ዘዳግም 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 3:1-29

የባሳን ንጉሥ የዐግ መሸነፍ

1ከዚያም፣ ተመልሰን የባሳንን መንገድ ይዘን ወጣን፤ የባሳን ንጉሥ ዐግም ከመላው ሰራዊቱ ጋር ሆኖ በኤድራይ ጦርነት ሊገጥመን ተነሣ። 2እግዚአብሔር (ያህዌ)፣ “እርሱን፣ መላው ሰራዊቱንና ምድሩን በእጅህ አሳልፌ ስለ ሰጠሁህ፣ አትፍራው፤ ሐሴቦንን ይገዛ በነበረው በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ላይ ያደረግህበትን በእርሱም ላይ አድርግበት” አለኝ።

3ስለዚህ አምላካችን እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የባሳንን ንጉሥ ዐግንና ሰራዊቱን ሁሉ እንደዚሁ በእጃችን ላይ ጣላቸው፤ እኛም አንድ እንኳ በሕይወት ሳናስቀር አጠፋናቸው። 4በዚያን ጊዜ ከተሞቹን ሁሉ ያዝን፤ የዐግ ግዛት ከሆነው፣ በባሳን ከሚገኘው ከጠቅላላው የአርጎብ ክልል ስድሳ ከተሞች ውስጥ፣ እኛ ያልያዝነው አንድም ከተማ አልነበረም። 5እነዚህ ከተሞች ሁሉ ከፍ ባሉ ቅጥሮች፣ በመዝጊያዎችና በመወርወሪያዎች የተመሸጉ ነበሩ፤ እንዲሁም ቅጥር የሌላቸው አያሌ መንደሮች ነበሩ። 6በእያንዳንዱ ከተማ ያሉትን ወንዶቹን፣ ሴቶቹንና ልጆቻቸውን ጭምር በማጥፋት፣ በሐሴቦን ንጉሥ በሴዎን ላይ እንዳደረግነው ሁሉ፣ እነዚህንም ፈጽመን ደመሰስናቸው3፥6 የ2፥34 አማራጭ ትርጕም ይመ።7ከብቱን በሙሉና ከየከተሞቻቸው የማረክነውን ሁሉ ግን ለራሳችን አደረግን።

8ስለዚህ በዚያን ጊዜ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ ያለውን ግዛት፣ ከእነዚህ ከሁለቱ የአሞራውያን ነገሥታት ላይ ወሰድንባቸው። 9አርሞንዔምን፣ ሲዶናውያን ሢርዮን ብለው ሲጠሩት፣ አሞራውያን ግን ሳኔር ይሉታል። 10በከፍታው ቦታ ላይ የሚገኙትን ከተሞች በሙሉ፣ ገለዓድን እንዳለ፣ እስከ ሰልካና እስከ ኤድራይ ያለውን ባሳንን ሁሉ እንዲሁም በባሳን ውስጥ የሚገኙትን የዐግ ግዛት ከተሞች በእጃችን አደረግን። 11ከራፋይማውያን ወገን የተረፈ የባሳን ንጉሥ ዐግ ብቻ ነበር። ዐልጋው3፥11 ወይም፣ ድንጋይ ተጠርቦ የተዘጋይ የሬሳ ሣጥን ከብረት የተሠራ ቁመቱም ዘጠኝ ክንድ፣ ስፋቱ ደግሞ አራት ክንድ3፥11 ቁመቱ 4 ሜትር ስፋቱ 1.8 ሜትር ያህል ነው። ነበር። ይህም እስካሁን በአሞናውያን ከተማ በረባት ይገኛል።

