ዘፍጥረት 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 9:1-29

እግዚአብሔር ከኖኅ ጋር የገባው ኪዳን

1እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅንና ልጆቹን እንዲህ ሲል ባረካቸው፤ “ብዙ ተባዙ፤ ምድርንም ሙሏት፤ 2አስፈሪነታችሁና አስደንጋጭነታችሁ በዱር አራዊት፣ በሰማይ አዕዋፍ፣ በደረት በሚሳቡ ተንቀሳቃሽ ፍጡሮችና በባሕር ዓሦች ሁሉ ላይ ይሁን፤ በእጃችሁ ተሰጥተዋል። 3ሕያውና ተንቀሳቃሽ ፍጡር ሁሉ ምግብ ይሁናችሁ፤ ለምለሙን ዕፀዋት እንደ ሰጠኋችሁ፣ አሁን ደግሞ ሁሉን ሰጠኋችሁ።

4“ነገር ግን ሕይወቱ፣ ማለት ደሙ ገና በውስጡ ያለበትን ሥጋ አትብሉ። 5ሰውን የገደለ ሁሉ ስለ ሟቹ ደም ተጠያቂ ነው፤ የሟቹን ሰው ደም ከገዳዩ፣ ከእንስሳም ይሁን ከሰው እሻለሁ።

6“የሰውን ደም የሚያፈስስ ሁሉ፣

ደሙ በሰው እጅ ይፈስሳል፤

በእግዚአብሔር (ኤሎሂም) አምሳል፣

እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰውን ሠርቶታልና።

7እናንተ ግን ብዙ ተባዙ፤ ዘራችሁ በምድር ላይ ይብዛ፤ ይንሰራፋ።”

8እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅንና አብረውት ያሉትን ልጆቹን እንዲህ አላቸው፤ 9“እነሆ፤ ከእናንተና ከእናንተ በኋላ ከሚመጣው ዘራችሁ ጋር ኪዳኔን እመሠርታለሁ፤ 10እንዲሁም ከእናንተ ጋር ከነበሩት ሕያዋን ፍጡራን ሁሉ፦ ከወፎች፣ ከቤት እንስሳት፣ ከዱር እንስሳት፣ ከእናንተ ጋር ከመርከቧ ከወጡት በምድር ላይ ካሉት ሕያዋን ፍጡራን ሁሉ ጋር ኪዳን እገባለሁ። 11ከእንግዲህ ሕይወት ያለው ፍጡር ሁሉ በጥፋት ውሃ እንደማይጠፋ፣ ዳግመኛም ምድርን የሚያጠፋ ውሃ ከቶ እንደማይመጣ ከእናንተ ጋር ኪዳን እገባለሁ።”

12እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) እንዲህ አለ፤ “በእኔና በእናንተ መካከል፣ ከእናንተም ጋር ካሉ ሕያዋን ፍጡራን ሁሉ ጋር ከሚመጣውም ትውልድ ሁሉ ጋር፣ የማደርገው የኪዳኑ ምልክት ይህ ነው፤ 13ቀስተ ደመናዬን በደመና ላይ አደርጋለሁ፤ ይህም በእኔና በምድር መካከል ለገባሁት ኪዳን ምልክት ይሆናል። 14ደመናን በምድር ላይ በጋረድሁና ቀስቴም በደመና ላይ በሚታይበት ጊዜ ሁሉ፣ 15ከእናንተና ከሕያዋን ፍጡራን ሁሉ ጋር የገባሁትን ኪዳን ዐስባለሁ፤ ሕይወት ያለውንም ሁሉ ያጠፋ ዘንድ፣ ከእንግዲህ የጥፋት ውሃ ከቶ አይመጣም። 16ቀስቱ በደመና ላይ ተገልጦ በማይበት ጊዜ ሁሉ፣ በእኔና በምድር ላይ ባሉ ሕያዋን ፍጡራን መካከል ያለውን ዘላለማዊ ኪዳን ዐስባለሁ።”

17ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅን፣ “ይህ በእኔና በምድር ላይ በሚኖሩ ሕያዋን ሁሉ መካከል የገባሁት ኪዳን ምልክት ነው” አለው።

