ዘዳግም 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 4:1-49

ሙሴ እስራኤላውያን እንዲታዘዙ ማስጠንቀቁ

1አሁንም እስራኤል ሆይ፤ በሕይወት እንድትኖሩ፣ የአባቶቻችሁ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ወደሚሰጣችሁ ምድር እንድትገቡና እንድትወርሱ የማስተምራችሁን ሥርዐትና ሕግ ስሙ፤ ጠብቋቸውም። 2ባዘዝኋችሁ ላይ አትጨምሩ፤ ከእርሱም አትቀንሱ፤ ነገር ግን የምሰጣችሁን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ትእዛዞች ጠብቁ።

3እግዚአብሔር (ያህዌ) በብዔልፌጎር ላይ ምን እንዳደረገ በዐይናችሁ አይታችኋል፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከመካከላችሁ ብዔልፌጎርን የተከተሉትን ሁሉ አጥፍቷቸዋል፤ 4አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) የተከተላችሁት እናንተ ሁላችሁ ግን ይኸው እስከ ዛሬ በሕይወት አላችሁ።

5ገብታችሁ በምትወርሷት ምድር፣ እንድትፈጽሟቸው እግዚአብሔር አምላኬ (ያህዌ ኤሎሂም) ባዘዘኝ መሠረት ሥርዐትንና ሕግን አስተምሬአችኋለሁ። 6በጥንቃቄ ጠብቋቸው፤ ስለ እነዚህ ሥርዐቶች ሁሉ ለሚሰሙና፣ “በእውነቱ ይህ ታላቅ ሕዝብ የቱን ያህል ጥበበኛና አስተዋይ ነው” ለሚሉ ሕዝቦች ይህ ጥበባችሁንና ማስተዋላችሁን ይገልጣልና። 7በምንጠራው ጊዜ ሁሉ አምላካችን እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለእኛ ቅርብ እንደ ሆነ አማልክቱ የሚቀርቡት ሌላ ታላቅ ሕዝብ ማነው? 8ዛሬ እኔ በፊታችሁ እንዳስቀመጥሁት ሕግ ያለ ጽድቅ የሆነ ሥርዐትና ሕግ ያሉት ሌላ ታላቅ ሕዝብስ ማነው?

9ዐይኖቻችሁ ያዩአቸውን ነገሮች እንዳትረሱ፣ ደግሞም በሕይወት እስካላችሁ ድረስ ከልባችሁ እንዳይጠፉ ብቻ ተጠንቀቁ፣ ነቅታችሁም ራሳችሁን ጠብቁ። እነዚህን ለልጆቻችሁና ከእነርሱ በኋላ ለሚወለዱት ልጆቻቸው አስተምሯቸው። 10“በምድሪቱ በሚኖሩበት ጊዜ ሁሉ እኔን ማክበር እንዲማሩ፣ ለልጆቻቸውም እንዲያስተምሩ ቃሌን ይሰሙ ዘንድ ሕዝቡን በፊቴ ሰብስብ” ባለኝ ጊዜ፣ በኮሬብ በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት የቆማችሁበትን ዕለት አስታውሱ። 11ተራራው በጥቍር ደመናና በድቅድቅ ጨለማ ተውጦ ሳለ ነበልባሉ ሰማይ እስከሚደርስ ድረስ በተቃጠለ ጊዜ መጥታችሁ ከተራራው ግርጌ ቆማችሁ። 12ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳቱ ውስጥ ሆኖ ተናገራችሁ፤ እናንተም የቃሉን ድምፅ ሰማችሁ፤ መልክ ግን አላያችሁም፤ ድምፅ ብቻ ነበርና። 13እርሱ ኪዳኑን ይኸውም እንድትከተሏቸው ያዘዛችሁን ዐሥርቱን ትእዛዛት ዐወጀላችሁ፤ ከዚያም በሁለት የድንጋይ ጽላቶች ላይ ጻፋቸው፤ 14ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ በምትወርሷት ምድር ውስጥ የምትከተሏቸውን ሥርዐትና ሕግ እንዳስተምራችሁ በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) አዘዘኝ።

