ዘፍጥረት 31 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 31:1-55

ያዕቆብ ከላባ ቤት ኰበለለ

1የላባ ወንዶች ልጆች፣ “ያዕቆብ የአባታችንን ሀብት እንዳለ ወስዶታል፤ ይህ ሁሉ እርሱ ያካበተውም ሀብት ከአባታችን የተገኘ ነው” እያሉ ሲያወሩ ያዕቆብ ሰማ። 2የላባ አመለካከት ከቀድሞው የተለወጠበት መሆኑንም ያዕቆብ ተረዳ።

3እግዚአብሔርም (ያህዌ) ያዕቆብን፣ “ወደ አባቶችህና ዘመዶችህ አገር ተመለስ፤ እኔም ካንተ ጋር እሆናለሁ” አለው።

4ስለዚህም ያዕቆብ መንጎቹ ወደ ተሰማሩበት መስክ እንዲመጡ፣ ራሔልንና ልያን አስጠራቸው፤ 5እንዲህም አላቸው፤ “አባታችሁ ስለ እኔ ያለው አመለካከት እንደ ቀድሞው አለመሆኑን ተረድቻለሁ፤ ቢሆንም የአባቴ አምላክ (ኤሎሂም) አልተለየኝም፤ 6መቼም ባለኝ ዐቅም አባታችሁን ማገልገሌ ከእናንተ የተሰወረ አይደለም። 7አባታችሁ ደሞዜን ዐሥር ጊዜ እየለዋወጠ አታልሎኛል፣ ሆኖም እንዲጐዳኝ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አልፈቀደለትም። 8እርሱ፣ ‘ደመወዝህ ዝንጕርጕሮቹ ይሆናሉ’ ሲለኝ፣ መንጎቹ ሁሉ ዝንጕርጕር ወለዱ፤ ደግሞም ‘ደመወዝህ ሽመልመሌዎቹ ይሆናሉ’ ሲለኝ፣ መንጎቹ ሁሉ ሽመልመሌ መልክ ያላቸውን ወለዱ፤ 9ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የአባታችሁን ከብቶች ወስዶ ለእኔ ሰጠኝ።

10“እንስሳቱ በሚጠቁበት ወራት፣ የሚያጠቋቸው አውራ ፍየሎች መልካቸው፣ ሽመልመሌ፣ ዝንጕርጕርና ነቍጣ ያለባቸው መሆናቸውን ዐይኔን አንሥቼ በሕልሜ አየሁ። 11የእግዚአብሔርም (ኤሎሂም) መልአክ፣ ‘ያዕቆብ’ አለኝ፤ እኔም፣ ‘እነሆ አለሁኝ’ አልሁት። 12እርሱም ‘መንጎቹን የሚያጠቋቸው አውራ ፍየሎች ሁሉ ሽመልመሌ መልክ ያላቸው፣ ዝንጕርጕርና ነቍጣ ያለባቸው መሆናቸውን ቀና ብለህ ተመልከት፤ ላባ በአንተ ላይ የሚፈጽመውን ድርጊት ሁሉ አይቻለሁና፤ 13የድንጋይ ሐውልት በማቆም ዘይት ቀብተህ የተሳልህባት የቤቴል አምላክ (ኤል) እኔ ነኝ፤ አሁንም ይህን አገር ፈጥነህ ልቀቅና ወደ ተወለድህበትም ምድር ተመልሰህ ሂድ’ አለኝ።”

14ራሔልና ልያም እንዲህ ብለው መለሱለት፤ “ከአባታችን ሀብት የምናገኘው ምን ውርስ አለ? 15እኛን የሚያየን እንደ ባዕድ አይደለምን? ደግሞም እኮ እኛን ሸጦናል፤ የተሸጥንበትንም ዋጋ ራሱ በልቶታል። 16እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ከአባታችን ወስዶ ለአንተ የሰጠው ሀብት ሁሉ የእኛና የልጆቻችን ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የነገረህን ሁሉ አድርግ።”

