ዘፍጥረት 30 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 30:1-43

1ራሔል ለያዕቆብ አንድም ልጅ እንዳልወለደችለት ባየች ጊዜ በእኅቷ ቀናች። ስለዚህ ያዕቆብን፣ “ልጅ ስጠኝ፤ አለዚያ እሞታለሁ” አለችው።

2ያዕቆብም ራሔልን ተቈጥቶ “እኔ እንዳትወልጂ ያደረገሽን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) መሰልኹሽን?” አላት።

3እርሷም፣ “እነሆ፤ አገልጋዬ ባላ አለችልህ፤ ልጆች እንድትወልድልኝና እኔም ደግሞ በእርሷ አማካይነት ልጆች እንዳገኝ ከእርሷ ጋር ተኛ” አለችው።

4ስለዚህም አገልጋይዋን ባላን ሚስት እንድትሆነው ሰጠችው፤ ያዕቆብም አብሯት ተኛ፤ 5እርሷም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደችለት። 6ራሔልም፣ “እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ፈርዶልኛል፣ ልመናዬንም ሰምቶ ወንድ ልጅ ሰጥቶኛል” አለች። ስለዚህ ስሙን ዳን ብላ አወጣችለት።

7የራሔል አገልጋይ ባላ እንደ ገና ፀነሰች፤ ለያዕቆብም ሁለተኛ ወንድ ልጅ ወለደች። 8ራሔልም፣ “እኅቴን ብርቱ ትግል ገጥሜ አሸነፍሁ” አለች፤ ስሙንም ንፍታሌም ብላ አወጣችለት።

9ልያም ልጅ መውለድ ማቆሟን እንደ ተረዳች፣ አገልጋይዋን ዘለፋን ሚስት እንድትሆነው ለያዕቆብ ሰጠችው። 10የልያ አገልጋይ ዘለፋም ለያዕቆብ ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ 11ልያም፣ “ምን ዐይነት መታደል30፥11 ወይም ጭፍራ እየመጣ ነው። ነው” አለች፤ ስሙንም ጋድ30፥11 ጋድ ማለት መልካም ዕድል ወይም ሰራዊት ማለት ነው። ብላ አወጣችለት።

12የልያም አገልጋይ ዘለፋ፤ ለያዕቆብ ሁለተኛ ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ 13ልያም፣ “ምንኛ ደስተኛ ሆንሁ ከእንግዲህ ሴቶች ደስተኛዋ ይሉኛል” አለች፤ ስሙንም አሴር30፥13 አሴር ማለት ደስተኛ ማለት ነው። ብላ አወጣችለት። 14ስንዴ በሚታጨድበት ወቅት፣ ሮቤል ወደ ሜዳ ወጣ፤ እንኮይም አግኝቶ ለእናቱ ለልያ አመጣላት። ራሔልም ልያን፣ “እባክሽን ልጅሽ ካመጣልሽ እንኮይ ስጪኝ” አለቻት።

15ልያም፣ “ባሌን የቀማሽኝ አነሰና የልጄን እንኮይ ደግሞ ልትወስጂ አማረሽ?” አለቻት።

ራሔልም፣ “ስለ ልጅሽ እንኮይ ዛሬ ከአንቺ ጋር ይደር” አለቻት።

16በዚያች ምሽት ያዕቆብ ከዕርሻ ሲመለስ፣ ልያ ወጥታ ተቀበለችውና፣ “በልጄ እንኮይ ስለ ተከራየሁህ የዛሬው ዐዳርህ ከእኔ ጋር ነው” አለችው፤ ያዕቆብም በዚያች ሌሊት ከእርሷ ጋር ዐደረ።

17እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የልያን ጸሎት ሰማ፤ ፀነሰች፤ ለያዕቆብም አምስተኛውን ወንድ ልጅ ወለደች። 18ልያም፣ “አገልጋዬን ለባሌ በመስጠቴ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ክሶኛል” አለች፤ ስሙንም ይሳኮር30፥18 ይሳኮር የሚለው ቃል ሽልማት የሚል ትርጕም ካለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር አንድ ዐይነት ድምፅ አለው። ብላ አወጣችለት።

