ዘፍጥረት 36 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 36:1-43

የዔሳው ዝርያዎች

36፥10-14 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥35-37

36፥20-28 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥38-42

1ኤዶም የተባለው የዔሳው ትውልድ ይህ ነው፦

2ዔሳው ከከነዓን ሴቶች አገባ፤ እነርሱም፦ የኬጢያዊው የዔሎን ልጅ ዓዳን፣ የኤዊያዊው የፅብዖን ልጅ ዓና የወለዳት አህሊባማ፣ 3እንዲሁም የነባዮት እኅት የሆነችው የእስማኤል ልጅ ቤሴሞት ነበሩ።

4ዓዳ ለዔሳው ኤልፋዝን ወለደችለት፤ ቤሴሞት ደግሞ ራጉኤልን ወለደችለት። 5እንደዚሁም አህሊባማ የዑስን፣ የዕላምንና ቆሬን ወለደችለት፤ እነዚህ ዔሳው በከነዓን አገር የወለዳቸው ልጆች ናቸው።

6ዔሳው ሚስቶቹን፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቹን፣ ቤተ ሰቦቹን በሙሉ እንደዚሁም የቀንድ ከብቶቹንና ሌሎቹንም እንስሳት ሁሉ በከነዓን ምድር ያፈራውን ሀብት እንዳለ ይዞ ከወንድሙ ከያዕቆብ ራቅ ወዳለ ቦታ ሄደ። 7ብዙ ሀብት ስለ ነበራቸው አብረው መኖር አልቻሉም፤ የነበሩበትም ስፍራ ከከብቶቻቸው ብዛት የተነሣ ሊበቃቸው አልቻለም። 8ስለዚህ ኤዶም የተባለው ዔሳው መኖሪያውን በተራራማው አገር በሴይር አደረገ።

9በሴይር ተራራማ አገር የሚኖሩ የኤዶማውያን አባት፣ የዔሳው ዝርያዎች እነዚህ ናቸው፤

10የዔሳው ልጆች ስም፦

የዔሳው ሚስት የዓዳ ልጅ ኤልፋዝና የዔሳው ሚስት የቤሴሞት ልጅ ራጉኤል፤

11የኤልፋዝ ልጆች፦

ቴማን፣ ኦማር፣ ስፎ፣ ጎቶምና ቄኔዝ፤ 12የዔሳው ልጅ ኤልፋዝ ትምናዕ የምትባል ቁባት ነበረችው፤ እርሷም አማሌቅን ወለደችለት፤ የዔሳው ሚስት የዓዳ የልጅ ልጆች እነዚህ ናቸው።

13የራጉኤል ልጆች፦

ናሖት፣ ዛራ፣ ሣማና ሚዛህ፤ እነዚህ ደግሞ የዔሳው ሚስት የቤሴሞት የልጅ ልጆች ናቸው።

14የፅብዖን የልጅ ልጅ፣ የዓና ልጅ የዔሳው ሚስት አህሊባማ ለዔሳው የወለደቻቸው ልጆች፦

የዑስ፣ የዕላማና ቆሬ።

15ከዔሳው ዝርያዎች እነዚህ የነገድ አለቆች ነበሩ፤

የዔሳው የበኵር ልጅ የኤልፋዝ ልጆች፦

አለቃ ቴማን፣ አለቃ ኦማር፣ አለቃ ስፎ፣ አለቃ ቄኔዝ፣ 16አለቃ ቆሬ፣36፥16 ከማሶሬቲኩ ጽሑፍ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን በኦሪተ ሳምራውያን ግን (በተጨማሪ ዘፍ 36፥11 እና 1ዜና 1፥36 ይመ) ውስጥ “ቆሬ” የሚለው ቃል የለም። አለቃ ጎቶምና አለቃ አማሌቅ፤ እነዚህ በኤዶም ምድር ከኤልፋዝ የተገኙ የነገድ አለቆች፣ የዓዳ የልጅ ልጆች ነበሩ።

17የዔሳው ልጅ ራጉኤል ልጆች፦

አለቃ ናሖት፣ አለቃ ዛራ፣ አለቃ ሣማና አለቃ ሚዛህ፤ እነዚህ በኤዶም ምድር ከራጉኤል የተገኙ የነገድ አለቆች፣ የዔሳው ሚስት የቤሴሞት የልጅ ልጅ ነበሩ።