17ከዚያም ያዕቆብ ልጆቹንና ሚስቶቹን ግመሎች ላይ አስቀመጠ፤ 18በመስጴጦምያ ካፈራው ሀብት ሁሉ ጋር ከብቶቹን በሙሉ ወደ ፊት አስቀደመ፤ ወደ አባቱም ወደ ይስሐቅ አገር፣ ወደ ከነዓን ምድር ጕዞውን ቀጠለ።

19ላባ በጎቹን ሊሸልት ሄዶ ሳለ፣ ራሔል የአባቷን ቤት የጣዖታት ምስል ሰረቀች።

20ያዕቆብም ቢሆን፣ መኰብለሉን ለሶርያዊው ለላባ ሳይገልጥለት በመቅረቱ አታልሎታል። 21ያዕቆብ የእርሱ የሆነውን ሁሉ ይዞ፣ የኤፍራጥስን ወንዝ ተሻግሮ ወደ ኰረብታማው አገር፣ ወደ ገለዓድ አመራ።

ላባ ያዕቆብን ተከታተለው

22የያዕቆብ መኰብለል ለላባ በሦስተኛው ቀን ተነገረው። 23ላባ ዘመዶቹን ይዞ ተነሣ፤ ያዕቆብንም ሰባት ቀን ተከታትሎ ገለዓድ በተባለ ኰረብታማ አገር ደረሰበት። 24ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ለሶርያዊው ለላባ በሕልም ተገልጦ፣ “ያዕቆብን፣ ክፉም ሆነ ደግ፣ እንዳትናገረው ተጠንቀቅ” አለው።

25ያዕቆብ ገለዓድ በተባለው ኰረብታማ አገር ድንኳኑን ተክሎ ሳለ፣ ላባ ደረሰበት፤ ላባና ዘመዶቹም በዚያው ሰፈሩ። 26ከዚያም ላባ ያዕቆብን እንዲህ አለው፤ “ምን ማድረግህ ነው? አታልለኸኛል፤ ልጆቼን የጦር ምርኮኛ ይመስል አካልበህ ወሰድሃቸው። 27ለመሆኑ ለምን ተደብቀህ ሄድህ? ለምንስ አታለልኸኝ? ብትነግረኝ ኖሮ፣ በደስታና በዘፈን በከበሮና በበገና አልሸኝህም ነበር? 28የልጆቼን ልጆችና ልጆቼንም ስሜ ብሰናበት ምን ነበረበት? የሠራኸው የጅል ሥራ ነው። 29ልጐዳችሁ እችል ነበር፤ ዳሩ ግን ባለፈው ሌሊት የአባታችሁ አምላክ (ኤሎሂም) ‘ያዕቆብን፣ ክፉም ሆነ ደግ እንዳትናገረው ተጠንቀቅ’ አለኝ። 30አንተ ወደ አባትህ ቤት ለመመለስ ስለ ናፈቅህ ሄደሃል፤ ነገር ግን የቤቴን የጣዖት ምስል የሰረቅኸው ለምንድን ነው?”

31ያዕቆብም ለላባ እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “ሴቶች ልጆችህን በኀይል ነጥቀህ ታስቀርብኛለህ ብዬ ስለ ፈራሁ ነው። 32ነገር ግን ከእኛ መካከል የአንተን የጣዖታት ምስል ደብቆ የተገኘ ሰው ካለ ይሙት። ያንተ የሆነ አንዳች ነገር ከኔ ዘንድ ቢገኝ፣ አንተው ራስህ ዘመዶቻችን ባሉበት ፈልግና ውሰድ።” ይህን ሲል፣ ራሔል የጣዖታቱን ምስል መስረቋን ያዕቆብ አያውቅም ነበር።

33ላባም ወደ ያዕቆብ፣ ድንኳንና ወደ ልያ ድንኳን እንዲሁም ወደ ሁለቱ ደንገጡሮቿ ድንኳኖች ገባ፤ ነገር ግን ምንም አላገኘም። ከልያ ድንኳን ከወጣ በኋላ ወደ ራሔል ድንኳን ገባ። 34ራሔል የጣዖታቱን ምስል ከግመሏ ኮርቻ ሥር ሸሽጋ፣ በላዩ ተቀምጣበት ነበር፤ ላባም ድንኳኑን አንድ በአንድ በርብሮ ምንም ሊያገኝ አልቻለም።