የኖኅ ልጆች

18ከመርከቧ የወጡትም የኖኅ ልጆች ሴም፣ ካምና ያፌት ነበሩ፤ ካም የከነዓን አባት ነው። 19ሦስቱ የኖኅ ልጆች እነዚህ ሲሆኑ፣ በምድር ላይ የሚኖሩ ሕዝቦች ሁሉ የተገኙት ከእነዚሁ ነው።

20ኖኅ ገበሬ ነበረና ወይን ተከለ፤9፥20 ወይም የመጀመሪያ ነበር 21ከወይኑም ጠጅ ጠጥቶ ሰከረና በድንኳኑ ውስጥ ዕርቃኑን ተኛ። 22የከነዓን አባት ካም የአባቱን ዕርቃነ ሥጋ አየ፤ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። 23ሴምና ያፌት ግን ልብስ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉና የአባታቸውን ዕርቃነ ሥጋ እንዳያዩ ፊታቸውን አዙረው የኋሊት በመሄድ የአባታቸውን ዕርቃነ ሥጋ ሸፈኑ።

24ኖኅ ከወይን ጠጁ ስካር ሲነቃ፣ ታናሽ ልጁ ያደረገበትን ዐወቀ፤ 25እንዲህም አለ፤

“ከነዓን የተረገመ ይሁን፤

ለወንድሞቹም፣ የባሪያ ባሪያ ይሁን።”

26ደግሞም፤

“የሴም አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ይባረክ፤

ከነዓንም የሴም9፥26 ወይም የእርሱ ባሪያ ይሁን ባሪያ ይሁን።

27እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የያፌትን9፥27 ያፌት የሚለው ቃል መዘርጋት የሚል ትርጕም ካለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር ተመሳሳይ ድምፅ አለው። ግዛት ያስፋ፤

ያፌት በሴም ድንኳኖች ይኑር፤

ከነዓንም የእርሱ9፥27 ወይም የእነርሱ ባሪያ ይሁን” አለ።

28ኖኅ ከጥፋት ውሃ በኋላ 350 ዓመት ኖረ፤ 29ኖኅ በአጠቃላይ 950 ዓመት ኖሮ ሞተ።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 9:1-29

พระเจ้าทรงทำพันธสัญญากับโนอาห์

1แล้วพระเจ้าทรงอวยพรโนอาห์กับบุตรของเขาและตรัสว่า “จงมีลูกมีหลานทวีขึ้นจนเต็มแผ่นดินโลก 2สัตว์ป่าทั้งปวงบนโลก นกทั้งปวงในอากาศ สัตว์ที่เลื้อยคลานทุกชนิด และปลาทั้งปวงในทะเลจะเกรงกลัวเจ้า เพราะเรามอบมันไว้ในมือของเจ้า 3ทุกสิ่งที่มีชีวิตและเคลื่อนไหวไปมาได้จะเป็นอาหารของเจ้า เราได้ยกพืชสีเขียวให้แก่เจ้าแล้วอย่างไร บัดนี้เราก็ให้ทุกสิ่งแก่เจ้าอย่างนั้น

4“แต่เจ้าจะต้องไม่กินเนื้อสัตว์พร้อมชีวิตของมัน คือเลือด 5สำหรับเลือดอันเป็นชีวิตของพวกเจ้า เราจะให้มีการชดใช้อย่างแน่นอน เราจะให้สัตว์ทุกตัวชดใช้ และเราจะให้แต่ละคนชดใช้ชีวิตของพี่น้องเพื่อนมนุษย์เช่นกัน

6“ใครก็ตามที่ฆ่าคน

เขาก็จะถูกคนฆ่า

เพราะพระเจ้าทรงสร้างคนขึ้น

ตามพระฉายของพระองค์

7ส่วนเจ้าจงมีลูกมีหลานมากมายเพิ่มจำนวนทวีขึ้นบนแผ่นดินโลก”

8แล้วพระเจ้าตรัสกับโนอาห์และบุตรของเขาว่า 9“บัดนี้เราเองเป็นผู้ทำพันธสัญญากับเจ้าและกับเชื้อสายของเจ้า 10ตลอดจนสัตว์ทุกตัวที่อยู่กับเจ้าคือ นก สัตว์ใช้งาน และสัตว์ป่า และสัตว์ทั้งปวงที่ออกจากเรือ คือสิ่งมีชีวิตทั้งหมดในโลกนี้ 11เราทำพันธสัญญากับเจ้าว่าจะไม่ให้น้ำท่วมทำลายล้างสิ่งมีชีวิตทั้งปวงอีกเลยและจะไม่ให้น้ำท่วมทำลายโลกอีกต่อไป”

