2 ነገሥት 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 1:1-18

የእግዚአብሔር ፍርድ በአካዝያስ ላይ

1አክዓብ ከሞተ በኋላ ሞዓብ በእስራኤል ላይ ዐመፀ። 2በዚህ ጊዜ አካዝያስ በሰማርያ ካለው እልፍኝ ሰገነቱ ላይ ሳለ፣ ከዐይነ ርግቡ ሾልኮ ወድቆ ነበርና ታመመ፤ ስለዚህ፣ “ሄዳችሁ ከዚህ ሕመም እድን እንደ ሆነ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ጠይቁ” ሲል መልእክተኞች ላከ።

3የእግዚአብሔር መልአክ ግን ቴስብያዊውን ኤልያስን እንዲህ አለው፤ “ተነሥተህ የሰማርያን ንጉሥ መልእክተኞች ለመገናኘት ውጣና፣ ‘የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ የምትሄዱ በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን?’ ብለህ ጠይቃቸው። 4ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።’ ” ከዚያም ኤልያስ ሄደ።

5መልእክተኞቹ ወደ ንጉሡ ሲመለሱ እርሱም፣ “ለምን ተመልሳችሁ መጣችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

6እነርሱም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ “አንድ ሰው ሊገናኘን መጥቶ፣ ‘ወደ ላካችሁ ንጉሥ ተመልሳችሁ ሂዱና፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ለመጠየቅ ሰዎች የምትልከው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ስለዚህ ከተኛህበት ዐልጋ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ።” ’ ”

7ንጉሡም፣ “ለመሆኑ ሊገናኛችሁ መጥቶ እንዲህ ያላችሁ ሰው እንዴት ያለ ነው?” ሲል ጠየቃቸው።

8እነርሱም “ሰውየው ጠጕራም ልብስ የለበሰ ነው፤ በወገቡም ላይ ጠፍር ታጥቋል” አሉት።

ንጉሡም፣ “ዐወቅሁት፤ ቴስብያዊው ኤልያስ ነው” አላቸው።

9ከዚያም ንጉሡ አንድ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ወታደሮቹ ጋር ወደ ኤልያስ ላከ። የአምሳ አለቃውም ኤልያስ ወደ ተቀመጠበት ኰረብታ ጫፍ ወጥቶ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

10ኤልያስም መልሶ የአምሳ አለቃውን፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ፣ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ አንተንና አምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው። ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ የአምሳ አለቃውንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

11እንደ ገናም ንጉሡ ሌላ የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ፤ የአምሳ አለቃውም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ ንጉሡ፣ ‘አሁኑኑ ና ውረድ’ ይልሃል” አለው።

12ኤልያስም መልሶ፣ “እኔ የእግዚአብሔር ሰው ከሆንሁ እሳት ከሰማይ ወርዳ አንተንና ሃምሳውን ሰዎችህን ትብላ!” አለው፤ ከዚያም እሳት ከሰማይ ወርዳ እርሱንና ሰዎቹን ፈጽማ በላች።

13ስለዚህም ንጉሡ ሦስተኛውን የአምሳ አለቃ ከአምሳ ሰዎቹ ጋር ላከ። ይህም ሦስተኛው የአምሳ አለቃ ወጥቶ፣ በኤልያስ ፊት በጕልበቱ ተንበርክኮ እንዲህ ሲል ለመነ፤ “አንተ የእግዚአብሔር ሰው፤ እባክህ የእኔና የእነዚህ የአምሳዎቹ አገልጋዮችህ ነፍስ በፊትህ የከበረች ትሁን። 14እነሆ፤ እሳት ከሰማይ ወርዳ፣ የፊተኞቹን ሁለት አምሳ አለቆችና ሰዎቻቸውን ሁሉ በላች፤ አሁን ግን ሕይወቴ በፊትህ የከበረች ትሁን።”

15የእግዚአብሔርም መልአክ ኤልያስን፣ “አብረኸው ውረድ፤ ደግሞም አትፍራው” አለው። ስለዚህ ኤልያስ ተነሣ፤ አብሮትም ወደ ንጉሡ ወረደ።

16ንጉሡንም፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለመሆኑ የአቃሮንን አምላክ ብዔልዜቡልን ስለ ራስህ ለመጠየቅ መልእክተኞች የላክኸው በእስራኤል አምላክ ስለሌለ ነውን? ይህን በማድረግህም ከተኛህበት ዐልጋ ፈጽሞ አትነሣም፤ በርግጥ ትሞታለህ’ ” ብሎ ነገረው። 17ስለዚህ አካዝያስ ኤልያስ እንደ ተናገረው እንደ እግዚአብሔር ቃል ሞተ።

አካዝያስ ወንድ ልጅ ስላልነበረው፣ የኢዮሣፍጥ ልጅ ኢዮራም በይሁዳ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ወንድሙ ኢዮራም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ። 18ሌላው አካዝያስ በዘመኑ ያከናወናቸውና የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ የተጻፉ አይደለምን?