35ራሔልም አባቷን፣ “በፊትህ ተነሥቼ መቆም ስላልቻልሁ፣ ጌታዬ አትቈጣ፤ የወር አበባዬ መጥቶ ነው።” አለችው፤ ስለዚህ በረበረ፤ የጣዖታቱን ምስል ግን ማግኘት አልቻለም።

36በዚህ ጊዜ ያዕቆብ ተቈጣ፤ ላባንም እንዲህ ሲል ወቀሠው፤ “እስቲ ወንጀሌ ምንድን ነው? ይህን ያህል የምታሳድደኝ ኀጢአቴ ምን ቢሆን ነው? 37ዕቃዬን አንድ በአንድ በርብረሃል፤ ታዲያ፣ የአንተ ሆኖ ያገኘኸው ዕቃ የትኛው ነው? ካለ፣ እስቲ በአንተም በእኔም ዘመዶች ፊት አቅርብና እነርሱ ያፋርዱን።

38“ሃያ ዓመት አብሬህ ኖሬአለሁ፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከመንጋህ አንድ ጠቦት እንኳ አልበላሁም። 39አውሬ የሰበረውንም ቢሆን እተካ ነበር እንጂ፣ ትራፊውን ለምልክትነት አምጥቼ አላውቅም፤ በቀንም ሆነ በሌሊት የተሰረቁትን ሁሉ ስታስከፍለኝ ኖረሃል። 40ቀን በሐሩር ሌሊት በቍር ተቃጠልሁ፤ እንቅልፍም በዐይኔ አልዞር አለ፤ 41ሃያ ዓመት በቤትህ የኖርሁት በዚህ ሁኔታ ነበር፤ ዐሥራ አራት ዓመት ለሁለቱ ልጆችህ ብዬ አገለገልሁ፤ ስድስት ዓመት ስለ መንጋዎችህ ስል አገለገልሁ፤ ይህም ሆኖ ደመወዜን ዐሥር ጊዜ ለዋውጠህብኛል። 42የአባቴ አምላክ (ኤሎሂም)፣ የአብርሃም አምላክ (ኤሎሂም)፣ የይስሐቅም ፍርሀት ከእኔ ጋር ባይሆን ኖሮ ባዶ እጄን ሰድደኸኝ ነበር፤ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ግን መከራዬን አይቶ፣ ልፋቴን ተመልክቶ ትናንት ሌሊት ገሠጸህ።”

43ላባም ለያዕቆብ እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “ሴቶቹም፣ ልጆቹም የእኔው ልጆች ናቸው፣ መንጎቹም ቢሆኑ የራሴ ናቸው። ታዲያ፣ በእነዚህ ሴቶች ልጆቼና በወለዷቸው ልጆቻቸው ላይ ዛሬ ምን ማድረግ እችላለሁ? 44በል አሁን ቃል ኪዳን እንጋባ፤ ኪዳኑም በአንተና በእኔ መካከል ምስክር ይሁን።”

45ያዕቆብም ድንጋይ ወስዶ ሐውልት አድርጎ አቆመው፤ 46ከዚያም ዘመዶቹን፣ “ድንጋይ ሰብስቡ” አላቸው። እነርሱም ድንጋይ እያመጡ ከመሩ፤ በክምሩም አጠገብ ምግብ በሉ። 47ላባም ክምር ድንጋዩን ይጋርሠሀዱታ31፥47 ይጋርሠሀዱታ የሚለው ቃል በአረማይክ የኪዳን ክምር ድንጋይ ማለት ነው። ብሎ ጠራው፤ ያዕቆብ ደግሞ ገለዓድ31፥47 ገለዓድ የሚለው ቃል በዕብራይስጥ የኪዳን ክምር ድንጋይ ማለት ነው። አለው።