ጣዖትን ማምለክ ስለ መከልከሉ

15እግዚአብሔር (ያህዌ) በኮሬብ ተራራ ላይ በእሳት ውስጥ በተናገራችሁ ቀን ምንም ዐይነት መልክ ከቶ አላያችሁም፤ ስለዚህ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ 16ይኸውም እንዳትረክሱ፣ በወንድ ወይም በሴት መልክ በማናቸውም ዐይነት ምስል የተቀረጸ ጣዖት ለራሳችሁ እንዳታበጁ፣ 17ወይም በምድር ላይ የሚኖር የማናቸውንም እንስሳ ወይም በአየር ላይ የሚበርር የማናቸውንም ወፍ፣ 18ወይም በደረቱ የሚሳብ የማናቸውንም ፍጡር ወይም በውሃ ውስጥ የሚኖር የማናቸውንም ዓሣ ምስል እንዳታደርጉ ነው። 19ወደ ሰማይ ቀና ብለህ ፀሓይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን፣ የሰማይ ሰራዊትንም ሁሉ በምትመለከትበት ጊዜ፣ ወደ እነርሱ እንዳትሳብና እንዳትሰግድላቸው፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከሰማይ በታች ላሉ ሕዝቦች ሁሉ ድርሻ አድርጎ የሰጣቸውንም ነገሮች እንዳታመልክ ተጠንቀቅ። 20እናንተን ግን ልክ ዛሬ እንደ ሆናችሁት ሁሉ ርስቱ ትሆኑለት ዘንድ፣ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እናንተን ከብረት ማቅለጫ ምድጃ፣ ከግብፅ አውጥቶ አመጣችሁ።

21በእናንተም ምክንያት እግዚአብሔር እኔን ተቈጣኝ፤ ዮርዳኖስንም እንዳልሻገርና አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ርስት አድርጎ ወደሚሰጣችሁ ወደ መልካሚቱ ምድር እንዳልገባ ማለ። 22እኔም በዚህች ምድር እሞታለሁ፤ ዮርዳኖስን አልሻገርም፤ እናንተ ግን ልትሻገሩ ነው፤ ያችንም መልካም ምድር ትወርሳላችሁ። 23አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከእናንተ ጋር የገባውን ኪዳን እንዳትረሱ ተጠንቀቁ፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የከለከለውን ጣዖት በማናቸውም ዐይነት መልክ ለራሳችሁ አታብጁ። 24አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚባላ እሳት ቀናተኛም አምላክ (ኤሎሂም) ነውና።

25ልጆችንና የልጅ ልጆችን ከወለዳችሁና በምድሪቱም ላይ ለረዥም ጊዜ ከኖራችሁ በኋላ ራሳችሁን በማርከስ ማንኛውንም ዐይነት ጣዖት ብታበጁ፣ በአምላካችሁም በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ክፋት በማድረግ ለቍጣ ብታነሣሡት፣ 26ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ ከምትወርሷት ምድር ላይ ፈጥናችሁ እንደምትጠፉ በዚህ ቀን ሰማይንና ምድርን በእናንተ ላይ ምስክሮች አድርጌ እጠራለሁ፤ በዚያ ቦታ ብዙ ዘመን አትኖሩም፤ ፈጽሞ ትጠፋላችሁ። 27እግዚአብሔር (ያህዌ) እናንተን በአሕዛብ መካከል ይበትናችኋል፤ እግዚአብሔር በሚበትናችሁ አሕዛብ መካከል የምትተርፉት ጥቂቶቻችሁ ብቻ ናችሁ። 28እዚያም፣ ማየት ወይም መስማት ወይም መብላት ወይም ማሽተት በማይችሉ በሰው እጅ በተሠሩ የዕንጨትና የድንጋይ አማልክት ታመልካላችሁ። 29ነገር ግን እዚያም ሆናችሁ አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) በፍጹም ልባችሁና በፍጹም ነፍሳችሁ ብትፈልጉት ታገኙታላችሁ። 30ስትጨነቅና ይህ ሁሉ ነገር ሲደርስብህ ያን ጊዜ፣ በኋለኞቹ ዘመናት ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ትመለሳለህ፤ ትታዘዝለታለህም። 31አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) መሓሪ አምላክ (ኤሎሂም) ነውና አይተውህም ወይም አያጠፋህም፤ ወይም ደግሞ ለአባቶችህ በመሐላ ያጸናላቸውን ቃል ኪዳን አይረሳም።

