1 ነገሥት 22 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 22:1-53

ሚክያስ በአክዓብ ላይ ትንቢት ተናገረ

22፥1-28 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥1-27

1በሶርያና በእስራኤል መካከል ለሦስት ዓመት ጦርነት አልነበረም። 2በሦስተኛው ዓመት ግን የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ የእስራኤልን ንጉሥ ለመጐብኘት ወረደ። 3የእስራኤልም ንጉሥ ሹማምቱን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት የእኛ ሆና ሳለች፣ ከሶርያው ንጉሥ እጅ ለመመለስ ምንም እንዳላደረግን አታውቁምን?” አላቸው።

4ስለዚህ ኢዮሣፍጥን፣ “በገለዓድ የምትገኘው ሬማት ላይ ለመዝመት አብረኸኝ ለመሄድ ትፈቅዳለህን?” ሲል ጠየቀው።

ኢዮሣፍጥም፣ “እኔ ያው እንደ አንተው ነኝ፤ ሕዝቤ እንደ ሕዝብህ፣ ፈረሶቼም እንደ ፈረሶችህ ናቸው” አለ። 5ኢዮሣፍጥም የእስራኤልን ንጉሥ፣ “በመጀመሪያ ግን የእግዚአብሔርን ሐሳብ ጠይቅ” አለው።

6ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ አራት መቶ ነቢያትን በአንድነት ሰብስቦ፣ “በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ልዝመት ወይስ ልተው?” ሲል ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዝመትባት” አሉት።

7ኢዮሣፍጥ ግን፣ “የምንጠይቀው የእግዚአብሔር ነቢይ እዚህ የለምን?” አለ።

8የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “መኖሩንማ በእርሱ አማካይነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምንጠይቀው አንድ ሰው አሁንም አለ፤ ነገር ግን ምንጊዜም ቢሆን ስለ እኔ ክፉ እንጂ አንዳችም መልካም ትንቢት ተናግሮ ስለማያውቅ እጠላዋለሁ፤ ይህም ሰው የይምላ ልጅ ሚክያስ ነው” አለ። ኢዮሣፍጥም፣ “ንጉሡ እንዲህ ማለት አይገባውም” ሲል መለሰ።

9ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ከሹማምቱ አንዱን ጠርቶ፣ “በል የይምላን ልጅ ሚክያስን በፍጥነት አምጣው” አለው።

10የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ አልባሰ መንግሥታቸውን ለብሰው፣ በሰማርያ ቅጥር በር አጠገብ ባለው አውድማ ላይ በየዙፋናቸው ተቀምጠው ሳለ፣ ነቢያቱ ሁሉ በፊታቸው ትንቢት ይናገሩ ነበር።

11በዚህ ጊዜ ሴዴቅያስ የተባለው የክንዓና ልጅ የብረት ቀንዶች አበጅቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሶርያውያን እስኪጠፉ ድረስ የምትወጋቸው በእነዚህ ነው’ ” አለው።

12የቀሩትም ነቢያት ሁሉ፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና በገለዓድ የምትገኘውን ሬማትን ወግተህ ድል አድርግ” በማለት በአንድ ቃል ትንቢት ይናገሩ ነበር።

13ከዚያም ሚክያስን ሊጠራ የሄደው መልእክተኛ፣ “እነሆ፤ ሌሎቹ ነቢያት ንጉሡ ድል እንደሚያደርግ በአንድ ቃል ትንቢት እየተናገሩለት ነውና የአንተም ቃል ከእነርሱ ጋር አንድ እንዲሆን እባክህ መልካም ነገር ተናገር” አለው።

14ሚክያስ ግን፣ “ሕያው እግዚአብሔርን! ለእርሱ የምነግረው እግዚአብሔር የነገረኝን ብቻ ነው” አለ።

15እዚያም እንደ ደረሰ ንጉሡ፣ “ሚክያስ ሆይ፤ በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ እንዝመትባት ወይስ እንተው?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “እግዚአብሔር በንጉሡ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ዘምተህ ድል አድርጋት” ብሎ መለሰለት።