18የዔሳው ሚስት የአህሊባም ልጆች፦

አለቃ የዑስ፣ አለቃ የዕላማና፣ አለቃ ቆሬ፤ እነዚህ ከዓና ልጅ፣ ከዔሳው ሚስት ከአህሊባማ የተገኙ የነገድ አለቆች ነበሩ።

19እነዚህም ኤዶም የተባለው የዔሳው ልጆችና የነገድ አለቆቻቸው ነበሩ።

20በዚያች ምድር ይኖሩ የነበሩ የሖሪው የሴይር ልጆች እነዚህ ነበሩ፦

ሎጣን፣ ሦባል፣ ፅብዖን፣ ዓና፣ 21ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በኤዶም የነበረው የሴይር ልጆች፣ የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

22የሎጣን ልጆች፦

ሖሪና ሔማም36፥22 ሔማም የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ሖማም ለሚለው ቃል አማራጭ ትርጕም ነው (1ዜና 1፥39 ይመ)።፤ የሎጣንም እኅት ቲምናዕ ትባል ነበር።

23የሦባል ልጆች፦

ዓልዋን፣ ማኔሐት፣ ዔባል፣ ስፎና አውናም፤

24የፅብዖን ልጆች፦

አያና ዓና፤ ይህ ዓና የአባቱን የፅብዖንን አህዮች ሲጠብቅ፣ የፍል ውሃ ምንጮችን36፥24 ከቩልጌት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ሱርስቱ ግን የተገኘ ውሃ ይለዋል፤ በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። በምድረ በዳ ያገኘ ሰው ነው።

25የዓና ልጆች፦

ዲሶንና የዓና ሴት ልጅ አህሊባማ፤

26የዲሶን36፥26 በዕብራይስጥ ዲሳን፣ የዲሶን አማራጭ ትርጕም ነው። ልጆች፦

ሔምዳን፣ ኤስባን፣ ይትራንና ክራን፤

27የኤጽር ልጆች፦

ቢልሐን፣ ዛዕዋንና ዓቃን፤

28የዲሳን ልጆች፦

ዑፅና አራን።

29የሖሪውያን የነገድ አለቆች እነዚህ ነበሩ፦

ሎጣን፣ ሦባል፣ ፅብዖን፣ ዓና፣ 30ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በሴይር ምድር እንደየነገዳቸው የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

የኤዶም ነገሥታት

36፥31-43 ተጓ ምብ – 1ዜና 1፥43-54

31ንጉሥ በእስራኤል ከመንገሡ በፊት፣36፥31 ወይም እስራኤላዊ መንግሥት በእነርሱ ላይ ከመንገሡ በፊት በኤዶም የነገሡ ነገሥታት እነዚህ ነበሩ፦

32የቢዖር ልጅ ባላቅ በኤዶም ነበር፤ የከተማውም ስም ዲንሃባ ይባል ነበር።

33ባላቅ ሲሞት፣ የባሶራው የዛራ ልጅ ኢዮባብ በምትኩ ነገሠ።

34ኢዮባብ ሲሞት፣ የቴማኒው ሑሳም በምትኩ ነገሠ።

35ሑሳም ሲሞት፣ የምድያምን ሰዎች በሞዓብ ምድር ድል ያደረጋቸው የባዳድ ልጅ ሃዳድ በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ዓዊት ይባል ነበር።

36ሃዳድ ሲሞት፣ የመሥሬቃው ሠምላ በምትኩ ነገሠ።

37ሠምላ ሲሞት፣ በወንዙ36፥37 የኤፍራጥስ ወንዝ ሊሆን ይችላል። አጠገብ ያለው የርሆቦቱ ሳኦል በምትኩ ነገሠ።

38ሳኦል ሲሞት፣ የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን በምትኩ ነገሠ።

39የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን ሲሞት፣ ሃዳር በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ፋዑ ይባል ነበር፤ የሚስቱም ስም መሄጣብኤል ሲሆን፣ እርሷም የሜዛሃብ ልጅ መጥሬድ የወለደቻት ነበረች።

40ከዔሳው የተገኙት የነገድ አለቆች ስም፣ እንደየነገዳቸውና እንደየአገራቸው ይህ ነው፦

ቲምናዕ፣ ዓልዋ፣ የቴት፣

41አህሊባማ፣ ኤላ፣ ፊኖን፣

42ቄኔዝ፣ ቴማን፣ ሚብሳር፣

43መግዲኤልና ዒራም።

እነዚህ፣ በያዙት ምድር እንደየይዞታቸው ከኤዶም የተገኙ የነገድ አለቆች ነበሩ።

ይህም ዔሳው፣ የኤዶማውያን አባት ነው።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 36:1-43

วงศ์วานของเอซาว

(1พศด.1:35-42)

1นี่คือเรื่องราวเชื้อสายของเอซาว (คือเอโดม)