19ልያ አሁንም ደግማ ፀነሰች፤ ለያዕቆብም ስድስተኛውን ወንድ ልጅ ወለደች። 20እርሷም፣ “እግዚአብሔር (ኤሎሂም) በከበረ ስጦታ ዐድሎኛል፣ ስድስት ወንዶች ልጆች ስለ ወለድሁለት፣ ከእንግዲህ ባሌ አክብሮ ይይዘኛል”። አለች፤ ስሙንም ዛብሎን30፥20 ዛብሎን ማለት ማክበር ማለት ነው። አለችው።

21ከዚያም በኋላ ሴት ልጅ ወለደች፤ ስሟንም ዲና አለቻት።

22እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ራሔልን ዐሰባት፤ ልመናዋንም ሰምቶ ማሕፀኗን ከፈተላት። 23ከዚያም ፀንሳ፣ ወንድ ልጅ ወለደችና “እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ዕፍረቴን አስወገደልኝ” አለች፤ 24ስሙንም፣ “እግዚአብሔር (ይህዌ) ሌላ ወንድ ልጅ ጨምሮ ይስጠኝ” ስትል፣ ዮሴፍ30፥24 ዮሴፍ ማለት እርሱ ይጨምር ማለት ነው። አለችው።

የያዕቆብ መንጎች መብዛት

25ራሔል ዮሴፍን ከወለደች በኋላ ያዕቆብ ላባን እንዲህ አለው፤ “ወደ ገዛ ቤቴ፣ ወደ አገሬ እንድመለስ አሰናብተኝ፤ 26የድካሜ ዋጋ የሆኑትን ሚስቶቼንና ልጆቼን ስጠኝና ይዤአቸው ልሂድ፤ መቼም የቱን ያህል እንዳገለገልሁህ ታውቃለህ” አለው።

27ላባም እንዲህ አለው፤ “በጎ ፈቃድህ ቢሆን፣ እባክህ እዚሁ ከእኔ ጋር ተቀመጥ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔርም (ያህዌ) በአንተ ምክንያት እንደ ባረከኝ በንግርት ተረድቻለሁ፤30፥27 ወይም እየበለጸግሁና እግዚአብሔርም በአንተ ምክንያት እየባረከኝ ነው 28ይልቅስ ይገባኛል የምትለውን ደመወዝ ንገረኝና እከፍልሃለሁ።”

29ያዕቆብም እንዲህ አለው፤ “መቼም እንዴት እንዳገለገልሁህ፣ ከብቶችህ በእኔ ጥበቃ ምን ያህል እንደ ተመቻቸው አንተ ታውቃለህ። 30እኔ ከመምጣቴ በፊት ጥቂት የነበረው ሀብትህ ዛሬ ተትረፍርፏል፣ በተሰማራሁበት ሁሉ እግዚአብሔር (ያህዌ) በረከቱን አብዝቶልሃል። ታዲያ፣ ስለ ራሴ ቤት የማስበው መቼ ነው?”

31ላባም፣ “ታዲያ ምን ልስጥህ?” ሲል ጠየቀው።

ያዕቆብም መልሶ እንዲህ አለው፤ “ምንም አትስጠኝ፤ ነገር ግን የምጠይቅህን አንዲት ነገር ብቻ ብታደርግልኝ ከብቶችህን ማገዴን እቀጥላለሁ፤ 32በመንጎቹ መካከል ዛሬ ልዘዋወርና ከበጎቹ መካከል ዝንጕርጕር የሆኑትን፣ ነቍጣ ያለባቸውንና ጥቋቁሮቹን እንዲሁም ከፍየሎቹ ነቍጣ ያለባቸውንና ዝንጕርጕሮቹን ልምረጥ፤ እነዚህ ደሞዜ ይሁኑ። 33ወደ ፊት ደሞዜን ለመቈጣጠር በምትመጣበት ጊዜ ታማኝነቴ ይታወቃል፤ በመንጎቼ መካከል ዝንጕርጕር ወይም ነቍጣ የሌለበት ፍየል ወይም ጥቁር ያልሆነ ቢገኝ ያ እንደ ተሰረቀ ይቈጠር።”

