2 ዜና መዋዕል 4 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 4:1-22

የቤተ መቅደሱ ዕቃዎች መሟላት

4፥2-6፡10–5፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 7፥23-2638-51

1ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ወርዱ ሃያ ክንድ፣ ቁመቱ ዐሥር ክንድ4፥1 ርዝመቱና ወርዱ 9 ሜትር ቍመቱ 4.5 ሜትር ያህል ነው። የሆነ የናስ መሠዊያ ሠራ። 2እንዲሁም የጐኑ ስፋት ከጠርዝ እስከ ጠርዝ ዐሥር ክንድ፣ ቁመቱ አምስት4፥2 2.3 ሜትር ያህል ነው። ክንድ የሆነ ክብ በርሜል ቀልጦ ከፈሰሰ ብረት ሠራ፤ ዙሪያውም ሲለካ ሠላሳ ክንድ4፥2 13.5 ሜትር ይህል ነው። ሆነ። 3ከበርሜሉ ከንፈር በታችም በእያንዳንዱ ክንድ ርቀት ላይ ዙሪያውን ዐሥር የኮርማ ቅርጾች4፥3 0.5 ሜትር ያህል ነው። ነበሩበት፤ ኮርማዎቹም ከበርሜሉ ጋር አንድ ወጥ ሆነው በሁለት ረድፍ ቀልጠው ተሠርተው ነበር።

4በርሜሉ በዐሥራ ሁለት ኮርማዎች ላይ የቆመ ሲሆን፣ ኮርማዎቹም ሦስቱ ወደ ሰሜን፣ ሦስቱ ወደ ምዕራብ፣ ሦስቱ ወደ ደቡብ፣ ሦስቱ ወደ ምሥራቅ ይመለከቱ ነበር። በርሜሉ በእነዚህ ላይ ያረፈ ሲሆን፣ የሁሉም ጀርባ ወደ መካከል የዞረ ነበር። 5የበርሜሉ ውፍረት አንድ ስንዝር፣4፥5 8 ሳንቲ ሜትር ያህል ነው። ከንፈሩ ደግሞ የጽዋ ከንፈር ወይም የሱፍ አበባ ይመስል ነበር፤ ይህም ሦስት ሺሕ የባዶስ መስፈሪያ4፥5 66 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። የሚይዝ ነበር።

6እንዲሁም ዐሥር የመታጠቢያ ገንዳዎች አሠርቶ አምስቱን በደቡብ፣ አምስቱን ደግሞ በሰሜን በኩል አስቀመጠ፤ ገንዳዎቹ ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርቡት ነገሮች የሚታጠቡባቸው ሲሆኑ፣ በርሜሉ ግን ለካህናት መታጠቢያ የሚያገለግል ነበር።

7በተሰጠው የአሠራር መመሪያ መሠረት፣ ዐሥር የወርቅ መቅረዞች ሠርቶ ወደ ቤተ መቅደሱ በማስገባት፣ አምስቱን በስተ ደቡብ፣ አምስቱን በስተ ሰሜን አኖራቸው።

8ዐሥር ጠረጴዛ ሠርቶም ወደ ቤተ መቅደሱ በማስገባት አምስቱን በስተ ደቡብ፣ አምስቱን ደግሞ በስተ ሰሜን በኩል አኖራቸው፤ ደግሞም አንድ መቶ ጐድጓዳ የወርቅ ሳሕኖች ሠራ።

9የካህናቱንም አደባባይ ሠራ፤ እንዲሁም ታላቁን አደባባይና በሮቹን ከሠራ በኋላ በናስ ለበጣቸው። 10በርሜሉንም ከቤተ መቅደሱ በስተ ደቡብ ምሥራቅ ባለው ማእዘን በቀኝ በኩል አኖረው።

11እንዲሁም ምንቸቱን፣ መጫሪያዎችንና ጐድጓዳ ሳሕኖችን ሠራ። ኪራምም ለቤተ መቅደሱ አገልግሎት የሚውሉትን ዕቃዎች ለንጉሥ ሰሎሞን ሠርቶ ጨረሰ፤ እነዚህም፦

12ሁለቱ ዐምዶች፣

በአዕማዱ ጫፍ ላይ ያሉት ሁለት ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት በዐምዶቹ ላይ ያሉትን ሁለቱን፣

ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት የሚያስጌጡ ሁለት ዙር መርበቦች፤

13በዐምዶቹ ላይ ያሉትን ሁለቱን፣ ባለ ሳሕን ቅርጽ ጕልላት እንዲያስጌጡ ለእያንዳንዱ መርበብ ሁለት ዙር ሮማኖች ለሁለቱም ዙር መርበቦች በድምሩ አራት መቶ ሮማኖች፤