16ንጉሡም፣ “ከእውነት በቀር በእግዚአብሔር ስም አንዳች ነገር እንዳትነግረኝ የማምልህ ስንት ጊዜ ነው?” አለው።

17ከዚያም ሚክያስ እንዲህ ሲል መለሰ፣ “እስራኤል ሁሉ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በየተራራው ላይ ተበትነው አየሁ፣ እግዚአብሔርም፣ ‘ይህ ሕዝብ ጌታ የለውም፤ እያንዳንዱ በሰላም ወደየቤቱ ይሂድ’ አለ።”

18የእስራኤልም ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “ስለ እኔ ክፉ ብቻ እንጂ ከቶ መልካም ትንቢት አይናገርም አላልሁህምን?” አለው።

19ከዚያም ሚክያስ እንዲህ አለ፤ “እንግዲህ የእግዚአብሔር ቃል የሚለውን ስማ፤ እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ፣ የሰማይ ሰራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ፤ 20እግዚአብሔርም፣ ‘በገለዓድ በምትገኘው ሬማት ላይ ዘምቶ እዚያው እንዲሞት፣ አክዓብን ማን ያስተው?’ አለ።

“ታዲያ አንዱ ይህን፣ ሌላውም ያን አለ፤ 21በመጨረሻም፣ አንድ መንፈስ ወጣ፤ ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ፣ ‘እኔ አስተዋለሁ’ አለ።

22እግዚአብሔርም፣ ‘እንዴት አድርገህ?’ ሲል ጠየቀው።

“እርሱም፣ ‘እኔ እወጣለሁ፤ በገዛ ነቢያቱም አፍ ሁሉ የሐሰት መንፈስ እሆናለሁ’ አለ።

እግዚአብሔርም፣ ‘በል እንግዲያው ውጣና አስተው፤ ይሳካልሃል’ አለው።

23“ስለዚህ እነሆ እግዚአብሔር በእነዚህ ሁሉ ነቢያትህ አፍ የሐሰት መንፈስ አኖረ፤ በአንተም ላይ መዓቱን እንደሚያመጣብህ ተናገረ።”

24ከዚያም የክንዓና ልጅ ሴዴቅያስ ወጥቶ ሚክያስን በጥፊ መታውና፣ “ለመሆኑ የእግዚአብሔር መንፈስ ከእኔ በየት በኩል ዐልፎ ነው አንተን መጥቶ ያናገረህ?” ሲል ጠየቀው።

25ሚክያስም፤ “ይህንማ ለመደበቅ ወደ አንዲት እልፍኝ በሄድህ ዕለት ታውቀዋለህ” አለው።

26ከዚያም የእስራኤል ንጉሥ እንዲህ ሲል አዘዘ፤ “በሉ ሚክያስን ይዛችሁ ወደ ከተማዪቱ ገዥ ወደ አሞንና ወደ ንጉሡ ልጅ ወደ ኢዮአስ መልሱት፤ 27ከዚያም፣ ‘ንጉሡ፣ በደኅና እስክመለስ ድረስ፣ ይህን ሰው በእስር ቤት አቈዩት፤ ከደረቅ እንጀራና ከውሃ በስተቀር ሌላ እንዳትሰጡት’ ብሏል በሉት” አለ።

28ሚክያስም፣ “አንተ በደኅና ከተመለስህ እግዚአብሔር በእኔ አልተናገረማ!” አለ፤ ከዚያም በመቀጠል፣ “በዚህ ያለኸው ሕዝብ ሁሉ ይህን ቃሌን ልብ ብለህ ያዘው፤” አለ።

አክዓብ በገለዓድ በምትገኘው በሬማት ተገደለ

22፥29-36 ተጓ ምብ – 2ዜና 18፥28-34

29ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በገለዓድ ወደምትገኘው ሬማት ወጡ። 30የእስራኤል ንጉሥ ኢዮሣፍጥን፣ “እንዳልታወቅ እኔ ልብስ ለውጬና ሌላ ሰው መስዬ እገባለሁ፤ አንተ ግን ልብሰ መንግሥትህን ልበስ” አለው። ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ራሱን ደብቆ ወደ ጦርነቱ ገባ።