እስራኤላውያን ምድሪቱን መከፋፈላቸው

12በዚያን ጊዜ ከያዝነው ምድር ላይ በአርኖን ሸለቆ አጠገብ ካለችው ከአሮዔር አንሥቶ በስተ ሰሜን ያለውን ግዛት፣ በተጨማሪም ኰረብታማውን የገለዓድ አገር እኩሌታ ከነከተሞቹ ለሮቤላውያንና ለጋዳውያን ሰጠኋቸው። 13ቀሪውን የገለዓድ ምድርና የዐግ ግዛት የሆነውን ባሳንን በሙሉ ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ሰጠሁ። በባሳን የሚገኘው መላው የአርጎብ ክልል የራፋይማውያን ምድር በመባል ይታወቅ ነበር። 14ከምናሴ ነገድ የሆነው ኢያዕር፣ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ወሰን ድረስ የሚገኘውን መላውን የአርጎብ ምድር ወሰደ፤ ምድሪቱም በስሙ ተጠራች3፥14 ወይም፣ የኢያዕር መኖሪያ ተብላ ተጠራች፤ ከዚሁ የተነሣ ባሳን እስከ ዛሬ ድረስ ሓቦት ኢያዕር ትባላለች። 15ገለዓድንም ለማኪር ሰጠሁት። 16ነገር ግን የሸለቆውን እኩሌታ ወሰን በማድረግ ከገለዓድ አንሥቶ እስከ አርኖን ሸለቆ፣ ከዚያም የአሞናውያን ድንበር እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ያለውን ግዛት ለሮቤላውያንና ለጋዳውያን ሰጠኋቸው። 17የምዕራቡ ወሰን፣ በዓረባ የሚገኘው ዮርዳኖስ ሲሆን፣ ይኸውም ከፈስጋ ተረተሮች በታች፣ ከኪኔሬት አንሥቶ የጨው ባሕር3፥17 ይኸውም የሙት ባሕር ነው። እስከሚባለው እስከ ዓረባ ባሕር ድረስ ነው።

18በዚያን ጊዜ እኔ እንዲህ ብዬ አዘዝኋችሁ፤ “አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ይህችን ምድር ርስት አድርጎ ለእናንተ ሰጥቷችኋል፤ ይሁን እንጂ የአካል ብቃት ያላቸው ሰዎቻችሁ ሁሉ ለጦርነት ዝግጁ ሆነው ከወንድሞቻችሁ ከእስራኤላውያን ፊት በመቅደም መሻገር አለባቸው። 19ሆኖም ሚስቶቻችሁና ልጆቻችሁ፣ (ብዙ ከብቶች እንዳሏችሁም ስለማውቅ) ከብቶቻችሁም በሰጠኋችሁ ከተሞች ውስጥ ይቈዩ፤ 20ይኸውም፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለእናንተ እንዳደረገው ሁሉ ወንድሞቻችሁን እስኪያሳርፋቸውና አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከዮርዳኖስ ማዶ የሚሰጣቸውን ምድር እነርሱም እንደዚሁ እስኪወርሱ ድረስ ነው፤ ከዚያ በኋላ እያንዳንዳችሁ ወደ ሰጠኋችሁ ርስት ትመለሳላችሁ።”

ሙሴ ዮርዳኖስን እንዳይሻገር መከልከሉ

21በዚያን ጊዜ ኢያሱን እንዲህ ስል አዘዝሁት፤ “አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእነዚህ በሁለቱ ነገሥታት ላይ ያደረገውን ሁሉ በገዛ ዐይንህ አይተሃል፤ አሁንም ዐልፈህ በምትሄድባቸው መንግሥታት ላይ ሁሉ እግዚአብሔር ይህንኑ ይደግመዋል። 22አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ራሱ ይዋጋላችኋልና አትፍሯቸው።”

23በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ ብዬ ለመንሁት፤ 24“ጌታ እግዚአብሔር (አዶናይ ያህዌ) ሆይ፤ ታላቅነትህንና ብርቱ ክንድህን ለእኔ ለባሪያህ እነሆ ማሳየት ጀምረሃል፤ ለመሆኑ በሰማይም ሆነ በምድር፣ አንተ የምታደርጋቸውን ሥራዎችና ታላላቅ ድርጊቶች መፈጸም የሚችል አምላክ ማነው? 25አሁንም ከዮርዳኖስ ማዶ ያለችውን ያችን መልካሚቱን ምድር፣ ውብ የሆነችውን ኰረብታማ አገርና ሊባኖስን እንዳይ ፍቀድልኝ።”

26እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን በእናንተ ሰበብ ተቈጥቶኝ ነበርና አልሰማኝም፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤ “ይበቃል፤ ከእንግዲህ ወዲያ ስለዚህ ነገር አታንሣብኝ። 27ወደ ፈስጋ ተራራ ጫፍ ውጣ፤ ወደ ምዕራብና ወደ ሰሜን፣ ወደ ደቡብና ወደ ምሥራቅም ተመልከት። አንተ ዮርዳኖስን ስለማትሻገር፣ ምድሪቱን በዐይንህ ብቻ እያት። 28ነገር ግን ሕዝቡን መርቶ በማሻገር የምታያትን ምድር እንዲወርሱ የሚያደርጋቸው ስለሆነ፣ ኢያሱን ላከው፤ አደፋፍረው፤ አበረታታውም።” 29ስለዚህ እኛ በቤተ ፌጎር አጠገብ ባለው ሸለቆ ውስጥ ቈየን።