34ላባም፣ “እሺ፣ ይሁን፤ ባልኸው ተስማምቼአለሁ” አለው። 35ነገር ግን በዚያኑ ዕለት ከተባዕት ፍየሎች ሽመልመሌ የሆኑትን ወይም ነቍጣ ያለባቸውን ሁሉ፣ እንዲሁም ከእንስት ፍየሎች ነቍጣ ያለባቸውን ዝንጕርጕር የሆኑትን ሁሉ፣ ማንኛውንም ነጭ ያለበትን ሁሉ መረጠ፤ ደግሞም ጥቋቁር የሆኑትንም በጎች ሁሉ ለየና ወንዶች ልጆቹን አስጠበቃቸው። 36ከዚያም በእርሱና በያዕቆብ መካከል የሦስት ቀን መንገድ ርቀት እንዲኖር አደረገ፤ ያዕቆብም የቀሩትን የላባን መንጎች ማገዱን ቀጠለ።

37ነገር ግን ያዕቆብ እርጥብ የልብን፣ የለውዝንና የኤርሞን በትሮች ወሰደ፤ ቅርፊታቸውንም በቀጭን ልጦ እያነሣ የበትሮቹ ግንድ ነጩ እንዲታይ፣ ሽመልመሌ መልክ እንዲኖራቸው አደረገ። 38የላጣቸውንም በትሮች መንጎቹ ውሃ ለመጠጣት ሲመጡ ከፊት ለፊት እንዲያዩአቸው በማጠጫ ገንዳዎቹ ሁሉ አስቀመጠ። መንጎቹም ስሜታቸው ሲነሣሣና ውሃ ለመጠጣት ሲመጡ፣ 39በትሮቹን ፊት ለፊት እያዩ ይሳረሩ ነበር፤ ሽመልመሌ፣ ዝንጕርጕርና ነቍጣ የጣለባቸውንም ግልገሎች ወለዱ። 40ያዕቆብ ግልገሎቹን ለብቻ ለያቸው፤ የቀሩትንም የላባ መንጎች ሽመልመሌና ጥቋቁር በሆኑት ትይዩ አቆማቸው፤ በዚህም መሠረት የራሱ መንጋ ከላባ መንጋ ጋር እንዳይቀላቀል ለብቻ ለየ። 41ያዕቆብም ብርቱ እንስቶች አውራ ፈልገው በሚቅበጠበጡበት ጊዜ፣ በትሮቹ አቅራቢያ እንዲጠቁ በትሮቹን በውሃ ገንዳዎቹ ውስጥ ፊት ለፊታቸው ያስቀምጥ ነበር፤ 42ደካማ በሆኑት እንስቶች ፊት ግን፣ በትሮቹን አያስቀምጥም ነበር፤ ስለዚህ ደካማ ደካማዎቹ ለላባ ሲሆኑ፣ ብርቱ ብርቱዎቹ ለያዕቆብ ሆኑ። 43በዚህም ሁኔታ ይህ ሰው እጅግ ባለጠጋ ሆነ፤ የብዙ መንጎች፣ የሴትና የወንድ አገልጋዮች፣ እንዲሁም የግመሎችና የአህዮች ባለቤት ሆነ።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 30:1-43

1เมื่อราเชลเห็นว่าตนไม่มีบุตรให้ยาโคบก็อิจฉาพี่สาว ดังนั้นนางจึงกล่าวกับยาโคบว่า “จงให้ลูกแก่ฉัน ไม่อย่างนั้นฉันตายดีกว่า!”