2เอซาวแต่งงานกับหญิงชาวคานาอันคือ อาดาห์บุตรสาวของเอโลนชาวฮิตไทต์ และโอโฮลีบามาห์เป็นบุตรสาวของอานาห์ และเป็นหลานสาวของศิเบโอนชาวฮีไวต์ 3และบาเสมัทบุตรสาวของอิชมาเอล น้องสาวของเนบาโยท

4อาดาห์ให้กำเนิดเอลีฟัสแก่เอซาว บาเสมัทให้กำเนิดเรอูเอล 5และโอโฮลีบามาห์ให้กำเนิดเยอูช ยาลาม และโคราห์ ทั้งหมดนี้คือบุตรชายของเอซาวที่เกิดในดินแดนคานาอัน

6เอซาวพาภรรยาทั้งหลาย บุตรชายหญิง คนทั้งปวงในครัวเรือน ฝูงสัตว์ สัตว์อื่นๆ รวมทั้งทรัพย์สมบัติทั้งหมดที่หามาได้ในดินแดนคานาอันย้ายไปยังอีกดินแดนหนึ่งซึ่งอยู่ไกลจากยาโคบน้องชายของเขา 7ทรัพย์สมบัติที่ทั้งสองฝ่ายมีนั้นมากเกินกว่าที่เขาทั้งสองจะอาศัยอยู่ร่วมกันได้ ดินแดนนั้นไม่สามารถรองรับฝูงสัตว์ของเขาทั้งสอง 8ดังนั้นเอซาว (คือเอโดม) จึงไปตั้งถิ่นฐานในแดนเทือกเขาเสอีร์

9นี่คือเรื่องราวเชื้อสายของเอซาวบิดาของชนชาติเอโดมในแดนเทือกเขาเสอีร์

10ต่อไปนี้เป็นรายชื่อบุตรชายของเอซาว

เอลีฟัสซึ่งเกิดจากนางอาดาห์ภรรยาของเอซาว และเรอูเอลซึ่งเกิดจากบาเสมัทภรรยาของเอซาว

11บุตรชายของเอลีฟัสได้แก่

เทมาน โอมาห์ เศโฟ กาทาม และเคนัส

12เอลีฟัสบุตรเอซาวมีภรรยาน้อยชื่อทิมนา ผู้ให้กำเนิดอามาเลขแก่เขา คนเหล่านี้เป็นหลานชายของนางอาดาห์ภรรยาของเอซาว

13บุตรชายของเรอูเอลได้แก่

นาหาท เศราห์ ชัมมาห์ และมิสซาห์ คนเหล่านี้เป็นหลานชายของนางบาเสมัทภรรยาของเอซาว

14บุตรชายของเอซาวซึ่งเกิดจากนางโอโฮลีบามาห์ภรรยาของเอซาว ซึ่งเป็นบุตรสาวของอานาห์และเป็นหลานสาวของศิเบโอน ได้แก่

เยอูช ยาลาม และโคราห์

15ต่อไปนี้เป็นรายชื่อหัวหน้าตระกูลในหมู่ลูกหลานของเอซาว

บุตรของเอลีฟัส ผู้เป็นบุตรหัวปีของเอซาวได้แก่

หัวหน้าเทมาน โอมาร์ เศโฟ เคนัส 16โคราห์36:16 ฉบับ SamP. ว่าไม่มีคำว่าโคราห์(ดูข้อ 11 และ1พศด.1:36) กาทาม และอามาเลข คนเหล่านี้คือหัวหน้าซึ่งสืบเชื้อสายจากเอลีฟัสแห่งเอโดม พวกเขาเป็นหลานชายของนางอาดาห์

17บุตรชายของเรอูเอลผู้เป็นบุตรของเอซาวได้แก่

หัวหน้านาหาท เศราห์ ชัมมาห์ และมิสซาห์ คนเหล่านี้คือหัวหน้าซึ่งสืบเชื้อสายจากเรอูเอลแห่งเอโดม พวกเขาเป็น หลานชายของนางบาเสมัทภรรยาของเอซาว

18บุตรชายของนางโอโฮลีบามาห์ภรรยาของเอซาวได้แก่

หัวหน้าเยอูช ยาลาม และโคราห์ คนเหล่านี้คือหัวหน้าซึ่งสืบเชื้อสายจากนางโอโฮลีบามาห์บุตรสาวของอานาห์ภรรยาของเอซาว

19คนเหล่านี้เป็นบุตรชายของเอซาว (คือเอโดม) และคนเหล่านี้เป็นหัวหน้าของพวกเขา

20ต่อไปนี้เป็นบุตรชายของเสอีร์ชาวโฮรีซึ่งอาศัยอยู่ในท้องถิ่นนั้น

โลทาน โชบาล ศิเบโอน อานาห์ 21ดีโชน เอเซอร์ และดีชาน คนเหล่านี้เป็นบุตรชายของเสอีร์แห่งเอโดม ซึ่งเป็นหัวหน้าของชาวโฮรี

