ዘፍጥረት 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 8:1-22

1እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅንና በመርከቧ ውስጥ ከእርሱ ጋር የነበሩትን የዱርና የቤት እንስሳት ሁሉ ዐሰበ፤ በምድር ላይ ነፋስ እንዲነፍስ አደረገ፤ ውሃውም ጐደለ። 2የጥልቁ ምንጮችና የሰማይ ውሃ መስኮቶች ተዘጉ፤ ዝናቡም መዝነቡን አቆመ። 3ውሃው ከምድር ላይ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጣ፤ ከመቶ አምሳ ቀን በኋላም ጐደለ። 4በሰባተኛው ወር፣ በዐሥራ ሰባተኛው ቀን መርከቧ በአራራት ተራሮች ላይ ዐረፈች። 5ውሃው እስከ ዐሥረኛው ወር ድረስ እየቀነሰ መጣ፤ በዐሥረኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን የተራሮቹ ጫፎች ታዩ።

6ከአርባ ቀን በኋላ ኖኅ የሠራውን የመርከቧን መስኮት ከፍቶ፣ 7ቍራን ወደ ውጭ ላከ፤ ቍራውም ውሃው ከምድር ላይ እስኪደርቅ ድረስ ወዲያና ወዲህ ይበር ነበር። 8ከዚያም በኋላ፣ ኖኅ ውሃው ከምድር ገጽ ጐድሎ እንደ ሆነ ለማወቅ ርግብን ላከ፤ 9ነገር ግን ውሃው የምድርን ገጽ ገና እንደ ሸፈነ ስለ ነበር፣ ተመልሳ ኖኅ ወዳለበት መርከብ መጣች፤ እርሱም እጁን ዘርግቶ ተቀበላት፤ ወደ መርከቢቱም አስገባት። 10ሰባት ቀን ከቈየ በኋላ ኖኅ ርግቧን እንደ ገና ላካት። 11እርሷም ወደ ማታ ተመለሰች፤ እነሆም የለመለመ የወይራ ቅጠል በአፏ ይዛ ነበር፤ ያን ጊዜ ኖኅ ውሃው ከምድር ላይ መጕደሉን ዐወቀ። 12ሰባት ቀንም ቈይቶ ርግቧን እንደ ገና ላካት፤ በዚህ ጊዜ ግን ርግቧ ወደ እርሱ አልተመለሰችም።

13ኖኅ በተወለደ በ 601 ኛው ዓመት፣ በመጀመሪያው ወር፣ ከወሩም በመጀመሪያው ቀን ውሃው ከምድር ላይ ደረቀ። 14ኖኅ በመርከቡ ላይ ያለውን ክዳን አንሥቶ ተመለከተ፤ የመሬቱም ገጽ እንደ ደረቀ አየ። በሁለተኛው ወር፣ በሃያ ሰባተኛው ቀን ምድሪቱ ሙሉ በሙሉ ደረቀች።

15ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ኖኅን እንዲህ አለው፤ 16“አንተና ሚስትህ፣ ልጆችህና የልጆችህ ሚስቶች ከመርከቧ ውጡ። 17እንዲዋለዱ፣ እንዲራቡና በምድር ላይ እንዲበዙ፣ ከአንተ ጋር ያሉትን እንስሳትና በምድር ላይ የሚሳቡ ሕያዋን ፍጡራንን ሁሉ ይዘሃቸው ውጣ።”

18ኖኅም ከልጆቹ፣ ከሚስቱና ከልጆቹ ሚስቶች ጋር ወጣ። 19እንስሳቱ ሁሉ፣ ወፎችም፣ በምድር የሚንቀሳቀሱ ሁሉ በየወገናቸው ከመርከቧ ወጡ።

20ከዚያም ኖኅ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሠዊያ ሠራ፤ መሠዊያው ላይ ንጹሕ ከሆኑት እንስሳት ሁሉ፣ እንዲሁም ንጹሕ ከሆኑት ወፎች የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረበ፤ 21እግዚአብሔርም (ያህዌ) ደስ የሚያሰኘውን መዐዛ አሸተተ፤ በልቡም እንዲህ አለ፤ “ምንም እንኳ ሰው ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ሐሳቡ ወደ ክፋት ያዘነበለ ቢሆንም8፥21 ወይም ስለሆነ በእርሱ ምክንያት ሁለተኛ ምድርን አልረግማትም፤ አሁን እንዳደረግሁት ሕያዋን ፍጡራንን ዳግመኛ አላጠፋም።

22“ምድር እስካለች ድረስ፣

የዘር ወቅትና መከር፣

ሙቀትና ቅዝቃዜ

በጋና ክረምት፣

ቀንና ሌሊት፣

አይቋረጡም።”

