መዝሙር 94 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 94:1-23

መዝሙር 94

የእግዚአብሔር ፍትሕ

1የበቀል አምላክ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤

የበቀል አምላክ ሆይ፤ ደምቀህ ተገለጥ።

2አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤

ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።

3ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4የእብሪት ቃላት ያዥጐደጕዳሉ፤

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጕራ ይነዛሉ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤

ርስትህንም አስጨነቁ።

6መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤

የድኻ ዐደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤

የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤

እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣

ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣

ከንቱም እንደ ሆነ ያውቃል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የምትገሥጸው፣

ከሕግህም የምታስተምረው ሰው ምስጉን ነው።

13ለኀጢአተኞች ጕድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣

እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።

14እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤

ርስቱንም አይተውም።

15ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤

ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።

16ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?

ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?

17እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣

ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።

18እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።

19የውስጤ ጭንቀት በበዛ መጠን፣

ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

20ዐመፃን ሕጋዊ የሚያደርግ፣

የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን?

21በጻድቁ ላይ ተሰልፈው ይወጣሉ፤

በንጹሑም ላይ ሞት ይፈርዳሉ።

22ለእኔ ግን እግዚአብሔር ምሽግ፣

አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል።

23በደላቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል፤

በክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፤

እግዚአብሔር አምላካችን ይደመስሳቸዋል።

New International Version

Psalms 94:1-23

Psalm 94

1The Lord is a God who avenges.

O God who avenges, shine forth.

2Rise up, Judge of the earth;

pay back to the proud what they deserve.

3How long, Lord, will the wicked,

how long will the wicked be jubilant?

4They pour out arrogant words;

all the evildoers are full of boasting.

5They crush your people, Lord;

they oppress your inheritance.

6They slay the widow and the foreigner;

they murder the fatherless.

7They say, “The Lord does not see;

the God of Jacob takes no notice.”

8Take notice, you senseless ones among the people;

you fools, when will you become wise?

9Does he who fashioned the ear not hear?

Does he who formed the eye not see?

10Does he who disciplines nations not punish?

Does he who teaches mankind lack knowledge?

11The Lord knows all human plans;

he knows that they are futile.

12Blessed is the one you discipline, Lord,

the one you teach from your law;

13you grant them relief from days of trouble,

till a pit is dug for the wicked.

14For the Lord will not reject his people;

he will never forsake his inheritance.

15Judgment will again be founded on righteousness,

and all the upright in heart will follow it.

16Who will rise up for me against the wicked?

Who will take a stand for me against evildoers?

17Unless the Lord had given me help,

I would soon have dwelt in the silence of death.

18When I said, “My foot is slipping,”

your unfailing love, Lord, supported me.

19When anxiety was great within me,

your consolation brought me joy.

20Can a corrupt throne be allied with you—

a throne that brings on misery by its decrees?

21The wicked band together against the righteous

and condemn the innocent to death.

22But the Lord has become my fortress,

and my God the rock in whom I take refuge.

23He will repay them for their sins

and destroy them for their wickedness;

the Lord our God will destroy them.