48ላባም “ይህ ክምር ድንጋይ በእኔና በአንተ መካከል ዛሬ ምስክር ነው” አለው። ገለዓድ ተብሎ የተጠራውም በዚሁ ምክንያት ነው፤ 49ደግሞም ምጽጳ31፥49 ምጽጳ የሚለው ቃል መጠበቂያ ማማ ማለት ነው። ተባለ፤ ምክንያቱም ላባ እንዲህ ብሏልና፤ “እኛ በተለያየን ጊዜ፣ እግዚአብሔር በእኔና በአንተ መካከል ታዛቢ ሆኖ ይቁም። 50ልጆቼን ብትበድላቸው ወይም ሌሎች ሚስቶች በላያቸው ላይ ብታገባ፣ ማንም ከእኛ ጋር ባይኖርም እንኳ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) በአንተና በእኔ መካከል ምስክር መሆኑን አትርሳ።”

51ደግሞም ላባ ያዕቆብን እንዲህ አለው፤ “ክምር ድንጋዩ እነሆ፤ በአንተና በእኔ መካከል ያቆምሁትም ሐውልት እነሆ፤ 52ይህን ክምር ድንጋይ ዐልፌ አንተን ለማጥቃት ላልመጣ፣ አንተም ይህን ክምር ድንጋይና ይህን ሐውልት ዐልፈህ እኔን ለማጥቃት ላትመጣ፣ ይህ ክምር ድንጋይ ምስክር ነው፤ ይህም ሐውልት ምስክር ነው። 53የአብርሃም አምላክ፣ የናኮር አምላክ፣ የአባታቸውም አምላክ (ኤሎሂም) በመካከላችን ይፍረድብን”።

ስለዚህ ያዕቆብ በአባቱ በይስሐቅ ፍርሀት ማለ። 54ያዕቆብ በኰረብታማው አገር ላይ መሥዋዕት አቀረበ፤ ዘመዶቹንም ምግብ እንዲበሉ ጋበዛቸው፤ እነርሱም ከበሉ በኋላ እዚያው ዐደሩ።

55በማግስቱም ማለዳ ላባ የልጅ ልጆቹን እንዲሁም ሴቶች ልጆቹን ስሞ መረቃቸው፤ ከዚያም ወደ አገሩ ተመለሰ።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 31:1-55

ยาโคบหนีไปจากลาบัน

1ยาโคบได้ยินลูกๆ ของลาบันพูดกันว่า “ยาโคบเอาทุกสิ่งที่เป็นของพ่อเราไป ที่เขาร่ำรวยขึ้นมาทั้งหมดนี้ก็ได้มาจากสิ่งที่เป็นของพ่อของเราแท้ๆ” 2และยาโคบสังเกตว่าลาบันเมินหน้าหนีตนซึ่งต่างไปจากแต่ก่อน

3แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับยาโคบว่า “จงกลับไปยังดินแดนของบิดาของเจ้า ไปหาญาติพี่น้องของเจ้า และเราจะอยู่กับเจ้า”

4ยาโคบจึงให้คนไปตามราเชลกับเลอาห์ออกมาพบเขาที่ทุ่งซึ่งเขาเลี้ยงสัตว์อยู่ 5เขาบอกนางทั้งสองว่า “ฉันเห็นว่าท่าทีของพ่อเธอต่อตัวฉันเปลี่ยนไป แต่พระเจ้าของพ่อฉันสถิตอยู่กับฉัน 6เธอสองคนก็รู้ว่าฉันพากเพียรทำงานให้พ่อของเธอด้วยสุดกำลัง 7แต่พ่อของเธอก็ยังบิดพลิ้วผิดสัญญาค่าจ้างของฉันถึงเป็นสิบครั้ง แต่พระเจ้าไม่ทรงยอมให้เขาทำอันตรายฉัน 8ถ้าเขากล่าวว่า ‘สัตว์ลายด่างจะเป็นค่าจ้างของเจ้า’ สัตว์ทุกตัวในฝูงก็จะตกลูกเป็นลายด่าง และถ้าเขากล่าวว่า ‘สัตว์ลายริ้วจะเป็นค่าจ้างของเจ้า’ สัตว์ทั้งฝูงก็จะตกลูกเป็นลายริ้ว 9ดังนั้นพระเจ้าจึงทรงยึดเอาฝูงสัตว์จากพ่อของเธอมาประทานแก่ฉัน