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 8:1-22

1แต่พระเจ้าทรงระลึกถึงโนอาห์และสัตว์ป่ากับสัตว์ใช้งานทุกชนิดที่อยู่กับเขาในเรือ พระองค์ทรงบันดาลให้กระแสลมพัดเหนือแผ่นดิน แล้วน้ำก็ลดลง 2ตาน้ำบาดาลและประตูน้ำแห่งฟ้าสวรรค์ก็ถูกปิดและฝนก็หยุดตกจากฟ้า 3น้ำจึงลดลงเรื่อยๆ จนกระทั่ง 150 วันผ่านไป 4และในวันที่สิบเจ็ดของเดือนที่เจ็ด เรือก็มาค้างอยู่บนเทือกเขาอารารัต 5น้ำลดลงเรื่อยๆ จนกระทั่งวันที่หนึ่งของเดือนที่สิบ ยอดเขาอื่นๆ ก็ปรากฏให้เห็น

6หลังจากนั้นอีกสี่สิบวัน โนอาห์เปิดหน้าต่างเรือ 7และปล่อยกาตัวหนึ่งออกไป มันบินวนเวียนไปมาจนถึงเวลาที่น้ำแห้งไปจากแผ่นดินโลก 8เขาจึงปล่อยนกพิราบออกไปตัวหนึ่งเพื่อดูว่าน้ำลดจนถึงผิวดินแล้วหรือไม่ 9แต่นกพิราบไม่พบที่ที่จะเกาะเพราะว่าระดับน้ำยังสูงอยู่ จึงกลับมาหาโนอาห์ที่เรือ โนอาห์ก็ยื่นมือออกรับนกพิราบเข้ามาในเรือดังเดิม 10เขาคอยอีกเจ็ดวัน แล้วปล่อยนกพิราบออกไปจากเรืออีกครั้งหนึ่ง 11เมื่อนกพิราบกลับมาหาเขาในตอนเย็น มันคาบใบมะกอกเขียวสดมาด้วย โนอาห์จึงรู้ว่าน้ำลดลงจากแผ่นดินแล้ว 12เขาคอยอีกเจ็ดวันแล้วปล่อยนกพิราบออกไปอีก แต่คราวนี้มันไม่ได้กลับมาหาเขา

13เมื่อวันที่หนึ่งของเดือนที่หนึ่งในปีที่โนอาห์มีอายุ 601 ปี น้ำก็แห้ง โนอาห์เปิดหลังคาเรือออกมาดูก็เห็นว่าพื้นดินแห้งแล้ว 14พอถึงวันที่ยี่สิบเจ็ดเดือนที่สอง แผ่นดินก็แห้งสนิท

15แล้วพระเจ้าตรัสกับโนอาห์ว่า 16“เจ้า ภรรยาของเจ้า บรรดาบุตรชายและบุตรสะใภ้ของเจ้า จงออกจากเรือ 17จงนำสิ่งมีชีวิตทุกชนิดที่อยู่กับเจ้าออกมาด้วย ทั้งนก สัตว์ต่างๆ สัตว์ที่เลื้อยคลาน เพื่อพวกมันจะได้ออกลูกออกหลานและทวีจำนวนขึ้นในโลก”

18ดังนั้นโนอาห์จึงออกมาพร้อมกับบุตรชาย รวมทั้งภรรยาและบุตรสะใภ้ของเขา 19สัตว์ทั้งปวง สัตว์ที่เลื้อยคลานทั้งปวง นกทั้งปวง คือสิ่งมีชีวิตทั้งหมดบนโลกต่างทยอยออกจากเรือทีละชนิด

20หลังจากนั้นโนอาห์สร้างแท่นบูชาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าและถวายสัตว์และนกที่ไม่เป็นมลทินจำนวนหนึ่งเป็นเครื่องเผาบูชาบนแท่นนั้น 21องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงได้กลิ่นอันเป็นที่พอพระทัยและทรงดำริว่า “เราจะไม่สาปแช่งแผ่นดินเพราะมนุษย์อีกต่อไป ถึงแม้ว่า8:21 หรือเพราะว่าจิตใจของมนุษย์จะโน้มเอียงไปในทางชั่วตั้งแต่วัยเด็ก แต่เราจะไม่ทำลายล้างสิ่งมีชีวิตทั้งปวงอย่างที่เราได้ทำในคราวนี้อีก

22“ตราบใดที่โลกยังคงอยู่

ตราบนั้นจะมีฤดูหว่านและฤดูเก็บเกี่ยว

ความหนาวเย็นและความร้อน

ฤดูร้อนและฤดูหนาว

วันและคืน

อยู่เรื่อยไป”