ዘካርያስ 11 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 11:1-17

1ሊባኖስ ሆይ፤ እሳት ዝግባሽን እንዲበላው

ደጆችሽን ክፈቺ!

2የጥድ ዛፍ ሆይ፤ ዝግባ ወድቋልና አልቅስ፤

የከበሩትም ዛፎች ጠፍተዋል!

የባሳን ወርካዎች ሆይ፤ አልቅሱ፤

ጥቅጥቅ ያለው ደን ተመንጥሯል!

3የእረኞችን ዋይታ ስሙ፤

ክብራቸው ተገፍፏልና፤

የአንበሶችን ጩኸት ስሙ፤

ጥቅጥቅ ያለው የዮርዳኖስ ደን ወድሟል!

ሁለቱ እረኞች

4እግዚአብሔር አምላኬ እንዲህ ይላል፤ “ለዕርድ የተለዩትን በጎች አሰማራ፤ 5የገዟቸው ያርዷቸዋል፤ ሳይቀጡም ይቀራሉ፤ የሸጧቸውም፣ ‘እግዚአብሔር ይመስገን፤ ባለጠጋ ሆኛለሁ’ ይላሉ፤ ጠባቂዎቻቸውም እንኳ አይራሩላቸውም። 6ከእንግዲህ በምድሪቱ ለሚኖረው ሕዝብ አልራራምና” ይላል እግዚአብሔር፤ “ሰውን ሁሉ ለባልንጀራውና ለንጉሡ አሳልፌ እሰጣለሁ፤ እነርሱ ምድሪቱን ያስጨንቃሉ፤ እኔም ከእጃቸው አላድናቸውም።”

7ስለዚህ ለዕርድ የተለዩትን በጎች፣ በተለይም የተጨቈኑትን አሰማራሁ። ሁለት በትሮች ወስጄም፣ አንዱን “ሞገስ” ሌላውንም “አንድነት” ብዬ ጠራኋቸው፤ መንጋውንም አሰማራሁ። 8በአንድ ወር ውስጥ ሦስቱን እረኞች አስወገድሁ።

በጎቹ ጠሉኝ፤ እኔም፣ ሰለቸኋቸው፤ 9“እረኛችሁ አልሆንም፤ የሚሞቱት ይሙቱ፤ የሚጠፉት ይጥፉ፤ የቀሩትም አንዱ የሌላውን ሥጋ ይብላ” አልኋቸው።

10ከዚያም ከአሕዛብ ሁሉ ጋር የገባሁትን ኪዳን ለማፍረስ፣ “ሞገስ” ብዬ የጠራሁትን በትሬን ወስጄ ሰበርሁት። 11በዚያም ቀን ኪዳኑ ፈረሰ፤ ሲመለከቱኝ የነበሩትና የተጨነቁት በጎችም የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ዐወቁ።

12እኔም፣ “የሚበጅ መስሎ ከታያችሁ ዋጋዬን ክፈሉኝ፤ አይሆንም ካላችሁም ተዉት” አልኋቸው፤ ስለዚህ ሠላሳ ብር ከፈሉኝ።

13እግዚአብሔርም ሊከፍሉኝ የተስማሙበትን ጥሩ ዋጋ “በግምጃ ቤቱ ውስጥ አኑረው” አለኝ፤ እኔም ሠላሳውን ብር ወስጄ በእግዚአብሔር ቤት ባለው ግምጃ ቤት አስቀመጥሁት። 14ከዚያም የእስራኤልንና የይሁዳን ወንድማማችነት በማፍረስ፣ “አንድነት” ብዬ የጠራሁትን ሁለተኛውን በትሬን ሰበርሁት።

15እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “እንደ ገና የሰነፍ እረኛ ዕቃ ውሰድ፤ 16እነሆ፤ በምድሪቱ ላይ እረኛ አስነሣለሁ፤ እርሱም የጠፋውን አያስብም፤ የባዘነውን አይፈልግም፤ የተሰበረውን አይጠግንም፤ የዳነውንም አይቀልብም፤ ነገር ግን የሠባውን ሥጋ ይበላል፤ ሰኰናውንም ሳይቀር ይቀለጣጥማል።

17“መንጋውን ለሚተው፣

ለማይረባ እረኛ ወዮለት!

ሰይፍ ክንዱንና ቀኝ ዐይኑን ትውጋው!

ክንዱ ፈጽማ ትስለል!

ቀኝ ዐይኑም ጨርሳ ትታወር!”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒迦利亞書 11:1-17

羊群必遭殺戮

1黎巴嫩啊,打開你的門吧,

好讓火焰吞噬你的香柏樹。

2松樹啊,哀號吧,

因為香柏樹已經倒下,

挺拔的樹木已被毀壞。

巴珊的橡樹啊,哀號吧,

因為茂密的樹林已被砍倒。

3聽啊,牧人在哀號,

因為他們肥美的草場已被毀壞。

聽啊,獅子在吼叫,

因為約旦河畔的叢林已被毀壞。

4我的上帝耶和華說:「你去牧養這群待宰的羊吧。 5買羊宰羊的不受懲罰,賣羊的說,『耶和華當受稱頌!我發財了。』牠們的牧人不憐憫牠們。 6因此,我不再憐憫這地方的居民,我要使他們落在鄰人及其君王手中,任這地方被摧毀,必不從敵人手中拯救他們。這是耶和華說的。」

7於是,我牧養這群最困苦的待宰之羊。我拿了兩根杖,一根叫「恩惠」,一根叫「聯合」,開始牧養羊群。 8我在一個月之內除掉了三個牧人。

然而,我厭煩羊群,他們也厭惡我。 9於是我說:「我不再牧養你們了。要死的就死吧,要滅亡的就滅亡吧,讓剩下的互相吞吃吧。」 10然後,我拿起那根叫「恩惠」的杖,把它折斷,以廢除我與萬民所立的約。 11約就在當天廢除了,那些注視著我的困苦羊便知道這是上帝的話。

12我對他們說:「你們若認為好,就給我工錢,不然就算了。」於是,他們給了我三十塊銀子作工錢。 13耶和華對我說:「把這一大筆錢丟給窯戶吧,這就是我在他們眼中的價值!」我便把三十塊銀子丟給聖殿中的窯戶。 14我又把那根叫「聯合」的杖折斷,以斷開猶大以色列之間的手足之情。

15耶和華又對我說:「你再拿起愚昧牧人的器具, 16因為我要使一位牧人在地上興起,他不照顧喪亡的,不尋找失散的,不醫治受傷的,不牧養健壯的,反而吃肥羊的肉,撕掉牠們的蹄子。

17「丟棄羊群的無用牧人有禍了!

願刀砍在他的臂膀和右眼上!

願他的臂膀徹底枯槁,

他的右眼完全失明!」