ዘፍጥረት 35 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 35:1-29

ያዕቆብ ወደ ቤቴል ተመለሰ

1እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ያዕቆብን፣ “ተነሥና ወደ ቤቴል ውጣ፤ እዚያም ተቀመጥ፤ ከወንድምህ ከዔሳው ሸሽተህ በሄድህ ጊዜ ለተገለጠልህ አምላክ (ኤል) በዚያ መሠዊያ ሥራ” አለው።

2ስለዚህም ያዕቆብ ለቤቱ ሰዎችና አብረውት ለነበሩት ሁሉ እንዲህ አላቸው፤ “በእናንተ ዘንድ ያሉትን ባዕዳን አማልክት አስወግዱ፤ ሰውነታችሁን አንጹ፤ ልብሳችሁንም ለውጡ። 3ተነሥተን ወደ ቤቴል እንውጣ፤ እዚያም በመከራዬ ጊዜ ለሰማኝ፣ በሄድሁበትም ስፍራ ሁሉ ላልተለየኝ አምላክ (ኤል) መሠዊያ እሠራለሁ።” 4ስለዚህ በእነርሱ ዘንድ የነበሩትን ባዕዳን አማልክት ሰብስበው፣ የጆሮ ጕትቾቻቸውን አውልቀው ለያዕቆብ ሰጡት። ያዕቆብም ወስዶ ሴኬም አጠገብ ካለው ወርካ ዛፍ ሥር ቀበራቸው። 5ያንንም ቦታ ለቅቀው ሄዱ፤ እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) በዙሪያቸው በነበሩት ከተሞች ሁሉ ላይ ፍርሀትና ድንጋጤ ስለ ለቀቀባቸው ያሳደዳቸው አልነበረም።

6ያዕቆብና አብረውት የነበሩት ሰዎች ሁሉ፣ በከነዓን ወደምትገኘው፣ ቤቴል ወደተባለችው ወደ ሎዛ ደረሱ። 7ያዕቆብም በዚያ ስፍራ መሠዊያ ሠርቶ፣ ስሙን ኤል-ቤቴል35፥7 ኤል-ቤቴል ማለት የቤቴል አምላክ ማለት ነው። አለው፤ ምክንያቱም ከወንድሙ ሸሽቶ በሄደ ጊዜ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የተገለጠለት በዚህ ቦታ ነበር።

8በዚህ ጊዜ የርብቃ ሞግዚት ዲቦራ ሞተች፤ ከቤቴል ዝቅ ብሎ በሚገኘው ወርካ ዛፍ ሥር ተቀበረች። ከዚህ የተነሣም ያ ቦታ አሎንባኩት35፥8 አሎንባኩት ማለት የለቅሶ ወርካ ማለት ነው። ተባለ።

9ያዕቆብ ከሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ከተመለሰ በኋላ፣ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ለያዕቆብ ዳግመኛ ተገለጠለት፤ ባረከውም። 10እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “እስካሁን ስምህ ያዕቆብ35፥10 ያዕቆብ ማለት ተረከዝ ይይዛል ማለት ነው፤ በምሳሌያዊ አገላለጽ ያታልላል ማለት ነው። ነበረ፤ ከእንግዲህ ያዕቆብ ተብለህ አትጠራም፤ ነገር ግን ስምህ እስራኤል35፥10 እስራኤል ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ ማለት ነው። ይባላል” አለው።

ስለዚህም እስራኤል ብሎ ጠራው።

11ደግሞም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ያዕቆብን እንዲህ አለው፤ “እኔ ሁሉን ማድረግ የሚችል35፥11 በዕብራይስጥ ኤልሻዳይ ማለት ነው። አምላክ ነኝ፤ ብዛ ተባዛ፤ ሕዝብና የሕዝቦች ማኅበር ከአንተ ይወጣሉ፤ ነገሥታትም ከአብራክህ ይከፈላሉ። 12ለአብርሃምና ለይስሐቅ የሰጠኋትን ምድር ለአንተ እሰጥሃለሁ፤ ከአንተም በኋላ ይህችኑ ምድር ለዘርህ እሰጣለሁ።” 13እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ከእርሱ ጋር ከተነጋገረበት ስፍራ ወደ ላይ ወጣ።

14ያዕቆብ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ከእርሱ ጋር በተነጋገረበት ስፍራ የድንጋይ ሐውልት አቆመ፤ በሐውልቱ ላይ የመጠጥ ቍርባን አፈሰሰ፤ ዘይትም አፈሰሰበት። 15ያዕቆብም፣ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ከእርሱ ጋር የተነጋገረበትን ስፍራ ቤቴል35፥15 ቤቴል ማለት የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው። ብሎ ጠራው።