እግዚአብሔር አምላክ ነው

32እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ ከፈጠረበት ቀን ጀምሮ እናንተ ከመኖራችሁ በፊት ስለ ነበረው የቀድሞ ዘመን ጠይቁ፤ ከአንዱ የሰማይ ጫፍ እስከ ሌላው የሰማይ ጫፍ ድረስ ጠይቁ፤ እንደዚህ ያለ ታላቅ ነገር ከቶ ተደርጎ ወይስ እንደዚህ ዐይነት ነገር ከቶ ተሰምቶ ያውቃልን? 33ከእሳት ውስጥ የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ድምፅ እንደ እናንተ የሰማና በሕይወት የኖረ ከቶ ሌላ ሕዝብ አለን? 34አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በዐይናችሁ እያያችሁ ለእናንተ በግብፅ እንዳደረገው ሁሉ በፈተና፣ በታምራዊ ምልክቶችና በድንቆች፣ በጦርነት፣ በጸናች እጅና በተዘረጋች ክንድ ወይም በታላቅና በአስፈሪ ሥራዎች ከሌላ ሕዝብ መካከል አንድን ሕዝብ የራሱ ለማድረግ የቻለ አምላክ አለን?

35እግዚአብሔር እርሱ አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) መሆኑን፣ ከእርሱም በቀር ሌላ አምላክ አለመኖሩን ታውቁ ዘንድ እነዚህን ነገሮች እንድታዩ ተደረገ። 36ሊገሥጽህ ድምፁን ከሰማይ እንድትሰማ አደረገ፤ በምድርም ላይ አስፈሪ እሳቱን አሳየህ፤ ከእሳቱም ውስጥ ቃሉን ሰማህ። 37አባቶችህን ከመውደዱ የተነሣና ከእነርሱም በኋላ ዘራቸውን ስለ መረጠ፣ ከአንተ ጋር በመሆን በታላቅ ኀይሉ ከግብፅ አወጣህ፤ 38ዛሬ እንደ ሆነው ሁሉ ከአንተ ይልቅ ታላቅና ብርቱ የሆኑትን አሕዛብ ከፊትህ በማስወጣት ወደ ምድራቸው አስገብቶህ ለአንተ ርስት አድርጎ ለመስጠት ነው።

39እንግዲህ በላይ በሰማይ፣ በታችም በምድር እግዚአብሔር እርሱ አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) መሆኑን ዛሬ ዕወቅ፤ በልብህም ያዘው፤ ሌላም የለም። 40ለአንተና ከአንተም በኋላ ለልጆችህ መልካም እንዲሆንላችሁ፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለዘላለም በሚሰጥህም ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም፣ ዛሬ እኔ የማዝዝህን ሥርዐቱንና ሕግጋቱን ጠብቅ።

የመማፀኛ ከተሞች

4፥41-43 ተጓ ምብ – ዘኍ 35፥6-34ዘዳ 19፥1-14ኢያ 20፥1-9

41በዚያን ጊዜ ሙሴ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ሦስት ከተሞችን ለየ፤ 42ይኸውም የቈየ ጠላትነት ሳይኖር፣ በድንገት ባልንጀራውን የገደለ ማናቸውም ሰው ሸሽቶ ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዲቱ በመሄድ ሕይወቱን ማትረፍ ይችል ዘንድ ነው። 43ከተሞቹም በምድረ በዳው በከፍተኛ ቦታ ላይ የምትገኘው ቦሶር ለሮቤላውያን፣ በገለዓድ የምትገኘው ራሞት ለጋዳውያን፣ በባሳን ያለችው ጎላን ለምናሴያውያን ነበሩ።