10“ครั้งหนึ่งในฤดูผสมพันธุ์ ฉันฝันไปว่าฉันเงยหน้าขึ้นเห็นแพะตัวผู้ที่กำลังผสมพันธุ์มีลายริ้ว ลายด่าง หรือลายจุด 11ทูตของพระเจ้ากล่าวกับฉันในฝันว่า ‘ยาโคบเอ๋ย’ ฉันตอบว่า ‘ข้าพเจ้าอยู่ที่นี่’ 12และทูตนั้นกล่าวว่า ‘จงเงยหน้าขึ้นดูเถิด แพะผู้ที่กำลังผสมพันธุ์นั้นล้วนมีลายริ้ว ลายด่าง หรือลายจุดเพราะเราได้เห็นทุกอย่างที่ลาบันทำกับเจ้า 13เราคือพระเจ้าแห่งเบธเอล ที่ซึ่งเจ้าได้เจิมเสาและได้กล่าวปฏิญาณไว้กับเรา บัดนี้เจ้าจงออกจากแผ่นดินนี้ทันทีและกลับไปยังบ้านเกิดเมืองนอนของเจ้า’ ”

14แล้วราเชลกับเลอาห์ตอบว่า “เรายังมีส่วนแบ่งในมรดกของพ่ออีกหรือ? 15พ่อไม่ถือว่าเราเป็นเหมือนคนต่างชาติหรอกหรือ? พ่อไม่เพียงแต่ขายเรา แต่ยังใช้เงินส่วนที่เป็นค่าตัวของเราจนหมด 16แน่ทีเดียวทรัพย์สมบัติทั้งสิ้นที่พระเจ้าทรงเอามาจากพ่อเป็นของเรากับลูกๆ ฉะนั้นเชิญท่านทำทุกอย่างตามที่พระเจ้าตรัสสั่งเถิด”

17แล้วยาโคบจึงให้ลูกๆ กับภรรยาขึ้นอูฐ 18ตัวเขาก็ต้อนฝูงสัตว์ทั้งหมดไปข้างหน้าเขา พร้อมกับสิ่งของต่างๆ ซึ่งเขาสะสมไว้ได้ที่ปัดดานอารัม ออกเดินทางกลับไปหาอิสอัคบิดาของเขาในแผ่นดินคานาอัน

19เมื่อลาบันออกไปตัดขนแกะ ราเชลก็ขโมยเหล่าเทวรูปประจำบ้านของบิดาติดตัวไปด้วย 20ยิ่งกว่านั้นยาโคบหลอกลวงลาบันชาวอารัมโดยการไม่บอกว่าเขากำลังจะหนีไป 21เขาจึงลอบหนีไปพร้อมกับข้าวของทั้งหมดที่มี เมื่อข้ามแม่น้ำยูเฟรติสแล้ว เขาก็มุ่งหน้าไปยังแดนเทือกเขากิเลอาด

ลาบันไล่ตามยาโคบ

22สามวันต่อมามีคนบอกลาบันให้รู้ว่ายาโคบหนีไปแล้ว 23เขาจึงพาญาติพี่น้องตามล่ายาโคบไปเป็นเวลาเจ็ดวัน และตามมาทันที่แดนเทือกเขากิเลอาด 24คืนนั้นพระเจ้าทรงปรากฏแก่ลาบันคนอารัมในความฝันและตรัสว่า “ไม่ว่าอะไรก็ตาม จงระวัง อย่าพูดจาคุกคามข่มขู่ยาโคบ”

25ขณะที่ยาโคบตั้งเต็นท์อยู่ที่แดนเทือกเขากิเลอาด ลาบันก็ตามมาทันและลาบันกับญาติพี่น้องก็ตั้งค่ายที่นั่นด้วย 26แล้วลาบันจึงกล่าวกับยาโคบว่า “ทำไมเจ้าทำอย่างนี้? เจ้าได้หลอกลวงเราและกวาดต้อนลูกสาวของเรามาราวกับเป็นเชลยศึก 27ทำไมเจ้าต้องแอบหนีมาและหลอกลวงเรา? ทำไมไม่บอกเราเพื่อเราจะได้ส่งเจ้ามาด้วยความยินดีด้วยการร้องเพลงพร้อมกับเล่นพิณและรำมะนา? 28เจ้าไม่ยอมแม้แต่จะให้เราได้จูบลาลูกหลานบ้างเลย เจ้าได้ทำสิ่งที่โง่เขลา 29เรามีอำนาจที่จะทำร้ายพวกเจ้า แต่เมื่อคืนนี้พระเจ้าของบิดาเจ้ากล่าวกับเราว่า ‘ไม่ว่าอะไรก็ตาม จงระวัง อย่าพูดจาคุกคามข่มขู่ยาโคบ’ 30ที่เจ้าจากมาเพราะอยากจะกลับไปบ้านบิดาของเจ้า แต่ทำไมเจ้าจึงขโมยบรรดาเทวรูปของเราไป?”

