1 ዜና መዋዕል 16 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 16:1-43

1ከዚያም የእግዚአብሔርን ታቦት አምጥተው ዳዊት በተከለለት ድንኳን ውስጥ አኖሩት፤ የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕትም16፥1 በዚህና በቍጥር 2 ላይ በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረቡ። 2ዳዊት የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ከሠዋ በኋላ፣ ሕዝቡን በእግዚአብሔር ስም ባረከ። 3ከዚያም ለእስራኤል ሁሉ ለወንዱም ለሴቱም አንዳንድ ሙልሙል ዳቦ፣ አንዳንድ ጥፍጥፍ ተምር፣ ሙዳ ሙዳ ሥጋና አንዳንድ ጥፍጥፍ ዘቢብ ሰጠ።

4በእግዚአብሔር ታቦት ፊት እንዲያገለግሉና ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ልመና፣ ምስጋናና ውዳሴ እንዲያቀርቡ ከሌዋውያን ሰዎች ሾመ፤ 5አለቃው አሳፍ ነበረ፤ ከእርሱ ቀጥሎ ዘካርያስ ሁለተኛ ሆኖ ተሾመ፤ ከዚያም ይዒኤል፣ ሰሚራሞት፣ ይሒኤል፣ መቲትያ፣ ኤልያብ፣ በናያስ፣ ዖቤድኤዶም፣ ይዒኤል ተሾሙ፤ እነርሱም በመሰንቆና በበገና ይዘምሩ ነበር፤ አሳፍ ደግሞ ጸናጽል የሚጸነጽል ሆኖ ተመደበ። 6እንዲሁም ካህናቱ በናያስና የሕዚኤል ዘወትር በእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት ፊት መለከት እንዲነፉ ተመደቡ።

የዳዊት የምስጋና መዝሙር

16፥8-22 ተጓ ምብ – መዝ 105፥1-15

16፥23-33 ተጓ ምብ – መዝ 96፥1-13

16፥34-36 ተጓ ምብ – መዝ 106፥147-48

7በዚያም ቀን ዳዊት በመጀመሪያ ለአሳፍና ለሥራ ጓደኞቹ ይህን የእግዚአብሔር ምስጋና መዝሙር ሰጠ፤

8ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ለአሕዛብ ያደረገውን ሁሉ ንገሩ፤

9ዘምሩለት፤ ውዳሴም አቅርቡለት፤

ድንቅ ሥራውን ሁሉ ንገሩ፤

10በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤

እግዚአብሔርን የሚፈልጉ ሁሉ፣ ልባቸው ሐሤት ያድርግ።

11ወደ እግዚአብሔርና ወደ ኀይሉ ተመልከቱ፤

ዘወትር ፊቱን ፈልጉ።

12ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣

ታምራቱንና የሰጠውንም ፍርድ አስታውሱ፤

13እናንተ የባሪያው የእስራኤል ዘሮች፣

እናንተ የተመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች።

14እርሱ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤

ፍርዱም በምድር ሁሉ ላይ ነው፤

15ኪዳኑን እስከ ዘላለም፣

ያዘዘውንም ቃል እስከ ሺሕ ትውልድ ያስባል።

16ከአብርሃም ጋር የገባውን ቃል ኪዳን፣

ለይስሐቅ የማለውን መሐላ።

17ይህንም ለያዕቆብ ሥርዐት አድርጎ አጸና፤

ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን አደረገ፤

18እንዲህ ሲል፣ “የምትወርሰው ርስት እንዲሆን፣

የከነዓንን ምድር ለአንተ እሰጣለሁ።”

19ቍጥራቸው ገና ጥቂት ሳለ፣

በርግጥ ጥቂትና መጻተኞች ሳሉ፣

20ከአንዱ ሕዝብ ወደ ሌላው ሕዝብ፣

ከአንዱም መንግሥት ወደ ሌላው መንግሥት ተንከራተቱ።

21ማንም እንዲጨቍናቸው አልፈቀደም፤

ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ፤

22እንዲህ ሲል፤ “የቀባኋቸውን አትንኩ፤

በነቢያቴ ላይ ክፉ አታድርጉ።”

23ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ማዳኑንም ዕለት ዕለት ዐውጁ።

24ክብሩን ለአሕዛብ ተናገሩ፤

ድንቅ ሥራዎቹን ለሕዝቦች ሁሉ ንገሩ።

25እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ ምስጋናውም ብዙ ነው፤

ከአማልክትም ሁሉ በላይ ሊፈራ የሚገባው ነው።

26የአሕዛብ ሁሉ አማልክት ጣዖታት ናቸው፤

እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።

27በፊቱ ክብርና ሞገስ አለ፤

ብርታትና ደስታም በማደሪያው ስፍራ።

28የአሕዛብ ወገኖች ለእግዚአብሔር ስጡ፤

ክብርና ኀይልን ለእግዚአብሔር አምጡ።

29ለስሙ የሚገባውን ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤

መባ ይዛችሁ በፊቱ ቅረቡ፤

በቅድስናውም ክብር ለእግዚአብሔር16፥29 ወይም፣ ከክብሩ ጋር ለእግዚአብሔር ስገዱ።

30ምድር ሁሉ በፊቱ ትንቀጥቀጥ፤

ዓለም በጽኑ ተመሥርታለች፤ አትናወጥምም።

31ሰማያት ደስ ይበላቸው፤ ምድር ሐሤት ታድርግ፤

በአሕዛብም መካከል፤ “እግዚአብሔር ነገሠ!” ይበሉ።

32ባሕርና በውስጧ ያለው ሁሉ ይናወጥ፤

ሜዳዎችና በእርሷ ላይ ያሉ ሁሉ ሐሤት ያድርጉ።

33ያን ጊዜ የዱር ዛፎች በእግዚአብሔር ፊት ደስ ይላቸዋል፤

በደስታ ይዘምራሉ፤

በምድረ በዳ ላይ ሊፈርድ ይመጣልና።

34ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

35“አዳኛችን እግዚአብሔር ሆይ ታደገን፤

ለቅዱስ ስምህ ምስጋና እንድናቀርብ፣ በምስጋናህም እንድንከብር ሰብስበን፤

ከአሕዛብም መካከል ታደገን”

ብላችሁ ጩኹ።

36ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።

ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ፣ “አሜን፤ እግዚአብሔር ይመስገን” አሉ።

37ዳዊትም ለእያንዳንዱ ቀን በተመደበው መሠረት፣ ዘወትር እንዲያገለግሉ አሳፍንና የሥራ ባልደረቦቹን በዚያው በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ታቦት ፊት ተዋቸው። 38እንዲሁም ዖቤድኤዶምና ስድሳ ስምንቱ የሥራ ባልደረቦቹ አብረዋቸው እንዲያገለግሉ በዚያው ተዋቸው። የኤዶታም ልጅ ዖቤድኤዶምና ሖሳ የቅጥሩ በር ጠባቂዎች ሆኑ።

39ዳዊት ካህኑን ሳዶቅንና የሥራ ባልደረቦቹን ካህናት በገባዖን ከፍተኛ ቦታ ላይ በሚገኘው በእግዚአብሔር ድንኳን ተዋቸው፤ 40የተዋቸውም ለእስራኤል በተሰጠው ትእዛዝ መሠረት፣ በእግዚአብሔር ሕግ እንደ ተጻፈው ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቀርበውን የሚቃጠል መሥዋዕት ጧትና ማታ በየጊዜው እንዲያቀርቡ ነው። 41እንዲሁም “ፍቅሩ ለዘላለም ነውና” እያሉ ለእግዚአብሔር ምስጋና እንዲያቀርቡ ኤማንና ኤዶታም እንዲሁም ተመርጠውና ስማቸው ተመዝግቦ የተመደቡ ሌሎችም አብረዋቸው ነበሩ። 42ድምፀ መለከቱንና ጸናጽሉን ለማሰማት፣ ደግሞም መንፈሳዊ መዝሙር ሲዘመር ለሚጠቀሙባቸው ሌሎች መሣሪያዎች ኀላፊዎቹ ኤማንና ኤዶታም ነበሩ፤ የኤዶታምም ልጆች በሩን እንዲጠብቁ ተመድበው ነበር።

43ከዚያም ሕዝቡ ተነሣ፤ እያንዳንዱም ወደየቤቱ ሄደ። ዳዊትም ቤተ ሰቡን ለመባረክ ወደ ቤቱ ተመለሰ።

Swedish Contemporary Bible

1 Krönikeboken 16:1-43

David prisar Herren

1Guds ark fördes in i tältet som David hade rest, och de bar fram brännoffer och gemenskapsoffer till Gud.

2När David avslutat brännoffren, välsignade han folket i Herrens namn, 3och sedan gav han var och en av israeliterna, både män och kvinnor, en kaka bröd, en dadelkaka och en druvkaka.

4Han utsåg några leviter att tjänstgöra framför Herrens ark; de skulle åkalla, prisa och lova Herren, Israels Gud.