31በዚህ ጊዜ የሶርያ ንጉሥ ሠላሳ ሁለቱን የሠረገላ አዛዦች፣ “ከራሱ ከእስራኤል ንጉሥ በቀር ትንሽም ይሁን ትልቅ ከማንም ጋር እንዳትገጥሙ” ሲል አዝዟቸው ነበር፤ 32የሠረገላ አዛዦቹ ኢዮሣፍጥን ሲያዩት፣ “ያለ ጥርጥር ይህ የእስራኤል ንጉሥ ነው” አሉ፤ ስለዚህ አደጋ ሊጥሉበት ከበቡት፤ ኢዮሣፍጥ ሲጮህ ግን 33የሠረገላ አዛዦቹ እርሱ የእስራኤል ንጉሥ አለመሆኑን ዐውቀው መከታተሉን ተዉት።

34ነገር ግን አንዱ ቀስቱን ሳያልም እንዲሁ ሲያስፈነጥር በጦር ልብሱ መጋጠሚያ ላይ የእስራኤልን ንጉሥ ወጋው፤ ንጉሡም ሠረገላ ነጂውን፣ “ቈስያለሁና ወደ ኋላ አዙረህ ከጦሩ ሜዳ አውጣኝ” አለው። 35ጦርነቱም ቀኑን ሙሉ ተፋፍሞ ዋለ፤ በዚህ ጊዜም ንጉሡ በሶርያውያን ፊት ለፊት ሠረገላው ላይ ቀና ብሎ እንደ ተደገፈ ነበር፤ የቍስሉ ደም በሠረገላው ወለል ላይ ይወርድ ነበር፤ በዚያኑ ዕለት ማታም ንጉሡ ሞተ። 36ፀሓይ ስትጠልቅም በሰራዊቱ መካከል፣ “እያንዳንዱ ሰው ወደ ቤቱ፣ እያንዳንዱም ወደ ሀገሩ ይሂድ!” የሚል ጩኸት አስተጋባ።

37ንጉሡ ስለ ሞተም ወደ ሰማርያ አምጥተውት እዚያው ተቀበረ። 38ሠረገላውንም አመንዝሮች በታጠቡበት በሰማርያ22፥38 ወይም፣ የጦር መሣሪያ በሚታጠብበት በሰማርያ ተብሎ መተርጐም ይችላል ኵሬ ዐጠቡት፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ቃል ደሙን ውሾች ላሱት።

39ሌላው በአክዓብ ዘመነ መንግሥት የተፈጸመውና ያደረገው ሁሉ፣ ቤተ መንግሥቱን መሥራቱና በዝኆን ጥርስ መለበጡ እንዲሁም የሠራቸው የምሽግ ከተሞች በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 40አክዓብም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ አካዝያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ

22፥41-50 ተጓ ምብ – 2ዜና 20፥31–21፥1

41የእስራኤል ንጉሥ አክዓብ በነገሠ በአራተኛው ዓመት የአሳ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ነገሠ። 42ኢዮሣፍጥ ሲነግሥ ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ነበር፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱ ዓዙባ ትባላለች፤ እርሷም የሺልሒ ልጅ ነበረች። 43በአካሄዱም ሁሉ የአባቱን የአሳን መንገድ ተከተለ፤ ከዚያች ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን አደረገ፤ ይሁን እንጂ በየኰረብታው ላይ ያሉትን የማምለኪያ ቦታዎች አላጠፋም፤ ሕዝቡም በዚያ መሥዋዕት ይሠዋ፣ ዕጣንም ያጥን ነበር። 44እንዲሁም ኢዮሣፍጥ ከእስራኤል ንጉሥ ጋር በሰላም ኖረ።

45ሌላውም ኢዮሣፍጥ በዘመነ መንግሥቱ የፈጸመው፣ ያከናወነውና ያደረገው ጦርነት ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ የተጻፈ አይደለምን? 46ከአባቱ ከአሳ ዘመን በኋላ እንኳ ተርፈው በጣዖት ማምለኪያ ቦታዎች የነበሩትን የወንደቃ ቅሬታዎች ከምድሪቱ አስወገደ። 47በዚያን ጊዜ ኤዶም ንጉሥ አልነበራትም፤ የሚገዛት እንደራሴ ነበር።