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 3:1-29

พิชิตกษัตริย์โอกแห่งบาชาน

1ต่อมาเราขึ้นไปตามเส้นทางสู่ดินแดนบาชาน และกษัตริย์โอกแห่งบาชานยกไพร่พลทั้งหมดขึ้นมาสู้กับเราที่เอเดรอี 2องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “ไม่ต้องกลัวเขา เพราะเราได้มอบเขากับไพร่พลทั้งหมดและดินแดนของเขาแก่เจ้าแล้ว จงทำกับเขาเหมือนที่ได้ทำกับกษัตริย์สิโหนของชาวอาโมไรต์ผู้ปกครองอยู่ในเฮชโบน”

3ดังนั้นพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราได้ทรงมอบกษัตริย์โอกแห่งบาชานกับไพร่พลทั้งหมดไว้ในมือของเรา เราประหารพวกเขาหมดไม่เหลือรอดสักคน 4ในเวลานั้นเรายึดหัวเมืองทั้งหกสิบแห่งของเขา คือทั่วภูมิภาคอารโกบซึ่งเป็นอาณาจักรของโอกในบาชาน 5เมืองเหล่านี้เป็นเมืองป้อมปราการ มีกำแพงสูง ประตูก็ลงดาลแน่นหนา และเราตีหมู่บ้านมากมายหลายแห่งซึ่งไม่มีกำแพงล้อมรอบได้ด้วย 6เราทำลายล้าง3:6 คำนี้ในภาษาฮีบรูหมายถึงสิ่งของหรือบุคคลที่ถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วไม่อาจเรียกคืนได้ มักจะต้องทำลายให้หมดสิ้นไปพวกเขาหมดสิ้นเหมือนที่ได้ทำแก่กษัตริย์สิโหนแห่งเฮชโบน คือทำลายล้างทุกเมือง ทำลายทั้งผู้ชาย ผู้หญิง และเด็ก 7แต่เรายึดฝูงสัตว์พร้อมทั้งทรัพย์สินที่ได้จากเมืองต่างๆ มาเป็นของเรา

8ครั้งนั้นเราได้ยึดครองดินแดนทั้งหมดของกษัตริย์ชาวอาโมไรต์ทั้งสองในฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดน จากโกรกธารอารโนนจดภูเขาเฮอร์โมน 9(ชาวไซดอนเรียกภูเขาเฮอร์โมนว่า สีรีออน ส่วนชาวอาโมไรต์เรียกว่า เสนีร์) 10เรายึดทุกเมืองบนที่ราบสูงนั้น และกิเลอาดกับบาชานทั้งหมดไปถึงเมืองสาเลคาห์และเมืองเอเดรอีของอาณาจักรโอกในบาชาน 11(กษัตริย์โอกแห่งบาชานผู้นี้เป็นเรฟาอิมคนสุดท้ายที่เหลืออยู่ เตียงเหล็กของเขายาว 9 ศอก3:11 คือ ประมาณ 4 เมตรและกว้าง 4 ศอก3:11 คือ ประมาณ 1.8 เมตร เตียงนี้ยังอยู่ที่รับบาห์ซึ่งเป็นเมืองหนึ่งของชาวอัมโมน)