31ยาโคบตอบลาบันว่า “ฉันกลัว เพราะฉันคิดว่าท่านจะใช้กำลังพรากลูกสาวของท่านคืนไปจากฉัน 32แต่ถ้าท่านเจอเทวรูปของท่านอยู่กับใคร เขาจะต้องตาย ท่านจงค้นดูต่อหน้าญาติพี่น้องของเราเอาเองเถิดว่ามีสิ่งใดที่เป็นของท่านอยู่กับฉันหรือไม่ ถ้ามีก็จงเอาไปเถิด” ยาโคบไม่รู้ว่าราเชลได้ขโมยเทวรูปมา

33ดังนั้นลาบันจึงเข้าไปค้นในเต็นท์ของยาโคบ แล้วเข้าไปในเต็นท์ของเลอาห์ และเต็นท์ของสาวใช้ทั้งสอง แต่เขาไม่พบอะไร หลังจากออกมาจากเต็นท์ของเลอาห์ เขาเข้าไปในเต็นท์ของราเชล 34ฝ่ายราเชลขโมยเทวรูปประจำบ้านมาไว้ใต้กูบอูฐแล้วนั่งทับไว้ ลาบันค้นจนทั่วเต็นท์แต่ไม่พบอะไร

35ราเชลพูดกับบิดาของนางว่า “ท่านเจ้าข้า ขออย่าโกรธที่ลูกไม่ได้ยืนขึ้นต้อนรับ เพราะลูกกำลังมีประจำเดือน” ดังนั้นเขาจึงค้นแต่ไม่พบเทวรูปประจำบ้าน

36ยาโคบก็โกรธและตำหนิลาบันอย่างรุนแรง เขาถามลาบันว่า “ฉันไปก่อเรื่องอะไรไว้หรือ? ฉันไปทำผิดอะไรมา ท่านจึงไล่ล่าฉันอย่างนี้? 37เมื่อท่านค้นข้าวของทุกอย่างของฉันแล้ว ท่านพบอะไรที่เป็นของท่านบ้าง? จงเอามาวางต่อหน้าญาติของท่านและของฉันเถิด ให้พวกเขาตัดสินเรื่องระหว่างเราทั้งสอง

38“ฉันอยู่กับท่านมาจนถึงวันนี้ก็ยี่สิบปีแล้ว ฉันไม่เคยทำให้แพะแกะของท่านแท้งลูก ทั้งฉันก็ไม่เคยกินแกะของท่านเลย 39ตัวไหนถูกสัตว์ร้ายกัดกิน ฉันก็ไม่ได้เอาไปให้ท่าน ฉันรับผิดชอบความสูญเสียนั้นเอง และท่านก็เรียกร้องให้ฉันชดใช้สัตว์ทุกตัวที่ถูกขโมยไป ไม่ว่าจะหายไปตอนกลางวันหรือกลางคืน 40ตอนกลางวันก็ถูกความร้อนแผดเผา ตอนกลางคืนก็ต้องทนเหน็บหนาวจนหลับตาไม่ได้ 41เป็นอย่างนี้ตลอดยี่สิบปีที่ฉันอยู่ในครอบครัวของท่าน ฉันทำงานให้ท่านสิบสี่ปีเพื่อจะได้ลูกสาวสองคนของท่าน และอีกหกปีเพื่อจะได้ฝูงสัตว์ และท่านยังเปลี่ยนค่าจ้างของฉันเป็นสิบครั้ง 42ถ้าพระเจ้าของบรรพบุรุษของฉัน คือพระเจ้าของอับราฮัมและพระเจ้าที่อิสอัคยำเกรงไม่ได้อยู่กับฉัน ท่านก็คงจะให้ฉันมามือเปล่าเป็นแน่ แต่พระเจ้าทอดพระเนตรความยากลำบากและการตรากตรำของฉัน พระองค์จึงทรงว่ากล่าวท่านเมื่อคืนนี้”