48ኢዮሣፍጥ ወርቅ ለማምጣት ወደ ኦፊር የሚሄዱ የንግድ መርከቦች22፥48 ዕብራይስጡ የተርሴስ መርከቦች ይላል አሠርቶ ነበር፤ ይሁን እንጂ በዔጽዮንጋብር ስለ ተሰበሩ ከቶ ወደዚያ መሄድ አልቻሉም ነበር። 49በዚያን ጊዜም የአክዓብ ልጅ አካዝያስ ኢዮሣፍጥን “ሰዎቼ ከሰዎችህ ጋር በመርከብ ይሂዱ” ሲል ጠይቆት ነበር፤ ኢዮሣፍጥ ግን እሺ አላለውም።

50ኢዮሣፍጥ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ እነርሱ በተቀበሩበት በአባቱ በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ ኢዮራምም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

የእስራኤል ንጉሥ አካዝያስ

51የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በነገሠ በዐሥራ ሰባተኛው ዓመት የአክዓብ ልጅ አካዝያስ የእስራኤል ንጉሥ ሆኖ በሰማርያ ነገሠ፤ እስራኤልንም ሁለት ዓመት ገዛ። 52እርሱም የአባቱንና የእናቱን፣ እንዲሁም እስራኤልን ያሳተውን የናባጥን ልጅ የኢዮርብዓምን መንገድ በመከተሉ፣ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ክፉ ሥራ ሠራ። 53አባቱ እንዳደረገው ሁሉ፣ እርሱም በኣልን አመለከ፤ ሰገደለትም። በዚህም የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ለቍጣ እንዲነሣሣ አደረገ።

Thai New Contemporary Bible

1พงศ์กษัตริย์ 22:1-53

มีคายาห์พยากรณ์เกี่ยวกับอาหับ

(2พศด.18:1-27)

1สงครามระหว่างอารัมกับอิสราเอลว่างเว้นไปสามปี 2แต่ในปีที่สามกษัตริย์เยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์เสด็จมาเยือนกษัตริย์อิสราเอล 3กษัตริย์อิสราเอลตรัสกับข้าราชบริพารว่า “พวกเจ้าก็รู้ไม่ใช่หรือว่าราโมทกิเลอาดเป็นของเรา แต่เราก็ไม่ทำอะไรเพื่อชิงคืนจากกษัตริย์อารัมเลย?”

4อาหับจึงตรัสถามเยโฮชาฟัทว่า “ท่านจะช่วยข้าพเจ้ารบกับราโมทกิเลอาดไหม?”

เยโฮชาฟัทตรัสตอบกษัตริย์อิสราเอลว่า “เราสองคนเป็นพวกเดียวกัน คนของข้าพเจ้าก็เหมือนเป็นคนของท่าน ม้าของข้าพเจ้าก็เหมือนเป็นม้าของท่าน” 5แต่เยโฮชาฟัทตรัสกับกษัตริย์อิสราเอลอีกว่า “เราควรทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้าก่อน”

6กษัตริย์อิสราเอลจึงทรงเรียกผู้เผยพระวจนะราวสี่ร้อยคนมาเข้าเฝ้า และตรัสถามว่า “เราควรจะไปรบกับราโมทกิเลอาด หรือเราควรจะยับยั้งไว้?”

เขาเหล่านั้นทูลว่า “ไปเลยพระเจ้าข้า เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงมอบดินแดนนั้นไว้ในพระหัตถ์ของฝ่าพระบาท”

7แต่เยโฮชาฟัทตรัสถามว่า “ที่นี่ไม่มีผู้เผยพระวจนะขององค์พระผู้เป็นเจ้าให้ถามเลยหรือ?”

