ዘፀአት 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 1:1-22

እስራኤላውያን በጭቈና ሥር

1ቤተ ሰቦቻቸውን ይዘው ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ የሄዱት የእስራኤል ልጆች ስሞች እነዚህ ናቸው፦

2ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣

3ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ ብንያም፣

4ዳን፣ ንፍታሌም፣

ጋድና አሴር።

5የያዕቆብ ዘር ጠቅላላ ብዛት ሰባ1፥5 የማሶሬቱ ቅጅ (ዘፍ 46፥27 ይመ)፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (ሐሥ 7፥14 እና የዘፍ 46፥27 ማብ ይመ)፣ ሰባ አምስት ይላሉ። ሲሆን፣ ዮሴፍ ግን ቀደም ብሎ በግብፅ ነበረ።

6ከጊዜ በኋላ ዮሴፍና ወንድሞቹ ያም ትውልድ በሙሉ ሞቱ፤ 7ይሁን እንጂ እስራኤላውያን እየተዋለዱ በዙ፤ ቍጥራቸው እጅግ ከመጨመሩም የተነሣ የግብፅን ምድር ሞሏት።

8በግብፅም፣ ስለ ዮሴፍ የማያውቅ አዲስ ንጉሥ ነገሠ። 9እርሱም ሕዝቡን እንዲህ አላቸው፤ “እነሆ፤ እስራኤላውያን በቍጥር በልጠውናል፤ ከእኛም ይልቅ እየበረቱ ነው፤ 10ቍጥራቸው እንዳይጨምር፣ ጦርነት ቢነሣ ከጠላቶቻችን ጋር አብረው እንዳይወጉንና ከምድሪቱም ኰብልለው እንዳይሄዱ ዘዴ እንፈልግ።”

11ስለዚህ እያስጨነቁ የግዳጅ ሥራ የሚያሠሯቸውን አሠሪ አለቆች ሾሙባቸው። እስራኤላውያንም ፊቶምና ራምሴ የተባሉ ንብረት ማከማቻ ከተሞችን ለፈርዖን ሠሩለት። 12ነገር ግን ባስጨነቋቸው መጠን የእስራኤላውያን ቍጥር በዛ፤ በምድሪቱም እየተስፋፉ ሄዱ፤ ከዚህም የተነሣ ግብፃውያኑ እስራኤላውያንን እጅግ ፈሯቸው፤ 13ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታም ያሠሯቸው ጀመር። 14ጭቃ በማስቦካት፣ ጡብ በማሠራትና በእርሻም ሁሉ እያስጨነቁ ከባድ ሥራ እንዲሠሩ በማድረግ ሕይወታቸውን አስመረሩ፤ ግብፃውያኑ በሚያሠሯቸው ከባድ ሥራ ሁሉ ፈጽሞ አይራሩላቸውም ነበር።

15የግብፅም ንጉሥ ሲፓራና ፉሐ የተባሉትን ዕብራውያን ሴቶች አዋላጆች እንዲህ አላቸው፤ 16“የዕብራውያንን ሴቶች በማማጫው ድንጋይ ላይ በምታዋልዱበት ጊዜ የሚወለደው ሕፃን ወንድ ከሆነ ግደሉት፤ ሴት ከሆነች ግን በሕይወት ትኑር።” 17አዋላጆቹ ግን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ስለ ፈሩ የግብፅ ንጉሥ ያዘዛቸውን አልፈጸሙም፤ ወንዶቹንም ልጆች በሕይወት እንዲኖሩ ተዉአቸው። 18ንጉሡም አዋላጆቹን ጠርቶ፣ “ለምንድን ነው ወንዶቹን ልጆች በሕይወት እንዲኖሩ የተዋችኋቸው?” አላቸው።

19እነርሱም፣ “የዕብራውያን ሴቶች እንደ ግብፃውያን ሴቶች አይደሉም፤ ብርቱዎች ስለሆኑ አዋላጆች ከመድረሳቸው በፊት ይወልዳሉ” ሲሉ ለፈርዖን መለሱለት።

20ከዚህም የተነሣ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ለአዋላጆቹ መልካም ሆነላቸው፤ ሕዝቡም በቍጥር እየበዛና እያየለ ሄደ። 21አዋላጆቹም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) በመፍራታቸው ቤተ ሰብ ሰጣቸው።

22ፈርዖንም፣ “የሚወለደውን ወንድ ልጅ1፥22 የማሶሬቱ ቅጅ፣ ኦሪተ ሳምራውያን፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም እንዲሁም ታርጕም ከዕብራውያን የሚወለደውን ይላሉ። ሁሉ አባይ ወንዝ ውስጥ ጣሉት፤ ሴት ልጅ ሁሉ ግን በሕይወት ትኑር” ሲል ሕዝቡን አዘዘ።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 1:1-22