ስለ ሕጉ የተሰጠ ማብራሪያ

44ሙሴ በእስራኤላውያን ፊት የደነገገው ሕግ ይህ ነው። 45ከግብፅ በወጡ ጊዜ ሙሴ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው መመሪያዎች፣ ሥርዐቶችና ሕጎች እነዚህ ናቸው፤ 46ይህም ከግብፅ በወጡ ጊዜ በሙሴና በእስራኤላውያን ድል በተደረገው፣ በሐሴቦን በነገሠው በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ በቤተ ፌጎር አጠገብ ባለው ሸለቆ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ነው። 47ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ያለውን፣ የእርሱን ምድርና የባሳንን ንጉሥ የዐግን፣ የሁለቱን አሞራውያን ነገሥታት ምድር ርስት አድርገው ወሰዱ። 48ይህም ምድር በአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ካለው ከአሮዔር አንሥቶ እስከ ሴዎን4፥48 የዕብራይስጡና የሱርስቱ ትርጕም፣ ሢርዮን ይለዋል (ዘዳ 3፥9 ይመ) ተራራ ማለትም እስከ አርሞንዔም የሚደርስ ሲሆን፣ 49በዮርዳኖስ ምሥራቅ ያለውን ዓረባን በሙሉና ከፈስጋ ተረተር በታች ያለውን የዓረባ ባሕር4፥49 ይኸውም የሙት ባሕር ነው። ያጠቃልላል።

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 4:1-49

บัญชาให้เชื่อฟัง

1อิสราเอลเอ๋ย บัดนี้จงฟัง4:1 หรือเชื่อฟังกฎหมายและบทบัญญัติซึ่งข้าพเจ้าจะสอน จงปฏิบัติตามเพื่อท่านจะมีชีวิตอยู่และเข้าไปครอบครองดินแดนที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของบรรพบุรุษของท่านกำลังยกให้ท่าน 2อย่าเพิ่มเติมหรือตัดทอนข้อความใดๆ ในบทบัญญัตินี้ แต่จงปฏิบัติตามพระบัญชาของพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านซึ่งข้าพเจ้ามอบให้แก่ท่าน

3ท่านก็ได้เห็นกับตาแล้วถึงสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำที่บาอัลเปโอร์ พระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านทรงประหารทุกคนที่ติดตามพระบาอัลแห่งเปโอร์ 4แต่ทุกคนที่ยึดมั่นในพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านยังมีชีวิตอยู่ตราบจนทุกวันนี้

5ดูเถิด ข้าพเจ้าได้สอนกฎหมายและบทบัญญัติตามที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพเจ้าทรงบัญชาแก่ท่าน เพื่อท่านจะปฏิบัติตามในดินแดนที่ท่านจะเข้ายึดครอง 6จงปฏิบัติตามอย่างเคร่งครัด เพื่อแสดงให้ประชาชาติทั้งหลายเห็นถึงสติปัญญาและความเข้าใจของท่าน เมื่อพวกเขาได้ยินถึงกฎหมายเหล่านี้ พวกเขาจะกล่าวว่า “ชนชาติยิ่งใหญ่นี้มีปัญญาและมีความเข้าใจจริงๆ” 7ชาติใดเล่าที่ยิ่งใหญ่ขนาดมีพระเจ้าของพวกเขาอยู่ใกล้ชิดอย่างที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของเราทรงอยู่ใกล้ชิดเราทุกครั้งที่เราทูลอธิษฐานต่อพระองค์? 8และมีชาติใดเล่าที่ยิ่งใหญ่ขนาดมีกฎหมายและบทบัญญัติอันชอบธรรมเหมือนบทบัญญัติซึ่งข้าพเจ้ามอบให้พวกท่านในวันนี้?