12และพระเจ้าตรัสว่า “นี่คือเครื่องหมายแห่งพันธสัญญาที่เรากำลังทำระหว่างเรากับเจ้าและกับสิ่งมีชีวิตทั้งปวงที่อยู่กับเจ้า เป็นพันธสัญญาที่ผูกพันตลอดทุกชั่วอายุคน 13คือเราได้ตั้งรุ้งของเราไว้ที่หมู่เมฆ เป็นเครื่องหมายแห่งพันธสัญญาของเรากับโลก 14ทุกครั้งที่เราส่งเมฆมาเหนือโลก และรุ้งปรากฏขึ้นที่เมฆ 15เราจะระลึกถึงพันธสัญญาระหว่างเรากับเจ้าและกับสรรพสิ่งที่มีชีวิตทุกชนิดว่าจะไม่ให้น้ำท่วมทำลายล้างสิ่งมีชีวิตทั้งปวงอีกเลย 16เมื่อใดที่รุ้งปรากฏบนเมฆ รุ้งจะเตือนให้เราระลึกถึงพันธสัญญานิรันดร์ระหว่างพระเจ้ากับสรรพสิ่งที่มีชีวิตทุกชนิดบนโลก”

17พระเจ้าจึงตรัสแก่โนอาห์ว่า “นี่คือเครื่องหมายแห่งพันธสัญญาที่เราได้ทำไว้ระหว่างเรากับทุกชีวิตบนโลก”

บรรดาบุตรของโนอาห์

18บุตรของโนอาห์ที่ออกมาจากเรือคือ เชม ฮาม และยาเฟท (ฮามเป็นบิดาของคานาอัน) 19นี่คือบุตรทั้งสามของโนอาห์ ประชาชาติที่กระจายไปทั่วโลกถือกำเนิดจากพวกเขา

20โนอาห์เป็นชาวไร่ชาวนา9:20 ภาษาฮีบรูว่ามนุษย์แห่งแผ่นดินดูปฐก.5:29 เขาเริ่ม9:20 หรือเป็นคนแรกที่ทำสวนองุ่น 21เมื่อเขาดื่มเหล้าองุ่นแล้ว เขาก็เมาและนอนเปลือยกายอยู่ในเต็นท์ของเขา 22ฮามผู้เป็นบิดาของคานาอันเห็นบิดาเปลือยกายจึงบอกพี่ชายทั้งสองของเขาที่อยู่ข้างนอก 23แต่เชมกับยาเฟทเอาเสื้อผ้าพาดบ่า เดินถอยหลังเข้ามาในเต็นท์ เอาผ้าคลุมปกปิดร่างอันเปลือยเปล่าของบิดา เขาทั้งสองหันหน้าไปทางอื่นเพื่อจะได้ไม่เห็นความเปลือยเปล่าของบิดา

24เมื่อโนอาห์สร่างเมาและรู้ถึงสิ่งที่บุตรคนสุดท้องได้ทำต่อเขา 25ก็กล่าวว่า

“เราขอแช่งคานาอัน!

ให้เขาเป็นทาสต่ำต้อยที่สุด

ของพวกพี่น้อง”

26เขากล่าวอีกว่า

“สรรเสริญพระยาห์เวห์ พระเจ้าของเชม!

ขอให้คานาอันเป็นทาสของเชม

27ขอพระเจ้าทรงขยายพรมแดนของยาเฟท9:27 คำว่ายาเฟทมีเสียงคล้ายคำภาษาฮีบรูที่มีความหมายว่าขยายออก

ขอให้ยาเฟทอาศัยในเต็นท์ของเชม

และขอให้คานาอันเป็นทาสของยาเฟท”

28หลังจากน้ำท่วม โนอาห์มีชีวิตต่อไปอีก 350 ปี 29โนอาห์มีชีวิตอยู่รวมทั้งสิ้น 950 ปี แล้วเขาก็ตาย