22บุตรชายของโลทานได้แก่

โฮรีและโฮมาม36:22 ภาษาฮีบรูว่าเฮมามเป็นอีกรูปหนึ่งของโฮมาน(ดู1พศด.1:39) ทิมนาเป็นน้องสาวของโลทาน

23บุตรชายของโชบาลได้เแก่

อัลวาน มานาฮาท เอบาล เชโฟ และโอนัม

24บุตรชายของศิเบโอนได้แก่

อัยยาห์และอานาห์ อานาห์คือผู้ค้นพบบ่อน้ำพุร้อน36:24 ฉบับ Syr. ว่าค้นพบน้ำ คำนี้ในภาษาฮีบรูมีความหมายไม่ชัดเจนในทะเลทรายขณะที่เลี้ยงฝูงลาของศิเบโอนผู้เป็นบิดา

25บุตรของอานาห์ได้แก่

ดีโชนและโอโฮลีบามาห์ ซึ่งเป็นบุตรสาวของอานาห์

26บุตรชายของดีโชน36:26 ภาษาฮีบรูว่าดีชานเป็นอีกรูปหนึ่งของดีโชนได้แก่

เฮมดาน เอชบาน อิธราน และเคราน

27บุตรชายเอเซอร์ได้แก่

บิลฮาน ศาอาวาน และอาขาน

28บุตรชายของดีชานได้แก่

อูศและอารัน

29ต่อไปนี้เป็นหัวหน้าของชาวโฮรี ได้แก่

โลทาน โชบาล ศิเบโอน อานาห์ 30ดีโชน เอเซอร์ และดีชาน ซึ่งแบ่งตามส่วนการปกครองของพวกเขาในดินแดนเสอีร์

กษัตริย์ของเอโดม

(1พศด.1:43-54)

31ต่อไปนี้เป็นบรรดากษัตริย์ที่ครองราชย์ในเอโดมก่อนที่ชนอิสราเอลจะมีกษัตริย์ปกครอง36:31 หรือก่อนกษัตริย์อิสราเอลปกครองเหนือพวกเขา

32เบลา บุตรเบโอร์ ได้ขึ้นเป็นกษัตริย์แห่งเอโดม เมืองของพระองค์ชื่อดินฮาบาห์

33เมื่อเบลาสิ้นพระชนม์ โยบับบุตรเศราห์จากโบสราห์ได้ขึ้นปกครองแทน

34เมื่อโยบับสิ้นพระชนม์ หุชามจากดินแดนของชาวเทมานได้ขึ้นปกครองแทน

35เมื่อหุชามสิ้นพระชนม์ ฮาดัดบุตรเบดัดผู้มีชัยเหนือกองทัพมีเดียนในดินแดนโมอับได้ขึ้นปกครองแทน เมืองของพระองค์ชื่ออาวีท

36เมื่อฮาดัดสิ้นพระชนม์ สัมลาห์จากมัสเรคาห์ได้ขึ้นปกครองแทน

37เมื่อสัมลาห์สิ้นพระชนม์ ชาอูลจากเรโหโบทที่อยู่ริมแม่น้ำ36:37 อาจจะเป็น แม่น้ำยูเฟรติสได้ขึ้นปกครองแทน

38เมื่อชาอูลสิ้นพระชนม์ บาอัลฮานันบุตรชายอัคโบร์ได้ขึ้นปกครองแทน

39เมื่อบาอัลฮานันสิ้นพระชนม์ ฮาดัด36:39 สำเนา MT. บางฉบับ ว่าฮาดาร์(ดู1พศด.1:50)ได้ขึ้นปกครองแทน เมืองของพระองค์ชื่อปาอู มเหสีของพระองค์ชื่อเมเหทาเบล บุตรีของมัทเรดผู้เป็นบุตรีของเมซาหับ

40ต่อไปนี้เป็นรายชื่อหัวหน้าที่สืบเชื้อสายจากเอซาว แบ่งตามตระกูลและถิ่นฐานที่ปกครอง ได้แก่

ทิมนา อัลวาห์ เยเธท 41โอโฮลีบามาห์ เอลาห์ ปิโนน 42เคนัส เทมาน มิบซาร์ 43มักดีเอล และอิราม คนเหล่านี้คือหัวหน้าของเอโดม แบ่งตามถิ่นฐานในดินแดนที่ปกครอง

นี่คือเอซาว บิดาของชาวเอโดม