2ยาโคบจึงโกรธนางและพูดว่า “ฉันอยู่ในฐานะพระเจ้าผู้ทรงไม่ให้เธอมีลูกหรือ?”

3นางจึงพูดว่า “นางบิลฮาห์สาวใช้ของฉันอยู่ที่นี่ จงหลับนอนกับนางเพื่อฉันจะได้รับลูกนางมาเป็นลูกฉัน และฉันเองก็จะสามารถสร้างครอบครัวขึ้นได้โดยอาศัยนาง”

4ดังนั้นนางจึงยกบิลฮาห์สาวใช้ของนางให้เป็นภรรยาของยาโคบ เขาก็หลับนอนกับบิลฮาห์ 5นางได้ตั้งครรภ์และให้กำเนิดบุตรชายคนหนึ่งแก่เขา 6แล้วราเชลกล่าวว่า “พระเจ้าทรงตัดสินให้ฉันชนะ พระองค์ทรงสดับฟังคำวิงวอนของฉันและประทานลูกชายแก่ฉัน” เพราะเหตุนี้นางจึงตั้งชื่อเขาว่าดาน30:6 ในที่นี้แปลว่าพระองค์ทรงตัดสิน

7แล้วบิลฮาห์สาวใช้ของราเชลก็ตั้งครรภ์อีกครั้งหนึ่งและคลอดบุตรชายคนที่สองให้แก่ยาโคบ 8แล้วราเชลกล่าวว่า “ฉันได้ต่อสู้กับพี่สาวอย่างหนักมาตลอดและฉันก็ชนะแล้ว” ดังนั้นนางจึงตั้งชื่อเขาว่านัฟทาลี30:8 แปลว่าการต่อสู้ของฉัน

9เมื่อเลอาห์เห็นว่าตนไม่มีลูกอีก จึงยกศิลปาห์สาวใช้ของตนให้เป็นภรรยาของยาโคบ 10ศิลปาห์ให้กำเนิดบุตรชายคนหนึ่งแก่ยาโคบ 11แล้วเลอาห์กล่าวว่า “โชคดีอะไรอย่างนี้!”30:11 หรือ“กองทหารกำลังมา! ดังนั้นนางจึงตั้งชื่อเขาว่ากาด30:11กาดแปลว่าโชคดีหรือกองทหารก็ได้

12แล้วศิลปาห์สาวใช้ของเลอาห์ก็ให้กำเนิดบุตรชายคนที่สองแก่ยาโคบ 13แล้วเลอาห์กล่าวว่า “ฉันสุขใจจริงๆ! พวกผู้หญิงจะเรียกฉันว่าเป็นสุข” ดังนั้นนางจึงตั้งชื่อเขาว่าอาเชอร์30:13 แปลว่าเป็นสุข

14วันหนึ่งในฤดูเก็บเกี่ยวข้าวสาลี รูเบนออกไปที่ทุ่งนาและพบต้นดูดาอิม30:14 เป็นพืชที่เชื่อกันว่ากินแล้วจะช่วยให้ตั้งท้องและเพิ่มความต้องการทางเพศ จึงนำมาให้เลอาห์ผู้เป็นมารดา ราเชลพูดกับเลอาห์ว่า “ขอดูดาอิมของลูกชายพี่ให้ฉันบ้างเถิด”

15แต่เลอาห์ตอบนางว่า “เจ้าเอาสามีของฉันไปยังไม่พออีกหรือ? แล้วยังจะมาเอาดูดาอิมของลูกฉันอีกหรือ?”