8กษัตริย์อิสราเอลตรัสตอบเยโฮชาฟัทว่า “ยังมีอยู่คนหนึ่งซึ่งเราจะทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้าผ่านทางเขาได้ แต่ข้าพเจ้าเกลียดเขา เพราะเขาไม่เคยพยากรณ์เรื่องดีๆ เกี่ยวกับข้าพเจ้าเลย มีแต่เรื่องร้ายๆ เขาคือมีคายาห์บุตรอิมลาห์”

เยโฮชาฟัทตรัสว่า “พระองค์อย่าตรัสเช่นนั้นเลย”

9ดังนั้นกษัตริย์อิสราเอลจึงทรงเรียกมหาดเล็กคนหนึ่งมาและสั่งว่า “จงนำตัวมีคายาห์บุตรอิมลาห์มาเดี๋ยวนี้”

10ทั้งกษัตริย์อิสราเอลและกษัตริย์เยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์ทรงฉลองพระองค์เต็มยศประทับอยู่บนพระที่นั่งในลานนวดข้าวใกล้ประตูเมืองสะมาเรีย ในขณะที่กลุ่มผู้เผยพระวจนะก็กล่าวพยากรณ์ไปต่อหน้า 11ฝ่ายเศเดคียาห์บุตรเคนาอะนาห์ได้ทำเขาเหล็กขึ้นมาและประกาศว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘เจ้าจะขวิดพวกอารัมด้วยเขาเหล็กนี้จนพวกเขาย่อยยับไป’ ”

12ผู้เผยพระวจนะคนอื่นๆ ทั้งหมดก็กำลังพยากรณ์อย่างเดียวกันว่า “จงบุกเข้าโจมตีราโมทกิเลอาดและมีชัยชนะเถิด เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงมอบเมืองนั้นไว้ในพระหัตถ์ของฝ่าพระบาท”

13คนที่ไปตามตัวมีคายาห์ได้กล่าวกับเขาว่า “ดูเถิด ผู้เผยพระวจนะคนอื่นๆ ล้วนแต่ทำนายเป็นเสียงเดียวกันว่ากษัตริย์จะชนะ ขอให้ท่านกล่าวไปในทางที่ดีเช่นเดียวกับพวกเขา”

14แต่มีคายาห์กล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด ข้าพเจ้าจะพูดแต่สิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสฉันนั้น”

15เมื่อเขามาถึง กษัตริย์ตรัสถามว่า “มีคายาห์เอ๋ย เราควรจะไปรบกับราโมทกิเลอาดหรือเราควรจะยับยั้งไว้?”

มีคายาห์ทูลว่า “จงบุกเข้าโจมตีราโมทกิเลอาดและมีชัยชนะเถิด เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงมอบเมืองนั้นไว้ในพระหัตถ์ของฝ่าพระบาท”

16กษัตริย์ตรัสว่า “เราจะต้องให้เจ้าสาบานกี่ครั้งกี่หนว่าจะบอกแต่ความจริงแก่เราในพระนามพระยาห์เวห์?”

17มีคายาห์จึงทูลตอบว่า “ข้าพเจ้าเห็นอิสราเอลทั้งปวงกระจัดกระจายไปตามภูเขาต่างๆ เหมือนแกะที่ไม่มีคนเลี้ยง และองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘คนเหล่านี้ไม่มีนาย ให้ทุกคนกลับบ้านโดยสวัสดิภาพเถิด’ ”

18กษัตริย์อิสราเอลตรัสกับเยโฮชาฟัทว่า “ข้าพเจ้าบอกท่านแล้วไม่ใช่หรือว่าเขาไม่เคยพยากรณ์เรื่องดีๆ เกี่ยวกับข้าพเจ้าเลย มีแต่เรื่องร้ายทั้งนั้น?”

19มีคายาห์กล่าวต่อไปว่า “ฉะนั้นจงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าข้าพเจ้าเห็นองค์พระผู้เป็นเจ้าประทับบนพระที่นั่งของพระองค์ ทูตสวรรค์ทั้งปวงยืนเฝ้าอยู่รอบพระองค์ทั้งซ้ายและขวา 20แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘ใครจะหลอกล่ออาหับให้ไปโจมตีราโมทกิเลอาดและตายที่นั่น?’

“มีผู้ทูลเสนอต่างๆ นานา 21ในที่สุดมีวิญญาณดวงหนึ่งก้าวออกมายืนต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าและกราบทูลว่า ‘ข้าพระองค์จะหลอกล่อเขา’

22องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสถามว่า ‘ทำอย่างไร?’