การแบ่งดินแดน

12ข้าพเจ้ายกดินแดนที่ยึดมาได้ในครั้งนั้นให้แก่เผ่ารูเบนและเผ่ากาด คือตั้งแต่อาโรเออร์ริมโกรกธารอารโนน ครึ่งหนึ่งของแดนเทือกเขากิเลอาดและหัวเมืองต่างๆ 13ส่วนดินแดนกิเลอาดที่เหลือและดินแดนบาชานทั้งหมดซึ่งเดิมเป็นอาณาจักรของกษัตริย์โอกมอบให้แก่เผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่า (อารโกบในบาชานนี้เคยได้ชื่อว่า ดินแดนแห่งเรฟาอิม 14ยาอีร์ซึ่งเป็นวงศ์วานของมนัสเสห์ครอบครองภูมิภาคอารโกบทั้งหมดจนจดชายแดนของชาวเกชูร์และชาวมาอาคาห์ ดินแดนบาชานได้ชื่อตามเขาจึงเรียกกันว่า ฮัฟโวทยาอีร์3:14 หรือบ้านเมืองของยาอีร์ มาจนถึงทุกวันนี้) 15ข้าพเจ้ายกดินแดนกิเลอาดให้มาคีร์ 16ส่วนเผ่ารูเบนและเผ่ากาด ข้าพเจ้ายกดินแดนจากกิเลอาดลงไปจดโกรกธารอารโนน (ถือเอาตอนกลางของโกรกธารเป็นพรมแดน) เรื่อยมาถึงแม่น้ำยับบอกซึ่งเป็นพรมแดนของชาวอัมโมน 17พรมแดนด้านตะวันตกคือแม่น้ำจอร์แดนในอาราบาห์จากคินเนเรทจดทะเลแห่งอาราบาห์ (คือทะเลเกลือ3:17 คือ ทะเลตาย) ใต้ลาดเขาปิสกาห์

18ครั้งนั้นข้าพเจ้าสั่งเผ่ารูเบน เผ่ากาด และเผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่าว่า “พระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านได้ประทานดินแดนฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดนให้ท่านยึดครอง แต่ชายฉกรรจ์ทุกคนในพวกท่าน จงจับอาวุธออกรบ นำหน้าพี่น้องอิสราเอลข้ามแม่น้ำไป 19ส่วนภรรยาของท่าน ลูกๆ และฝูงสัตว์ (ข้าพเจ้าทราบอยู่ว่าท่านมีฝูงสัตว์ใหญ่โต) ให้พักอยู่ในเมืองที่ข้าพเจ้ายกให้ 20ตราบจนองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงให้พี่น้องได้พักสงบเหมือนพวกท่าน และได้ยึดครองดินแดนซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านประทานให้ที่อีกฟากของแม่น้ำจอร์แดน เมื่อนั้นพวกท่านแต่ละคนจึงกลับสู่ดินแดนที่ข้าพเจ้ามอบให้ท่านเป็นกรรมสิทธิ์”

ห้ามโมเสสข้ามแม่น้ำจอร์แดน

21ครั้งนั้นข้าพเจ้ากำชับโยชูวาว่า “ท่านก็ได้เห็นกับตาแล้วถึงสิ่งทั้งปวงที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงกระทำแก่กษัตริย์ทั้งสองนั้น องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงกระทำอย่างเดียวกันต่ออาณาจักรทั้งปวงที่ฟากข้างโน้นซึ่งท่านกำลังมุ่งไป 22อย่ากลัวพวกเขา เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านเองจะทรงต่อสู้เพื่อท่าน”

23ครั้งนั้นข้าพเจ้าได้ทูลอ้อนวอนองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า 24“ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต พระองค์ทรงเริ่มสำแดงความยิ่งใหญ่และฤทธิ์อำนาจแก่ผู้รับใช้ของพระองค์แล้ว เพราะมีพระเจ้าใดเล่าทั่วฟ้าสวรรค์และแผ่นดินโลกที่ได้กระทำการยิ่งใหญ่เกรียงไกรเสมอเหมือนพระองค์? 25ขอโปรดให้ข้าพระองค์ได้ไปเห็นดินแดนอันอุดมสมบูรณ์ที่อีกฟากหนึ่งของแม่น้ำจอร์แดน คือแดนเทือกเขาอันงดงามนั้นกับเทือกเขาเลบานอน”

26แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธข้าพเจ้าเพราะพวกท่านและไม่ทรงฟังข้าพเจ้า องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาว่า “พอแล้ว เลิกพูดเรื่องนี้เสียที 27จงขึ้นไปบนยอดเขาปิสกาห์และมองไปให้ทั่วทุกทิศ จงมองดูแผ่นดินนั้นให้เต็มตาของเจ้า เพราะเจ้าจะไม่ได้ข้ามแม่น้ำจอร์แดนไป 28แต่จงมอบหมายงานให้โยชูวา จงให้กำลังใจเขาและช่วยให้เขาเข้มแข็งขึ้น เพราะเขาจะนำประชากรข้ามไปครอบครองดินแดนที่เจ้าจะเห็น” 29ฉะนั้นเราทั้งหลายจึงยังคงพักอยู่ในหุบเขาใกล้เบธเปโอร์