ราเชลกล่าวว่า “เอาอย่างนี้ก็แล้วกัน ให้ยาโคบไปนอนกับพี่คืนนี้ได้ แลกกับดูดาอิมของลูกชายพี่”

16เย็นวันนั้นเมื่อยาโคบกลับมาจากทุ่งนา เลอาห์ก็ออกไปพบและพูดว่า “ท่านต้องมานอนกับฉัน เพราะฉันเอาดูดาอิมของลูกเป็นสินจ้างแล้ว” คืนวันนั้นยาโคบก็นอนกับนาง

17พระเจ้าทรงฟังเลอาห์ นางก็ตั้งครรภ์และให้กำเนิดบุตรชายคนที่ห้า 18แล้วเลอาห์กล่าวว่า “พระเจ้าประทานรางวัลให้ฉันเพราะฉันได้ยกสาวใช้ให้สามี” ดังนั้นนางจึงตั้งชื่อเขาว่าอิสสาคาร์30:18 คำว่าอิสสาคาร์มีเสียงคล้ายคำภาษาฮีบรูที่มีความหมายว่ารางวัล

19เลอาห์ได้ตั้งครรภ์อีกและคลอดบุตรชายคนที่หกให้แก่ยาโคบ 20แล้วเลอาห์กล่าวว่า “พระเจ้าประทานของขวัญล้ำค่าแก่ฉัน คราวนี้สามีจะยกย่องฉัน เพราะฉันคลอดลูกชายให้แก่เขาถึงหกคน” ดังนั้นนางจึงตั้งชื่อเขาว่าเศบูลุน30:20 คงจะมีความหมายว่าเกียรติ

21ต่อมาภายหลัง นางได้คลอดบุตรสาวคนหนึ่งและตั้งชื่อว่าดีนาห์

22แล้วพระเจ้าทรงระลึกถึงราเชล พระองค์ทรงฟังนางและให้นางมีบุตร 23นางตั้งครรภ์และให้กำเนิดบุตรชายคนหนึ่ง นางกล่าวว่า “พระเจ้าทรงลบล้างความอับอายของฉันแล้ว” 24นางตั้งชื่อเขาว่าโยเซฟ30:24 แปลว่าขอพระองค์ทรงเพิ่ม และกล่าวว่า “ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเพิ่มลูกชายให้ฉันอีกคนหนึ่ง”

ฝูงสัตว์ของยาโคบเพิ่มจำนวนขึ้น

25หลังจากราเชลให้กำเนิดโยเซฟ ยาโคบพูดกับลาบันว่า “อนุญาตให้ฉันไปตามทางของฉันเถิด เพื่อฉันจะได้กลับไปบ้านเกิดเมืองนอน 26จงมอบภรรยาและลูกๆ ทั้งหมดให้ฉันด้วย เพราะฉันได้รับใช้ท่านแลกกับพวกเขาแล้ว และฉันก็จะได้ไปตามทางของฉัน ท่านก็รู้ว่าฉันทำงานให้ท่านมากเพียงใด”

27แต่ลาบันกล่าวกับเขาว่า “หากท่านจะกรุณาเรา โปรดอยู่ต่อเถิด เรารู้จากคำทำนายว่า30:27 หรืออาจแปลได้ว่าเราได้ร่ำรวยขึ้นและองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรเราเพราะท่าน” 28เขายังกล่าวเสริมอีกว่า “ท่านจะเรียกค่าจ้างเท่าไรก็บอกมาเถิด เราจะจ่ายให้”

29ยาโคบกล่าวกับเขาว่า “ท่านก็รู้ว่าฉันได้รับใช้ท่านอย่างไร และฝูงแพะแกะในความดูแลของฉันได้รับการเลี้ยงดูอย่างดีเพียงไร 30ที่ท่านมีอยู่เล็กน้อยก่อนที่ฉันจะมา เดี๋ยวนี้เพิ่มขึ้นมหาศาล และไม่ว่าฉันจะทำอะไร องค์พระผู้เป็นเจ้าก็ทรงอวยพรท่าน แต่เมื่อไรฉันจึงจะได้ทำอะไรเพื่อครัวเรือนของตนเองบ้าง?”

31ลาบันถามว่า “เราควรให้อะไรท่านดี?”