“วิญญาณนั้นทูลว่า ‘ข้าพระองค์จะไปเป็นวิญญาณมุสาในปากของผู้เผยพระวจนะทุกคนของอาหับ’

“พระองค์จึงตรัสว่า ‘เจ้าจะหลอกล่อเขาสำเร็จ ไปทำตามนั้นเถิด’

23“ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงใส่วิญญาณมุสาในปากผู้เผยพระวจนะเหล่านี้ของฝ่าพระบาท องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมีประกาศิตให้ฝ่าพระบาทถึงแก่หายนะแล้ว”

24แล้วเศเดคียาห์บุตรเคนาอะนาห์จึงเข้ามาตบหน้ามีคายาห์และถามว่า “พระวิญญาณจาก22:24 หรือพระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าออกจากข้าไปพูดกับเจ้าได้อย่างไร?”

25มีคายาห์ตอบว่า “ท่านจะรู้คำตอบในวันที่ท่านไปหลบซ่อนตัวอยู่ในห้องชั้นใน”

26กษัตริย์อิสราเอลจึงตรัสสั่งว่า “จงคุมตัวมีคายาห์กลับไปหาอาโมนผู้ว่าการของเมืองนี้และโยอาชบุตรของเรา 27บอกสองคนนั้นว่า ‘กษัตริย์ตรัสดังนี้ว่า จงขังชายผู้นี้ไว้ในคุก ให้แต่ขนมปังกับน้ำประทังชีวิตจนกว่าเราจะกลับมาอย่างปลอดภัย’ ”

28มีคายาห์ประกาศว่า “หากฝ่าพระบาทกลับมาอย่างปลอดภัย ก็แสดงว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ตรัสผ่านทางข้าพเจ้า” แล้วเขากล่าวอีกว่า “ทุกคนจงจำคำพูดของข้าพเจ้าไว้!”

อาหับถูกสังหารที่ราโมทกิเลอาด

(2พศด.18:28-34)

29ดังนั้นกษัตริย์อาหับแห่งอิสราเอลและกษัตริย์เยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์จึงเสด็จไปยังราโมทกิเลอาด 30กษัตริย์อิสราเอลตรัสกับเยโฮชาฟัทว่า “ข้าพเจ้าจะปลอมตัวไปออกรบ ส่วนท่านแต่งเครื่องทรงกษัตริย์ของท่านเถิด” แล้วกษัตริย์อิสราเอลก็ทรงปลอมพระองค์และเสด็จออกรบ

31ฝ่ายกษัตริย์อารัมได้ทรงบัญชาผู้บัญชาการรถรบ 32 คนของพระองค์ว่า “อย่าต่อสู้กับใคร ไม่ว่าผู้ใหญ่หรือผู้น้อย แต่จงต่อสู้กับกษัตริย์อิสราเอลเพียงองค์เดียวเท่านั้น” 32เมื่อผู้บัญชาการรถรบเหล่านั้นเห็นเยโฮชาฟัท พวกเขาก็คิดว่า “นี่เป็นกษัตริย์อิสราเอลแน่ๆ” จึงหันมาโจมตี แต่เมื่อเยโฮชาฟัทร้องตะโกนออกมา 33ผู้บัญชาการรถรบเหล่านั้นเห็นว่าไม่ใช่กษัตริย์อิสราเอล ก็เลิกไล่ล่าพระองค์

34แต่มีคนหนึ่งยิงธนูสุ่มไปถูกกษัตริย์อิสราเอลตรงช่วงรอยต่อของเสื้อเกราะ พระองค์จึงตรัสกับพลขับว่า “จงกลับรถพาเราออกจากสนามรบ เราบาดเจ็บแล้ว” 35สงครามดำเนินไปอย่างดุเดือดตลอดทั้งวัน กษัตริย์ทรงประคองตัวไว้ในรถม้าศึกให้ประจันหน้ากับชาวอารัม พระโลหิตจากบาดแผลไหลนองพื้นรถ ครั้นตกเย็นก็สิ้นพระชนม์ 36ขณะที่ดวงอาทิตย์กำลังลับไป มีเสียงร้องบอกไปทั่วกองทัพว่า “ทุกคนกลับบ้านเมืองของตนเถิด!”