9แต่จงรักษาตัวรักษาใจของท่านให้ดีเพื่อท่านจะไม่หลงลืมสิ่งที่ท่านเห็นกับตา ไม่ปล่อยให้สิ่งเหล่านี้เลือนรางจากใจตราบชั่วชีวิต จงสอนลูกหลานสืบต่อกันไป 10จงรำลึกถึงวันที่ท่านยืนอยู่ต่อหน้าพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทั้งหลายที่ภูเขาโฮเรบ เมื่อพระองค์ได้ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงเรียกประชากรมาชุมนุมต่อหน้าเรา เพื่อฟังถ้อยคำของเรา เพื่อเขาจะเรียนรู้ที่จะยำเกรงเราตราบเท่าที่เขายังมีชีวิตอยู่บนแผ่นดินนี้ และเพื่อเขาจะสอนบัญญัติของเราแก่ลูกหลาน” 11ท่านทั้งหลายได้เข้ามาใกล้และยืนอยู่ที่เชิงเขาซึ่งมีไฟลุกโชติช่วงขึ้นสู่ท้องฟ้า รายรอบด้วยเมฆดำและความมืดทึบ 12แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับท่านจากเปลวไฟ ท่านได้ยินพระดำรัสแต่ไม่ได้เห็นรูปพรรณสัณฐานของพระองค์ มีแต่พระสุรเสียงเท่านั้น 13พระองค์ทรงประกาศพันธสัญญาของพระองค์ คือบัญญัติสิบประการซึ่งพระองค์ทรงบัญชาให้ท่านปฏิบัติตาม แล้วทรงจารึกบัญญัตินั้นไว้บนศิลาสองแผ่น 14ครั้งนั้นเององค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาให้ข้าพเจ้าสอนกฎหมายและบทบัญญัติซึ่งท่านจะต้องปฏิบัติตามในดินแดนที่ท่านกำลังจะข้ามแม่น้ำจอร์แดนเข้าไปยึดครอง

ห้ามกราบไหว้รูปเคารพ

15พวกท่านไม่ได้เห็นรูปพรรณสัณฐานใดๆ ขององค์พระผู้เป็นเจ้าในวันที่พระองค์ตรัสกับท่านจากไฟที่ภูเขาโฮเรบ ฉะนั้นจงระวังตัวให้ดี 16เพื่อท่านจะไม่พินาศ โดยสร้างรูปจำลองของพระองค์ ไม่ว่าจะเป็นรูปเคารพในลักษณะใดๆ ก็ตาม ไม่ว่าจะมีลักษณะเหมือนผู้ชายหรือผู้หญิง 17เหมือนสัตว์ต่างๆ ในแผ่นดินหรือนกในอากาศ 18เหมือนสัตว์เลื้อยคลานหรือสัตว์น้ำ 19และเมื่อท่านเงยหน้าดูท้องฟ้าและเห็นดวงอาทิตย์ ดวงจันทร์ และดวงดาวอันเป็นวัตถุในท้องฟ้าทั้งปวง อย่าปล่อยใจไปกราบไหว้สิ่งเหล่านั้น และนมัสการสิ่งต่างๆ ที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านทรงปล่อยให้ชนชาติอื่นๆ ทั้งปวงทั่วใต้ฟ้าปฏิบัติ 20แต่ส่วนท่าน องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงนำออกมาจากเตาหลอมเหล็ก คือออกจากอียิปต์เพื่อเป็นประชากรในกรรมสิทธิ์ของพระองค์อย่างที่เป็นอยู่เดี๋ยวนี้

21องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระพิโรธข้าพเจ้าเพราะพวกท่านและทรงสัญญาอย่างหนักแน่นว่า ข้าพเจ้าจะไม่ได้ข้ามแม่น้ำจอร์แดนเข้าสู่ดินแดนอันอุดมสมบูรณ์ซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านจะประทานให้เป็นกรรมสิทธิ์ของท่าน 22ข้าพเจ้าจะต้องตายในดินแดนฟากนี้ จะไม่ได้ข้ามแม่น้ำจอร์แดนไป ส่วนท่านจะข้ามไปยึดครองดินแดนอันอุดมสมบูรณ์นั้น 23จงระวัง อย่าลืมพันธสัญญาที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านทรงกระทำไว้กับท่าน อย่าสร้างรูปเคารพเป็นรูปทรงใดๆ ให้กับตนตามที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านทรงห้ามไว้ 24เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงเป็นไฟอันเผาผลาญ เป็นพระเจ้าผู้ทรงหึงหวง

25ในอนาคตเมื่อท่านลงหลักปักฐานในดินแดนนั้นและมีลูกมีหลาน หากท่านเสื่อมทรามจนสร้างรูปเคารพใดๆ ซึ่งเป็นการกระทำที่ชั่วร้ายในสายพระเนตรของพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านและยั่วยุพระพิโรธของพระองค์ 26วันนี้ข้าพเจ้าขอให้ฟ้าดินเป็นพยานว่าไม่ช้าท่านจะพินาศย่อยยับจากดินแดนซึ่งพวกท่านกำลังจะข้ามแม่น้ำจอร์แดนเข้าไปครอบครอง ท่านจะอยู่ที่นั่นได้ไม่นานและจะพินาศไปอย่างแน่นอน 27องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงขับไล่ท่านให้กระจัดกระจายไปอยู่ท่ามกลางชนชาติต่างๆ ท่านจะเหลือรอดเพียงไม่กี่คนท่ามกลางประชาชาติเหล่านั้น 28ที่นั่นท่านจะนมัสการบรรดาเทพเจ้าที่มนุษย์สร้างขึ้นจากไม้และหิน ซึ่งมองก็ไม่เห็น ฟัง กิน หรือดมอะไรก็ไม่ได้ 29แต่หากท่านแสวงหาพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านที่นั่น ท่านจะพบพระองค์หากท่านแสวงหาพระองค์อย่างสุดจิตสุดใจ 30เมื่อท่านทุกข์ลำเค็ญเพราะสิ่งทั้งปวงนี้เกิดขึ้นแก่ท่านในเวลาต่อมา ท่านจะหวนกลับมาหาพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านและเชื่อฟังพระองค์ 31เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของพวกท่านทรงเป็นพระเจ้าผู้ทรงเมตตา พระองค์จะไม่ทรงทอดทิ้ง หรือทำลายท่าน หรือลืมพันธสัญญาที่ทรงให้ไว้กับบรรพบุรุษของท่านซึ่งพระองค์ทรงยืนยันกับพวกเขาโดยคำปฏิญาณ

พระยาห์เวห์ทรงเป็นพระเจ้า

32จงมองย้อนดูประวัติศาสตร์ตั้งแต่ครั้งพระเจ้าทรงสร้างมนุษย์ไว้ในโลก มองจากฟ้าข้างนี้ถึงฟ้าข้างโน้น เคยมีอะไรที่ยิ่งใหญ่อย่างนี้เกิดขึ้นมาก่อนหรือ? มีใครเคยได้ยินอะไรอย่างนี้ด้วยหรือ? 33มีคนชาติใดบ้างที่ยังมีชีวิตอยู่หลังจากได้ยินพระสุรเสียงของพระเจ้าตรัสออกมาจากไฟเหมือนที่ท่านได้ประสบมา? 34มีพระใดเล่าที่นำชนชาติหนึ่งออกมาจากอีกชนชาติหนึ่งมาเป็นของพระองค์เองโดยการทดสอบ โดยหมายสำคัญและการอัศจรรย์ โดยสงคราม โดยพระหัตถ์อันทรงฤทธิ์และพระกรที่เหยียดออก โดยพระราชกิจอันยิ่งใหญ่และน่าครั่นคร้าม เหมือนที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านได้ทรงกระทำเพื่อท่านในอียิปต์ต่อหน้าต่อตาท่าน?