ยาโคบตอบว่า “ไม่ต้องให้อะไรฉันหรอก ฉันจะเลี้ยงและดูแลฝูงสัตว์ให้ท่านต่อไป ถ้าท่านจะตกลงกับฉันสักอย่างหนึ่ง 32คือในวันนี้ให้ฉันออกไปสำรวจฝูงสัตว์ของท่านดู แล้วแยกแกะที่มีลายด่าง ลูกแกะสีคล้ำ และแพะที่มีลายด่างทุกตัวออกจากฝูง สัตว์เหล่านี้ถือเป็นค่าจ้างของฉัน 33และนี่จะเป็นพยานถึงความซื่อสัตย์ของฉันในอนาคต คือทุกครั้งที่ท่านตรวจดูค่าจ้างที่จ่ายให้ฉัน หากพบว่าแพะตัวใดในกรรมสิทธิ์ของฉันไม่มีลายด่าง หรือลูกแกะตัวใดไม่มีสีคล้ำก็ให้ถือว่าฉันขโมยมา”

34ลาบันตอบว่า “ตกลง ให้เป็นตามที่เจ้าว่าไว้” 35ในวันนั้นเองลาบันก็ออกไปคัดแพะทั้งตัวผู้และตัวเมียทุกตัวที่มีลายด่างออกมา (ทุกตัวที่มีสีขาวอยู่ด้วย) ตลอดจนลูกแกะสีคล้ำทุกตัวออกจากฝูง แล้วนำไปให้บรรดาบุตรชายของเขาเลี้ยง 36แล้วเขาให้ฝูงแพะแกะของเขากับของยาโคบอยู่ห่างกันเป็นระยะเวลาเดินทางสามวัน ในขณะที่ยาโคบยังเลี้ยงฝูงสัตว์ที่เหลือให้ลาบันต่อไป

37อย่างไรก็ตามยาโคบเอากิ่งไม้สดๆ จากต้นปอปลาร์ ต้นอัลมอนด์ และต้นเปลนมาลอกเปลือกออกเป็นริ้วให้เห็นเนื้อไม้สีขาวข้างใน 38แล้วเขาวางกิ่งไม้ที่ลอกเปลือกไว้ที่รางน้ำทุกรางเพื่อให้อยู่ตรงหน้าฝูงแพะแกะเวลาที่มันมากินน้ำ ทุกครั้งที่ฝูงแพะแกะเป็นสัดและมากินน้ำ 39มันก็ผสมพันธุ์กันหน้ากิ่งไม้นั้น ลูกที่เกิดมาจึงมีลายริ้ว ลายด่าง หรือลายจุด 40ยาโคบก็แยกลูกสัตว์เหล่านั้นไว้ต่างหาก แล้วให้ฝูงสัตว์ที่เหลือหันไปทางสัตว์ที่มีลายด่างหรือสัตว์ที่มีสีคล้ำของลาบัน โดยวิธีนี้เองเขาจึงสร้างฝูงแพะแกะของตนเองขึ้นและไม่ได้รวมไว้กับฝูงสัตว์ของลาบัน 41เมื่อใดก็ตามที่บรรดาตัวเมียที่แข็งแรงเป็นสัด ยาโคบก็เอากิ่งไม้ที่ลอกเปลือกไปวางไว้ในรางน้ำตรงหน้าสัตว์นั้น ให้มันผสมพันธุ์กันใกล้กิ่งไม้นั้น 42แต่ถ้าสัตว์ตัวใดอ่อนแอ เขาก็ไม่เอากิ่งไม้ไปวางไว้ที่นั่น ดังนั้นสัตว์ที่อ่อนแอก็เป็นของลาบัน ส่วนตัวที่แข็งแรงเป็นของยาโคบ 43ด้วยวิธีนี้เอง เขาจึงร่ำรวยขึ้นอย่างมากและกลายเป็นเจ้าของสัตว์ฝูงใหญ่ มีคนรับใช้ชายหญิงจำนวนมาก และมีอูฐมีลาอีกมากมาย