43ลาบันตอบยาโคบว่า “ผู้หญิงเหล่านี้เป็นลูกสาวของเรา เด็กๆ ก็เป็นลูกหลานของเรา ฝูงสัตว์เหล่านี้ก็เป็นฝูงสัตว์ของเรา และทุกอย่างที่เจ้าเห็นอยู่นี้ล้วนเป็นของเรา แต่เราจะทำอะไรลูกสาวของเรา และลูกๆ ที่พวกนางให้กำเนิดได้เล่า? 44มาเถิดให้เราทำสนธิสัญญาระหว่างเจ้ากับเรา ให้เป็นพยานหลักฐานระหว่างเราทั้งสอง”

45ดังนั้นยาโคบจึงเอาหินก้อนหนึ่งตั้งขึ้นเป็นเสา 46แล้วเขาบอกกับญาติว่า “รวบรวมก้อนหินมา” ดังนั้นพวกเขาก็เอาหินมากองรวมกันเป็นพะเนิน และพวกเขาก็รับประทานอาหารด้วยกันข้างกองหินนั้น 47ลาบันเรียกกองหินนั้นว่าเยการ์สหดูธา31:47 เป็นคำภาษาอารเมคแปลว่ากองพยาน และยาโคบเรียกว่ากาเลเอด31:47 เป็นคำภาษาฮีบรูแปลว่ากองพยาน

48ลาบันกล่าวว่า “ในวันนี้กองหินนี้จะเป็นพยานระหว่างเรากับเจ้า” นี่เป็นเหตุที่กองหินนั้นได้ชื่อว่ากาเลเอด 49ทั้งมีชื่อว่ามิสปาห์31:49 แปลว่าหอสังเกตการณ์ด้วย เพราะเขากล่าวว่า “ขอให้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเฝ้าดูเรากับเจ้าเมื่อเราจากกันไป 50ถ้าเจ้าข่มเหงบรรดาลูกสาวของเราหรือมีภรรยาใหม่นอกจากลูกสาวของเรา ถึงแม้ไม่มีใครอยู่กับเรา ก็ขอให้จำไว้ว่าพระเจ้าทรงเป็นพยานระหว่างเจ้ากับเรา”

51ลาบันกล่าวกับยาโคบด้วยว่า “นี่เป็นกองหินและเสาซึ่งเราตั้งไว้ระหว่างเรากับเจ้า 52กองหินนี้เป็นพยานและเสานี้เป็นพยานว่า เราจะไม่ล่วงล้ำผ่านกองหินไปทางเขตแดนของเจ้าเพื่อทำร้ายเจ้า และเจ้าก็จะไม่ล่วงล้ำผ่านกองหินและเสานี้มาทางเขตแดนของเราเพื่อทำอันตรายเรา 53ขอให้พระเจ้าของอับราฮัมและเทพเจ้าของนาโฮร์ คือบรรดาพระของบรรพบุรุษ31:53 หรือพระเจ้าของอับราฮัมและของนาโฮร์ พระเจ้าของบรรพบุรุษของพวกเขา ทรงตัดสินระหว่างเราและเจ้า”

ดังนั้นยาโคบจึงกล่าวปฏิญาณในพระนามพระเจ้าผู้ซึ่งอิสอัคบิดาของตนยำเกรง 54เขาถวายเครื่องบูชาที่นั่น ที่เทือกเขานั้นและเชิญญาติพี่น้องรับประทานอาหาร หลังจากรับประทานอาหารแล้วก็พักค้างคืนที่นั่น

55เช้าตรู่วันรุ่งขึ้น ลาบันจูบอำลาและให้พรลูกหลานแล้วก็เดินทางกลับบ้าน