14መቆሚያዎች ከነመታጠቢያ ሳሕኖቻቸው፤

15በርሜሉና እርሱን የተሸከሙት ዐሥራ ሁለት ኮርማዎች፤

16ምንቸቶችና መጫሪያዎች፣ ሜንጦዎችና ከነዚሁም ጋር የተያያዙ ዕቃዎች።

ኪራምአቢ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ እንዲሆን ለሰሎሞን የሠራቸው ዕቃዎች በሙሉ ከተወለወለ ናስ የተሠሩ ነበሩ። 17ንጉሡም እነዚህ ዕቃዎች በዮርዳኖስ ሸለቆ፣ በሱኮትና በጽሬዳ መካከል ባለው በሸክላ ዐፈር ቦታ ቀልጠው በሸክላ ቅርጽ ተሠርተው እንዲወጡ አደረገ። 18እነዚህ ሰሎሞን ያሠራቸው ነገሮች ሁሉ እጅግ ብዙዎች ስለሆኑ የናሱ ክብደት ምን ያህል እንደ ሆነ አልታወቀም ነበር።

19እንደዚሁም ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ የሚሆኑትን ዕቃዎች ሠራ፤ እነዚህም፦

የወርቅ መሠዊያ፣

የገጸ ኅብስቱ ጠረጴዛ፣

20በተሰጠው መመሪያ መሠረት፣ በቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ለፊት እንዲነድዱ፣ ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ መቅረዞች ከነቀንዲሎቻቸው፣

21የወርቅ አበባ ቅርጽ ሥራዎች፣ ቀንዲሎችና መኰስተሪያዎች ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ ነበሩ።

22ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ የመብራት ማጥፊያዎች፣ ለመርጨት የሚያገለግሉ ጐድጓዳ ሳሕኖች፣ ጭልፋዎችና ጥናዎች፣ እንደዚሁም የቤተ መቅደሱ የወርቅ መዝጊያዎች፣ ይኸውም የቅድስተ ቅዱሳኑ የውስጠኛው መዝጊያዎችና የቤተ መቅደሱ ዋናው አዳራሽ መዝጊያዎች ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ ነበሩ።

Swedish Contemporary Bible

2 Krönikeboken 4:1-22

Hirams skickliga hantverk

(1 Kung 7:23-40)

1Han gjorde sedan ett kopparaltare som var 10 meter långt, 10 meter brett och 5 meter högt. 2Han gjorde Havet av gjutgods, runt, 5 meter i diameter och hälften så högt, med en omkrets på 15 meter. 3Runt kanten, nertill, fanns ett mönster av oxar, tio på varje halvmeter, i två rader. De var gjutna i samma stycke som själva Havet. 4Havet stod på tolv oxar. Tre av dem var vända mot norr, tre mot väster, tre mot söder och tre mot öster. Havet vilade på dem, och deras bakdelar var vända inåt. 5Havet var en handsbredd tjockt, och kanten var formad som i en skål, så att den liknade en utslagen lilja. Det rymde 90 000 liter4:5 På hebreiska 3 000 (bat). 1 bat var lika med 1 efa, mellan 20 och 40 liter. Här är beräkningen gjord utifrån 30 liter..

6Han lät också göra tio vattenfat och ställde fem på den högra sidan och fem på den vänstra. De skulle användas till tvättning, och i dem skulle man skölja det som hörde till brännoffren. Prästerna skulle tvätta sig i Havet.

7Sedan gjorde han enligt föreskrifterna tio lampställ av guld, som han placerade i templet, fem till höger och fem till vänster. 8Han gjorde tio bord och ställde fem till höger och fem till vänster. Han gjorde också 100 skålar av rent guld.

9Därefter gjorde han prästernas gård och den stora förgården med dess dörrar. Dörrarna belade han med koppar. 10Havet ställde han på högra sidan, åt sydost. 11Hiram gjorde också grytorna, skovlarna och offerskålarna.

Han fullbordade det arbete som han fått i uppdrag att göra åt kung Salomo i Guds hus:

12De två pelarna,

de skålliknande pelarhuvudena,

de två flätverken som dekorationer på pelarhuvudena,

13400 granatäpplen till de båda flätverken, två rader granatäpplen för varje flätverk, som dekorerade de skålformade pelarhuvudena,

14de tio ställen med tio fat,

15Havet och de tolv oxarna under det,

16grytorna, skovlarna och skålarna med alla tillhörande föremål.

Mäster Hiram tillverkade alla föremålen åt kung Salomo till Herrens hus i polerad koppar. 17Kungen lät gjuta dem i lerformar på Jordanslätten mellan Suckot och Saretan. 18Salomo gjorde så mycket av alla dessa ting att vikten av koppar inte kunde fastställas.

19Salomo gjorde alla föremålen i Guds hus,

det gyllene altaret och borden för skådebröden,

20lampställen med sina lampor av rent guld, som skulle tändas framför det inre rummet enligt föreskrifterna,

21blomsterdekorationerna, lamporna och tängerna av guld, ja, av renaste guld,

22vidare knivarna, skålarna, pannorna och fyrfaten av rent guld, liksom dörrarna till templet, de inre dörrarna till det allra heligaste, och till templets huvudingång. Allt detta gjordes alltså av guld.