2 ዜና መዋዕል 5 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 5:1-14

1ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሠራው ሥራ ሁሉ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ አባቱ ዳዊት የቀደሰውን ብሩንና ወርቁን፣ ዕቃዎቹንም ሁሉ አምጥቶ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግምጃ ቤት አኖራቸው።

ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ

5፥2–6፥11 ተጓ ምብ – 1ነገ 8፥1-21

2ከዚያ በኋላ ሰሎሞን የእግዚአብሔርን የኪዳን ታቦት ከዳዊት ከተማ ከጽዮን እንዲያመጡ፣ የእስራኤልን ሽማግሌዎች፣ የየነገዱን መሪዎች ሁሉና የእስራኤላውያንን የቤተ ሰብ አለቆች በኢየሩሳሌም ሰበሰበ። 3የእስራኤልም ሰዎች ሁሉ የሰባተኛው ወር በዓል በሚከበርበት ጊዜ፣ በንጉሡ ፊት ተሰበሰቡ።

4የእስራኤል ሽማግሌዎች በተሰበሰቡም ጊዜ ሌዋውያኑ ታቦቱን አነሡት፤ 5ታቦቱን፣ የመገናኛ ድንኳኑንና በውስጡ ያሉትን የተቀደሱ ዕቃዎች ሁሉ ይዘው ወደ ላይ ወጡ፤ ሌዋውያን የሆኑ ካህናትም ተሸከሟቸው። 6ንጉሥ ሰሎሞንና በአጠገቡ የተሰበሰበው መላው የእስራኤል ጉባኤ ስፍር ቍጥር የሌላቸውን በጎችና በሬዎች በታቦቱ ፊት ሠዉ።

7ካህናቱም የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦት የቤተ መቅደሱ ውስጠኛ ክፍል ወደ ሆነው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ አግብተው ከኪሩቤል ክንፍ በታች ባለው ስፍራው አኖሩት። 8ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ከታቦቱ በላይ ባለው ስፍራ ላይ ዘርግተው፣ ታቦቱንና መሎጊያዎቹን ሸፈኑ። 9መሎጊያዎቹም በጣም ረጃጅም ከመሆናቸው የተነሣ፣ ታቦቱ እስካለበት ድረስ ያሉት ጫፎቻቸው ከቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ለፊት ይታዩ ነበር፤ ከመቅደሱ ውጭ ግን አይታዩም ነበር፤ ዛሬም እዚያው ቦታ ይገኛሉ። 10እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ኪዳን ባደረገ ጊዜ፣ ሙሴ በኮሬብ ተራራ በውስጡ ካስቀመጣቸው ከሁለቱ ጽላቶች በቀር በታቦቱ ውስጥ ምንም አልነበረም። 11ካህናቱም ከቤተ መቅደሱ ወጡ፤ እዚያ የነበሩት ካህናት በምድባቸው መሠረት ባይሆንም፣ ሁሉም ራሳቸውን ቀድሰው ነበር። 12መዘምራን የነበሩት ሌዋውያን ሁሉ፣ አሳፍ፣ ኤማን፣ ሄማንና ኤዶታም፣ ወንዶች ልጆቻቸውና የሥጋ ዘመዶቻቸው ሁሉ ያማረ ቀጭን በፍታ ለብሰው፣ ከመሠዊያው በስተ ምሥራቅ በኩል ቆመው ጸናጽል ይጸነጽሉ፣ በገና ይደረድሩና መሰንቆ ይመቱ ነበር፤ እነርሱም መለከት በሚነፉ አንድ መቶ ሃያ ካህናት ታጅበው ነበር። 13መለከት ነፊዎችና ዘማሪዎችም በአንድነት አንድ ድምፅ ሆነው ለእግዚአብሔር ውዳሴና ምስጋና አቀረቡ፤ በመለከት፣ በጸናጽልና በሌሎች መሣሪያዎች ታጅበውም ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ እግዚአብሔርን እያወደሱ፣

“እርሱ ቸር ነው፣

ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

እያሉ ዘመሩ።

ከዚያም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በደመና ተሞላ። 14የእግዚአብሔር ክብር የአምላክን ቤተ መቅደስ ሞልቶት ስለ ነበር፣ ከደመናው የተነሣ ካህናቱ አገልግሎታቸውን ማከናወን አልቻሉም።

Swedish Contemporary Bible

2 Krönikeboken 5:1-14

1När allt arbete Salomo gjorde för Herrens hus var klart, förde han in det som blivit helgat åt Herren av hans far David: silvret och guldet och alla kärlen, och lade dem i skattkammaren i Guds hus.

Salomo inviger templet

Arken förs till templet

(1 Kung 8:1-13)

2Därefter kallade Salomo samman alla äldste i Israel, alla stamhövdingar och överhuvuden för de israelitiska familjerna till Jerusalem, för att hämta Herrens ark från Sion, Davids stad. 3Alla israeliterna samlades hos kungen för högtiden i sjunde månaden.

4När alla Israels äldste hade kommit, lyfte leviterna arken. 5De bar upp arken och uppenbarelsetältet samt alla de heliga föremålen som fanns i det. De levitiska prästerna hämtade dem dit. 6Kung Salomo och hela Israels menighet som var samlad hos honom stod framför arken. De offrade får och boskap i en sådan mängd att de inte kunde räknas.

7Prästerna bar in Herrens förbundsark till dess plats i det inre rummet av templet, det allra heligaste, under kerubernas vingar, 8som var utbredda över platsen där arken stod, så att den och dess bärstänger täcktes av keruberna. 9Stängerna var så långa att deras ändar kunde ses från det heliga, framför koret, men inte utifrån. De finns där än idag.

10Ingenting annat fanns i arken förutom de två stentavlorna, som Mose lade ner i den vid Horeb, när Herren hade ingått förbundet med Israels folk efter uttåget ur Egypten.

11Prästerna lämnade helgedomen. Alla prästerna hade renat sig, oberoende av avdelning. 12Alla de levitiska sångarna, Asaf, Heman och Jedutun och deras söner och släktingar, var klädda i fint linne och stod på östra sidan om altaret med cymbaler, harpor och lyror, tillsammans med 120 präster som blåste i trumpeter, 13och tillsammans stämde trumpetblåsarna och sångarna samtidigt och samstämmigt upp i lovprisning och tacksägelse till Herren. När trumpeterna, cymbalerna och de övriga instrumenten ljöd, prisade man Herren:

”Han är god.

Hans nåd varar i evighet.”

Då fylldes huset, Herrens hus, av ett moln, 14så att prästerna inte kunde fortsätta sin tjänstgöring. Herrens härlighet uppfyllde Guds hus.