የራሔልና የይስሐቅ መሞት

35፥23-26 ተጓ ምብ – 1ዜና 2፥1-2

16ከዚያም ከቤቴል ተነሥተው ሄዱ፤ ኤፍራታ ለመድረስ ጥቂት ሲቀራቸው ራሔልን ምጥ ያዛት፤ ምጡም ጠናባት። 17ምጡ አስጨንቋት ሳለ፣ አዋላጇ፣ “አይዞሽ አትፍሪ፤ ሌላ ወንድ ልጅ ልትገላገይ ነው” አለቻት። 18እርሷ ግን ሕይወቷ ልታልፍ በማጣጣር ላይ ሳለች፣ ልጇን ቤንኦኒ35፥18 ቤንኦኒ ማለት የመከራዬ ልጅ ማለት ነው። አለችው፤ አባቱ ግን ብንያም35፥18 ብንያም ማለት የቀኜ ልጅ ማለት ነው። አለው።

19ራሔልም ሞተች፤ ወደ ኤፍራታ በሚወስደው መንገድ በቤተ ልሔም ተቀበረች። 20ያዕቆብም በራሔል መቃብር ላይ ሐውልት አቆመ፤ እስከ ዛሬም የራሔል መቃብር ምልክት ይኸው ሐውልት ነው።

21እስራኤልም ጕዞውን በመቀጠል ከጋዴር ወንዝ ባሻገር ድንኳኑን ተከለ። 22እስራኤልም በዚያ ምድር ሳለ፣ ሮቤል ከአባቱ ቁባት ከባላ ጋር ተኛ፤ እስራኤልም ድርጊቱን ሰማ።

ያዕቆብ ዐሥራ ሁለት ልጆች ነበሩት፤ እነርሱም፦

23የልያ ልጆች፦

የያዕቆብ የበኵር ልጅ ሮቤል፣

ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፤

24የራሔል ልጆች፦

ዮሴፍ፣ ብንያም፤

25የራሔል አገልጋይ የባላ ልጆች፦

ዳን፣ ንፍታሌም፤

26የልያ አገልጋይ የዘለፋ ልጆች፦

ጋድ፣ አሴር ናቸው።

እነዚህ ያዕቆብ በሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ሳለ የተወለዱለት ወንዶች ልጆች ነበሩ።

27ያዕቆብ አባቱ ወዳለበት ወደ መምሬ መጣ፤ አብርሃምና ይስሐቅ የኖሩባት፣ ቂርያትአርባቅ ወይም ኬብሮን የተባለችው ቦታ ናት። 28ይስሐቅ መቶ ሰማንያ ዓመት ኖረ፤ 29አርጅቶ፣ ዕድሜ ጠግቦ ሞተ፤ ወደ ወገኖቹ ተሰበሰበ፤ ልጆቹም ዔሳውና ያዕቆብ ቀበሩት።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 35:1-29

ยาโคบกลับไปเบธเอล

1แล้วพระเจ้าตรัสกับยาโคบว่า “จงขึ้นไปยังเบธเอล แล้วตั้งถิ่นฐานที่นั่น และจงสร้างแท่นบูชาขึ้นที่นั่นถวายพระเจ้าผู้ทรงปรากฏแก่เจ้าเมื่อเจ้าหนีจากเอซาวพี่ชายของเจ้า”

2ดังนั้นยาโคบจึงกล่าวกับครอบครัวของเขาและทุกคนที่อยู่กับเขาว่า “จงกำจัดเทวรูปทั้งหลายที่พวกเจ้ามีอยู่ แล้วชำระตัวให้บริสุทธิ์ และเปลี่ยนเสื้อผ้า 3แล้วให้เราขึ้นไปยังเบธเอลที่เราจะสร้างแท่นบูชาขึ้นถวายแด่พระเจ้าผู้ทรงตอบคำอธิษฐานของเราในคราวทุกข์ยาก และได้สถิตกับเราตลอดมาในทุกหนทุกแห่งที่เราไป” 4คนเหล่านั้นจึงเอาเทวรูปทั้งหมดของตนและตุ้มหูมามอบให้ยาโคบ และยาโคบก็ฝังมันไว้ใต้สถานบูชาต้นไม้ใหญ่ที่เชเคม 5จากนั้นพวกเขาก็ออกเดินทางต่อ และชาวเมืองที่อยู่รอบๆ พวกเขาก็เกิดหวาดกลัวพระเจ้า จึงไม่มีใครไล่ตามพวกเขาไป

6ยาโคบกับคนทั้งหมดที่ร่วมทางได้มาถึงเมืองลูส (คือเบธเอล) ในแผ่นดินคานาอัน 7เขาสร้างแท่นบูชาขึ้นและเรียกที่นั่นว่าเอลเบธเอล35:7 แปลว่าพระเจ้าแห่งเบธเอล เพราะพระเจ้าทรงเปิดเผยพระองค์แก่เขาที่นั่นเมื่อครั้งที่เขาหนีจากพี่ชายของเขา

8ครั้งนั้นเดโบราห์พี่เลี้ยงของเรเบคาห์สิ้นชีวิตและถูกฝังไว้ใต้ต้นไม้ใหญ่ที่อยู่ทางใต้ของเบธเอล ที่นั่นจึงได้ชื่อว่าอัลโลนบาคูท35:8 แปลว่าต้นไม้ใหญ่แห่งการร้องไห้