ชนอิสราเอลถูกกดขี่ข่มเหง

1ต่อไปนี้เป็นรายชื่อบุตรชายของอิสราเอล ซึ่งติดตามยาโคบไปยังอียิปต์พร้อมด้วยครอบครัวของเขา 2ได้แก่ รูเบน สิเมโอน เลวี ยูดาห์ 3อิสสาคาร์ เศบูลุน เบนยามิน 4ดาน นัฟทาลี กาด และอาเชอร์ 5วงศ์วานของยาโคบที่เข้าไปในอียิปต์กับเขานับได้ทั้งหมดเจ็ดสิบคน1:5 ฉบับ DSS. และ LXX. (ดูปฐก.46:27; กจ.7:14 และ เชิงอรรถปฐก.46:27) ว่า75 คน ส่วนโยเซฟอยู่ที่นั่นแล้ว

6ต่อมาโยเซฟกับพวกพี่น้องและคนในชั่วอายุนั้นก็เสียชีวิตหมด 7แต่ชนอิสราเอลมีลูกเต็มบ้านมีหลานเต็มเมืองจนกลายเป็นชนชาติใหญ่อยู่คับคั่งในดินแดนนั้น

8เมื่อกษัตริย์องค์ใหม่ซึ่งไม่ได้รู้จักโยเซฟขึ้นครองราชย์ในอียิปต์ 9พระองค์ตรัสกับประชากรของพระองค์ว่า “ดูสิ ชนอิสราเอลพวกนี้มีจำนวนมากเกินไปสำหรับเราแล้ว 10เราต้องจัดการกับพวกเขาอย่างแยบยล มิฉะนั้นพวกเขาจะยิ่งมีจำนวนมากขึ้น และถ้าเกิดสงคราม พวกนี้จะสมคบกับศัตรูหันมารบกับเรา แล้วหนีออกนอกประเทศ”

11ดังนั้นชาวอียิปต์จึงบีบบังคับพวกอิสราเอลให้เป็นทาส และตั้งนายงานคอยควบคุมพวกเขาให้ทำงานหนัก ให้สร้างเมืองปิธมและราเมเสสขึ้นเป็นเมืองพระคลังสำหรับฟาโรห์ 12แต่ยิ่งชนอิสราเอลถูกกดขี่ข่มเหงมากเท่าไร พวกเขาก็ยิ่งเพิ่มจำนวนและแพร่ขยายมากขึ้นเท่านั้น ดังนั้นชาวอียิปต์จึงหวั่นเกรงชนอิสราเอล 13และเคี่ยวเข็ญพวกเขาอย่างทารุณ 14ชาวอียิปต์สร้างความขมขื่นในชีวิตให้แก่ชนอิสราเอล โดยให้พวกเขาทำงานหนัก ไม่ว่าจะเป็นการทำอิฐทำปูน และทำงานทุกชนิดในท้องทุ่ง ชาวอียิปต์ ใช้พวกเขาทำงานอย่างทารุณ

15กษัตริย์อียิปต์ตรัสกับนางผดุงครรภ์ชาวฮีบรูชื่อชิฟราห์และปูอาห์ว่า 16“เมื่อเจ้าทำคลอดให้หญิงชาวฮีบรูและดูแลหญิงนั้นขณะคลอด ถ้าทารกเป็นผู้ชายให้ฆ่าทิ้ง ถ้าเป็นผู้หญิงให้ไว้ชีวิต” 17แต่นางผดุงครรภ์ทั้งสองยำเกรงพระเจ้า จึงไม่ได้ปฏิบัติตามคำสั่งของกษัตริย์อียิปต์ พวกนางปล่อยให้เด็กผู้ชายมีชีวิตอยู่ 18กษัตริย์อียิปต์จึงรับสั่งให้นำตัวนางผดุงครรภ์ทั้งสองมาเข้าเฝ้าและตรัสถามว่า “เหตุใดเจ้าจึงทำเช่นนี้? เหตุใดเจ้าจึงปล่อยเด็กผู้ชายให้มีชีวิตอยู่?”

19นางผดุงครรภ์ทั้งสองกราบทูลว่า “ผู้หญิงฮีบรูไม่เหมือนผู้หญิงอียิปต์ พวกเขาแข็งแรงและคลอดลูกก่อนที่นางผดุงครรภ์จะไปถึง”

20ดังนั้นพระเจ้าทรงอวยพรนางผดุงครรภ์ทั้งสองนี้ และชาวอิสราเอลเพิ่มจำนวนและทวีมากขึ้น 21เนื่องจากนางผดุงครรภ์ยำเกรงพระเจ้า พระองค์จึงทรงให้นางทั้งสองมีครอบครัวของตนเอง

22ฟาโรห์รับสั่งแก่ประชาชนทั้งปวงของพระองค์ว่า “ให้จับเด็กผู้ชายฮีบรูแรกเกิดทุกคนโยนทิ้งลงในแม่น้ำไนล์ ส่วนเด็กผู้หญิงให้ไว้ชีวิต”