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 1:1-18

องค์พระผู้เป็นเจ้า

1หลังจากที่อาหับสิ้นพระชนม์ ชนชาติโมอับกบฏต่ออิสราเอล 2ฝ่ายอาหัสยาห์ทรงพลัดตกจากเฉลียงชั้นบนของพระราชวังที่สะมาเรียพระอาการสาหัส พระองค์จึงทรงใช้ผู้สื่อสารไปกล่าวกับพวกเขาว่า “จงไปปรึกษาบาอัลเซบูบเทพเจ้าแห่งเอโครนว่าอาการบาดเจ็บของเราจะหายหรือไม่”

3แต่ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวกับเอลียาห์ชาวทิชบีว่า “จงไปพบผู้สื่อสารของกษัตริย์สะมาเรียนั้นและถามพวกเขาว่า ‘ในอิสราเอลไม่มีพระเจ้าหรือ ทำไมพวกเจ้าจึงต้องไปปรึกษาบาอัลเซบูบเทพเจ้าแห่งเอโครน?’ 4เพราะเหตุนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงตรัสว่า ‘เจ้าจะไม่ได้ลุกจากเตียงที่นอนอยู่ เจ้าจะต้องตายแน่!’ ” แล้วเอลียาห์ก็ไป

5เมื่อผู้สื่อสารของกษัตริย์กลับไปเข้าเฝ้า กษัตริย์ตรัสถามว่า “พวกเจ้ากลับมาทำไม?”

6พวกเขาทูลว่า “มีชายคนหนึ่งเดินเข้ามาหาพวกข้าพระบาท แล้วบอกให้กลับมาทูลฝ่าพระบาทว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ในอิสราเอลไม่มีพระเจ้าหรือ ทำไมเจ้าจึงต้องส่งคนไปปรึกษาบาอัลเซบูบเทพเจ้าแห่งเอโครน? เพราะเหตุนี้เจ้าจะไม่ได้ลุกจากเตียง แต่จะต้องตายแน่นอน!’ ”

7กษัตริย์ตรัสถามว่า “ชายคนที่มาพบและบอกเรื่องนี้แก่พวกเจ้าหน้าตาท่าทางเป็นอย่างไร?”

8พวกเขาทูลว่า “เขาสวมเสื้อคลุมขนสัตว์และใช้สายหนังคาดเอว”

กษัตริย์ตรัสว่า “เขาคือเอลียาห์ชาวทิชบี”

9แล้วพระองค์ทรงใช้นายทหารคนหนึ่งพร้อมด้วยทหารห้าสิบนายไปหาเอลียาห์ นายทหารขึ้นไปพบเอลียาห์ซึ่งนั่งอยู่บนยอดเขาแห่งหนึ่ง และกล่าวกับเขาว่า “คนของพระเจ้า กษัตริย์ตรัสว่า ‘จงลงมาเถิด!’ ”

10เอลียาห์ตอบนายทหารผู้นั้นว่า “หากเราเป็นคนของพระเจ้า ขอให้ไฟตกลงมาจากสวรรค์เผาผลาญเจ้าและทหารทั้งห้าสิบนายของเจ้า!” ไฟก็ตกลงมาเผาผลาญนายทหารและคนของเขาวอดวาย

11กษัตริย์จึงส่งนายทหารอีกคนพร้อมด้วยทหารห้าสิบนายมา นายทหารกล่าวกับเอลียาห์ว่า “คนของพระเจ้า กษัตริย์ตรัสว่า ‘จงลงมาทันที!’ ”

12เอลียาห์ตอบว่า “หากเราเป็นคนของพระเจ้า ขอให้ไฟตกลงมาจากสวรรค์เผาผลาญเจ้าและทหารห้าสิบนายของเจ้า!” แล้วไฟจากพระเจ้าก็ลงมาจากสวรรค์เผานายทหารและทหารทั้งห้าสิบนายวอดวาย

13กษัตริย์จึงส่งนายทหารกับทหารอีกห้าสิบนายมาเป็นครั้งที่สาม คราวนี้นายทหารคุกเข่าลงอ้อนวอนต่อหน้าเอลียาห์ว่า “ข้าแต่คนของพระเจ้า โปรดไว้ชีวิตข้าพเจ้าและคนทั้งห้าสิบคนซึ่งเป็นผู้รับใช้ของท่าน! 14ไฟจากสวรรค์ได้ลงมาเผาผลาญนายทหารสองคนก่อนหน้านี้กับพวก แต่บัดนี้ขอให้ไว้ชีวิตข้าพเจ้าเถิด!”

15ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวกับเอลียาห์ว่า “อย่ากลัวเลย ไปกับเขาเถิด” เอลียาห์จึงลงไปกับเขา แล้วไปเข้าเฝ้ากษัตริย์

16เอลียาห์ทูลกษัตริย์ว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า เป็นเพราะในอิสราเอลไม่มีพระเจ้าให้ปรึกษาใช่ไหม เจ้าจึงต้องส่งคนไปถามบาอัลเซบูบเทพเจ้าแห่งเอโครน? เนื่องจากเจ้าทำเช่นนี้ เจ้าจะไม่ได้ลุกจากเตียง แต่เจ้าจะต้องตายแน่นอน!” 17ดังนั้นอาหัสยาห์จึงสิ้นพระชนม์ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสไว้ผ่านทางเอลียาห์

เนื่องจากอาหัสยาห์ไม่มีโอรส โยรัม1:17 ภาษาฮีบรูว่าเยโฮรัมเป็นอีกรูปหนึ่งของโยรัมจึงขึ้นครองราชย์แทน ตรงกับปีที่สองแห่งรัชกาลกษัตริย์เยโฮรัมโอรสเยโฮชาฟัทแห่งยูดาห์

18เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลอาหัสยาห์ และพระราชกิจที่ทรงทำมีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งอิสราเอลไม่ใช่หรือ?