37ดังนั้นกษัตริย์อาหับก็สิ้นพระชนม์ และพระศพถูกนำกลับมาฝังไว้ที่สะมาเรีย 38เมื่อพวกเขาล้างรถม้าศึกที่สระในสะมาเรีย (ซึ่งพวกหญิงโสเภณีมาอาบน้ำ) สุนัขก็มาเลียพระโลหิตของกษัตริย์ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงลั่นวาจาไว้แล้ว

39เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลของอาหับ พระราชกิจทุกอย่าง พระราชวังที่ทรงสร้างและตกแต่งด้วยงาช้าง และเมืองต่างๆ ที่ทรงเสริมปราการ มีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งอิสราเอลไม่ใช่หรือ? 40อาหับทรงล่วงลับไปอยู่กับบรรพบุรุษและอาหัสยาห์โอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน

กษัตริย์เยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์

(2พศด.20:31—21:1)

41เยโฮชาฟัทโอรสของอาสาขึ้นครองราชย์ในยูดาห์ ตรงกับปีที่สี่ของรัชกาลกษัตริย์อาหับแห่งอิสราเอล 42เยโฮชาฟัทมีพระชนมายุ 35 พรรษาเมื่อขึ้นครองราชย์ และทรงปกครองในกรุงเยรูซาเล็มอยู่ 25 ปี ราชมารดาคืออาซูบาห์ธิดาของชิลหิ 43เยโฮชาฟัททรงดำเนินตามแบบอย่างของอาสาราชบิดาทุกประการโดยไม่หันเห ทรงทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้า แต่ไม่ได้ทรงทำลายสถานบูชาบนที่สูงทั้งหลาย ประชากรจึงยังคงถวายเครื่องบูชาและเผาเครื่องหอมที่นั่น 44เยโฮชาฟัทได้ทรงมีสัมพันธไมตรีกับกษัตริย์อิสราเอลด้วย

45เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลเยโฮชาฟัท พระราชกิจและวีรกรรมในการสงครามมีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งยูดาห์ไม่ใช่หรือ? 46เยโฮชาฟัททรงกำจัดโสเภณีชายในเทวสถานซึ่งยังหลงเหลืออยู่จากสมัยของอาสาราชบิดาให้หมดไปจากแผ่นดิน 47ในสมัยนั้นเอโดมไม่มีกษัตริย์ปกครอง มีแต่ผู้สำเร็จราชการ

48เยโฮชาฟัททรงสร้างกองเรือพาณิชย์22:48 หรือกองเรือทารชิช เพื่อไปขนทองคำจากเมืองโอฟีร์ แต่เรือเหล่านั้นไม่ได้ไป เพราะอับปางลงที่เอซีโอนเกเบอร์ 49ครั้งนั้นอาหัสยาห์โอรสของอาหับกล่าวกับเยโฮชาฟัทว่า “ขอให้คนของเราแล่นเรือไปกับคนของท่าน” แต่เยโฮชาฟัททรงปฏิเสธ

50แล้วเยโฮชาฟัททรงล่วงลับไปอยู่กับบรรพบุรุษและถูกฝังไว้ด้วยกันในเมืองดาวิด และเยโฮรัมโอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน

กษัตริย์อาหัสยาห์แห่งอิสราเอล

51อาหัสยาห์โอรสของอาหับขึ้นครองราชย์เป็นกษัตริย์อิสราเอลในสะมาเรียตรงกับปีที่สิบเจ็ดของรัชกาลกษัตริย์เยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์ ทรงปกครองอิสราเอลอยู่สองปี 52อาหัสยาห์ทรงทำสิ่งที่ชั่วในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้า เพราะทรงดำเนินตามวิถีทางของราชบิดากับราชมารดา และตามวิถีทางของเยโรโบอัมบุตรเนบัทผู้ได้ชักนำอิสราเอลให้ทำบาป 53พระองค์ทรงปรนนิบัตินมัสการพระบาอัล และยั่วยุพระพิโรธของพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลเหมือนที่ราชบิดาได้ทรงทำ