠበቅንም።

8“ለባሪያህ ለሙሴ እንዲህ ስትል የሰጠኸውን ቃል ዐስብ፤ ‘ታማኞች ካልሆናችሁ፣ በአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፤ 9ወደ እኔ ብትመለሱና ትእዛዞቼን ብትፈጽሙ፣ የተሰደዱት ወገኖቻችሁ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ እንኳ ቢበተኑ፣ ከዚያ እሰበስባቸዋለሁ፤ ለስሜም ማደሪያ ወደ መረጥሁት ስፍራ አመጣቸዋለሁ።’

10“እነዚህም በታላቁ ኀይልህና በብርቱ እጅህ የተቤዠሃቸው ባሪያዎችህና ሕዝብህ ናቸው። 11ጌታ ሆይ፤ የባሪያህን ጸሎት፣ ስምህን በመፍራት ደስ የሚሰኙትን የባሪያዎችህንም ጸሎት ጆሮህ ታድምጥ። በዚህ ሰው ፊት ሞገስን አድርገህለት ዛሬ ለባሪያህ መከናወንን ስጠው።”

በዚያን ጊዜ እኔ የንጉሡ ጠጅ አሳላፊ ነበርሁ።