5Asaf blev ledare, Sakarja den andre, och sedan Jeiel16:5 Enligt 15:18 Jaasiel., Shemiramot, Jechiel, Mattitja, Eliav, Benaja, Oved-Edom och Jeiel. De spelade lyra och harpa, Asaf slog på cymbalerna 6och prästerna Benaja och Jachasiel blåste ständigt på sina trumpeter framför Guds förbundsark.

David lovprisar Herren

(Ps 105:1-15; 96:1-13; 106:1; 106:47-48)

7Den dagen uppdrog David för första gången Asaf och hans bröder att lovsjunga Herren:

8”Prisa Herren, åkalla honom!

Gör hans verk kända för alla folk!

9Sjung och spela till hans ära,

berätta om alla hans under!

10Lovprisa hans heliga namn,

låt dem som söker Herren få en innerlig glädje!

11Vänd er till Herren och hans kraft,

sök honom ständigt!

12Tänk på de mäktiga gärningar han har gjort,

hans under och den dom som han uttalat,

13ni som är ättlingar till hans tjänare Israel,

till Jakob16:13 Jakob, Israel, se 1 Mos 32:28. Upprepningen är en ofta förekommande poetisk form, parallellism., hans utvalde.

14Han är Herren, vår Gud.

Över hela jorden sträcker sig hans domar.

15Han minns för evigt sitt förbund16:15 Enligt den masoretiska texten: Kom för alltid ihåg hans förbund. Jfr även Ps 105:8.,

sina befallningar för tusen generationer,

16det förbund som han slöt med Abraham,

och sin ed till Isak.

17Han bekräftade det till Jakob som en stadga,

till Israel som ett evigt förbund.

18Han sa: ’Jag ska ge dig Kanaans land

till arv och egendom.’

19Fastän de16:19 Enligt Septuaginta; se även Ps 105:12. Enligt den masoretiska texten ni. var få till antalet,

en liten skara främlingar,

20och vandrade från folk till folk,

från rike till rike,

21lät han ingen förtrycka dem,

och han straffade kungar för deras skull.

22’Rör inte mina smorda,

skada inte mina profeter!’

23Sjung till Herrens ära, hela jorden!

Ropa ut hans räddning varje dag!

24Förkunna hans härlighet bland folken,

berätta för alla människor om hans under!

25För Herren är stor och högt prisad,

värd att frukta, mer än alla gudar.

26Folkens alla gudar är avgudar,

men Herren har gjort himlen.

27Majestät och prakt omger honom,

kraft och glädje finns i hans boning.

28Ge Herren ära, alla folkslag,

erkänn hans majestät och kraft!

29Ge Herrens höga namn ära,

kom med era offer till honom,

tillbe Herren i helig skrud!16:29 I helig skrud kan syfta på Herrens härlighet, eller på den dräkt prästerna använde.

30Darra inför honom, hela jorden!

Världen står fast, den kan inte rubbas.

31Låt himlen vara glad och jorden jubla!

Låt dem förkunna bland folken att Herren regerar!

32Låt havet brusa och allt som finns i det!

Låt fälten glädjas och allt som växer på dem!

33Skogens alla träd ska susa av lovsånger,

ja, de ska jubla inför Herren,

ty han kommer för att döma jorden.

34Prisa Herren, för han är god.

Hans nåd varar i evighet.

35Säg: Rädda oss, Gud, du vår räddare!

Samla oss igen och befria oss från dessa folk,

så att vi får prisa ditt heliga namn

och tacka och lova dig.

36Lovad vare Herren, Israels Gud,

från evighet till evighet!”

Och allt folket sa: ”Amen!” och prisade Herren.

37David lämnade Asaf och hans bröder i ständig tjänst inför Herrens förbundsark, enligt föreskrifterna för varje dag, 38liksom Oved-Edom och hans 68 medhjälpare. Oved-Edom, Jedutuns son, var dörrvaktare tillsammans med Hosa.

39Prästen Sadok och hans bröder, prästerna, lämnade David kvar vid Herrens boning på offerhöjden i Givon, 40för att de alltid skulle bära fram brännoffer inför Herren på brännofferaltaret varje morgon och kväll, i enlighet med den lag som Herren hade gett Israel. 41Med dem var också Heman, Jedutun och andra utvalda, som var utsedda att prisa Herren, för hans nåd varar för evigt. 42Heman och Jedutun var ansvariga för musiken med trumpet och cymbal och andra instrument till gudstjänstssången. Jedutuns söner var dörrvaktare.

43Sedan återvände folket hem, var och en till sitt, och David återvände för att välsigna sin familj.