35พระองค์ทรงสำแดงสิ่งเหล่านี้เพื่อให้พวกท่านรู้ว่าพระยาห์เวห์ทรงเป็นพระเจ้า นอกจากพระองค์แล้วไม่มีพระเจ้าอื่นใด 36จากฟ้าสวรรค์พระองค์ทรงให้ท่านได้ยินพระสุรเสียงเพื่อท่านจะอยู่ในโอวาท ในโลกพระองค์ทรงโปรดให้ท่านเห็นไฟมหึมาของพระองค์ และท่านได้ยินพระดำรัสจากไฟนั้น 37ทั้งนี้เพราะพระองค์ทรงรักบรรพบุรุษของท่านและทรงเลือกสรรวงศ์วานของเขาเหล่านั้น พระองค์จึงทรงนำท่านออกจากอียิปต์ด้วยพระองค์เองและด้วยฤทธานุภาพอันยิ่งใหญ่ของพระองค์ 38ทรงขับไล่ชนชาติต่างๆ ซึ่งยิ่งใหญ่และเข้มแข็งกว่าท่านมากนัก และประทานดินแดนของพวกเขาเหล่านั้นให้เป็นกรรมสิทธิ์ของท่านดังเช่นทุกวันนี้

39ในวันนี้จงรับรู้และจำใส่ใจว่าพระยาห์เวห์ทรงเป็นพระเจ้าทั้งในฟ้าสวรรค์เบื้องบนและแผ่นดินโลกเบื้องล่าง ไม่มีพระเจ้าอื่นใด 40จงปฏิบัติตามกฎหมายและพระบัญชาของพระองค์ซึ่งข้าพเจ้าแจ้งท่านในวันนี้ เพื่อท่านกับลูกหลานจะอยู่เย็นเป็นสุข และอาศัยอยู่ยาวนานในแผ่นดินซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานแก่ท่านตลอดไป

เมืองลี้ภัย

(กดว.35:6-34; ฉธบ.19:1-14; ยชว.20:1-9)

41จากนั้นโมเสสกำหนดเมืองสามเมืองทางฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดน 42สำหรับเป็นเมืองลี้ภัยของผู้ที่ฆ่าคนตายโดยไม่เจตนาและไม่ได้วางแผนการร้ายไว้ล่วงหน้า เขาจะได้หนีไปเมืองลี้ภัยเมืองใดเมืองหนึ่งเพื่อรักษาชีวิตของตนไว้ 43โดยให้เผ่ารูเบนลี้ภัยไปเมืองเบเซอร์บนที่ราบสูงในถิ่นกันดาร ให้เผ่ากาดไปเมืองราโมทในกิเลอาด และให้เผ่ามนัสเสห์ไปเมืองโกลานในบาชาน

บทนำสู่บทบัญญัติ

44ต่อไปนี้คือบทบัญญัติซึ่งโมเสสมอบให้ชนอิสราเอล 45เป็นข้อกำหนด กฎหมาย และบทบัญญัติซึ่งโมเสสให้ไว้เมื่อพวกเขาออกจากอียิปต์ 46และมาอยู่ที่หุบเขาใกล้เบธเปโอร์ ด้านตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดน ในดินแดนซึ่งเคยเป็นของกษัตริย์สิโหนของชาวอาโมไรต์ผู้ครอบครองในเฮชโบน โมเสสและชนชาติอิสราเอลได้พิชิตเขาขณะออกมาจากอียิปต์ 47และยึดครองดินแดนของเขาและของกษัตริย์โอกแห่งบาชาน กษัตริย์ทั้งสองของชาวอาโมไรต์ทางฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดน 48ดินแดนนี้เริ่มจากอาโรเออร์ตรงริมโกรกธารอารโนนจดภูเขาสีรีออน4:48 ฉบับ Heb. ว่าสิยอน (คือเฮอร์โมน) 49รวมทั้งดินแดนอาราบาห์ทั้งหมดทางฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดนจนถึงทะเลตาย4:49 ภาษาฮีบรูว่าทะเลอาราบาห์แถบลาดเขาปิสกาห์