9หลังจากยาโคบกลับมาจากจากปัดดานอารัม พระเจ้าทรงปรากฏแก่ยาโคบอีกครั้งหนึ่งและทรงอวยพรเขา 10พระเจ้าตรัสกับเขาว่า “เจ้าชื่อยาโคบ35:10 แปลว่าเขาจับส้นเท้า(เป็นสำนวนแปลว่าเขาหลอกลวง) แต่คนจะไม่เรียกเจ้าว่ายาโคบอีกต่อไป เจ้าจะได้ชื่อว่าอิสราเอล35:10 แปลว่าเขาปล้ำสู้กับพระเจ้า” ดังนั้นพระองค์จึงตั้งชื่อเขาว่าอิสราเอล

11แล้วพระเจ้าตรัสกับเขาว่า “เราเป็นพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์ เจ้าจงมีลูกมีหลานมากมายและทวีจำนวนขึ้น จะมีชนชาติหนึ่งและหมู่ประชาชาติเกิดมาจากเจ้า และกษัตริย์หลายองค์จะมาจากกายของเจ้า 12ดินแดนนี้ซึ่งเรายกให้แก่อับราฮัมและอิสอัค เราจะยกให้แก่เจ้าด้วย และเราจะให้ดินแดนนี้แก่ลูกหลานของเจ้าที่จะมาภายหลัง” 13แล้วพระเจ้าเสด็จขึ้นไปจากสถานที่ที่พระองค์ตรัสกับเขา

14ยาโคบจึงตั้งเสาหินตรงสถานที่ซึ่งพระเจ้าตรัสกับเขา แล้วเทเครื่องดื่มบูชาลงบนเสาและเทน้ำมันลงบนนั้นด้วย 15ยาโคบเรียกสถานที่ซึ่งพระเจ้าตรัสกับเขาว่าเบธเอล35:15 แปลว่าพระนิเวศของพระเจ้า

ราเชลและอิสอัคสิ้นชีวิต

(1พศด.2:1-2)

16จากนั้นพวกเขาเดินทางออกจากเบธเอล ขณะที่พวกเขาใกล้จะถึงเอฟราธาห์ ราเชลเริ่มเจ็บท้องคลอดและทรมานมาก 17ขณะที่กำลังทุรนทุรายอยู่นั้น นางผดุงครรภ์ก็ปลอบว่า “อย่ากลัวเลย เพราะเธอกำลังจะได้ลูกชายอีกคน” 18ขณะที่ราเชลกำลังจะสิ้นลมหายใจ นางตั้งชื่อลูกว่าเบนโอนี35:18 แปลว่าบุตรชายแห่งความทุกข์ระทมของเรา แต่ยาโคบเรียกเขาว่าเบนยามิน35:18 แปลว่าบุตรชายแห่งมือขวาของเรา

19ราเชลก็สิ้นชีวิตและถูกฝังไว้บนเส้นทางที่จะไปเอฟราธาห์ (คือเบธเลเฮม) 20ยาโคบปักเสาหินเหนือหลุมฝังศพของนางเป็นอนุสรณ์ซึ่งยังคงอยู่จนทุกวันนี้

21แล้วอิสราเอลก็เดินทางต่อไปอีกครั้ง และได้ตั้งเต็นท์ถัดจากมิกดัลเอเดอร์ 22ขณะอิสราเอลพักอยู่ในละแวกนั้น รูเบนก็ไปหลับนอนกับบิลฮาห์ภรรยาน้อยของบิดา และอิสราเอลก็ได้ทราบเรื่องนี้

ยาโคบมีบุตรชายสิบสองคน

23บุตรชายที่เกิดจากเลอาห์ ได้แก่

รูเบนบุตรชายหัวปีของยาโคบ สิเมโอน เลวี ยูดาห์ อิสสาคาร์ และเศบูลุน

24บุตรชายที่เกิดจากราเชล ได้แก่

โยเซฟและเบนยามิน

25บุตรชายที่เกิดจากบิลฮาห์สาวใช้ของราเชลได้แก่

ดานและนัฟทาลี

26บุตรชายที่เกิดจากศิลปาห์ สาวใช้ของเลอาห์ ได้แก่

กาดและอาเชอร์

ทั้งหมดนี้คือบุตรชายของยาโคบที่เกิดในปัดดานอารัม

27ยาโคบกลับบ้านมาหาอิสอัคบิดาของเขาที่มัมเรใกล้คีริยาทอารบา (คือเมืองเฮโบรน) ที่ซึ่งอับราฮัมกับอิสอัคได้อาศัยอยู่ 28อิสอัคมีอายุจนถึง 180 ปี 29แล้วอิสอัคก็สิ้นลมหายใจและถูกรวมไว้กับบรรพบุรุษของเขา เขาสิ้นชีวิตเมื่อชรามากแล้ว เอซาวกับยาโคบผู้เป็นบุตรก็จัดการฝังศพบิดา