ዘካርያስ 10 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 10:1-12

እግዚአብሔር ለይሁዳ ይጠነቀቃል

1የበልግ ዝናብ እንዲሰጣችሁ እግዚአብሔርን ጠይቁ፤

ማዕበሉን ደመና የሚያደርግ እግዚአብሔር ነው፤

እርሱ ለሰዎች በቂ ዝናብን፣

ለእያንዳንዱም የምድርን ተክል ይሰጣል።

2ተራፊም አሳሳች ነገር ይናገራል፤

ሟርተኞች የሐሰት ራእይ ያያሉ፤

የውሸት ሕልም ይናገራሉ፤

ከንቱ መጽናናት ይሰጣሉ፤

ስለዚህ ሕዝቡ እንደ በጎች ተቅበዘበዙ፤

እረኛ በማጣትም ተጨነቁ።

3“ቍጣዬ በእረኞች ላይ ነድዷል፤

መሪዎችንም እቀጣለሁ፤

እግዚአብሔር ጸባኦት፣

ለመንጋው ለይሁዳ ቤት ይጠነቀቃልና፤

በጦርነትም ጊዜ እንደ ክብሩ ፈረስ ያደርጋቸዋል።

4ከይሁዳ፣ የማእዘን ድንጋይ፣

የድንኳን ካስማ፣

የጦርነት ቀስት፣

ገዥም ሁሉ ይወጣል።

5ጠላትን መንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ ይረጋግጣሉ፤

በአንድነት10፥5 ወይም ሁሉም ገዦች በአንድነት ማለት ነው 5 እነርሱም እንደ ጦር ሰልፈኛ ይሆናሉ፤

እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ስለሆነ ተዋግተው፤

ፈረሰኞችን ያዋርዳሉ።

6“የይሁዳን ቤት አበረታለሁ፤

የዮሴፍንም ቤት እታደጋለሁ።

ስለምራራላቸው፣

ወደ ቦታቸው እመልሳቸዋለሁ፤

እነርሱም በእኔ እንዳልተተዉ ሰዎች

ይሆናሉ፤

እኔ አምላካቸው እግዚአብሔር ነኝና፣

ጸሎታቸውን እሰማለሁ።

7ኤፍሬማውያን እንደ ኀያላን ሰዎች ይሆናሉ፤

ልባቸውም የወይን ጠጅ እንደ ጠጣ ሰው ሐሤት ያደርጋል።

ልጆቻቸው ያዩታል፤ ደስተኛም ይሆናሉ፤

ልባቸውም በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል።

8በፉጨት እጠራቸዋለሁ፤

በአንድነት እሰበስባቸዋለሁ፤

በርግጥ እቤዣቸዋለሁ፤

እንደ ቀድሞው ይበዛሉ።

9በሕዝቦች መካከል ብበትናቸውም፣

በሩቅ ምድር ሆነው ያስቡኛል፤

እነርሱና ልጆቻቸው ተርፈው፣

በሕይወት ይመለሳሉ።

10ከግብፅ እመልሳቸዋለሁ፤

ከአሦርም እሰበስባቸዋለሁ፤

ወደ ገለዓድና ወደ ሊባኖስ አመጣቸዋለሁ፤

በቂ ስፍራም አይገኝላቸውም።

11በመከራ ባሕር ውስጥ ያልፋሉ፤

የባሕሩ ማዕበል ጸጥ ይላል፤

የአባይም ጥልቅ ሁሉ ይደርቃል።

የአሦር ትምክሕት ይዋረዳል፤

የግብፅም በትረ መንግሥት ያበቃል።

12በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ፤

በስሙም ይመላለሳሉ”

ይላል እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒迦利亞書 10:1-12

耶和華應許拯救以色列

1要在春季向耶和華求雨。

祂創造雷雨,

為世人降下甘霖,

使田間長出青翠之物。

2因為神像說的是虛言,

占卜者講的是謊話,

他們說的是假夢,

他們的安慰是空的。

所以人們如迷失的羊,

因沒有牧人而受苦。

3「我必向牧人發怒,

我必懲罰這些首領10·3 首領」希伯來文作「公山羊」。

因為我——萬軍之耶和華必眷顧我的羊群猶大家,

我必使他們像戰場上的駿馬。

4房角石、帳篷的橛子、戰弓,

以及所有掌權者必出自猶大

5他們必像戰場上的勇士,

將仇敵踐踏在街上的泥土中。

他們必爭戰,

因為耶和華與他們同在。

他們必使敵方的騎兵蒙羞。

6「我必使猶大家強盛,

我必拯救約瑟家。

我必帶他們回到故土,

因為我憐憫他們。

他們必好像從未被我拋棄一樣,

因為我是他們的上帝耶和華,

我必應允他們的禱告。

7以法蓮人必如勇士,

他們必心裡快樂,如同喝了酒,

他們的兒女見狀也必快樂,

他們必因耶和華而歡心。

8「我必吹哨聚集他們,

因為我救贖了他們,

他們必像從前一樣人數眾多。

9雖然我把他們分散到列國,

他們必在遠方想起我,

他們及其子女必得以倖存,

並且回到故土。

10我必從埃及領他們回到故土,

亞述招聚他們,

領他們到基列黎巴嫩

那裡將不夠他們居住。

11祂必經過苦海,

擊打海浪,

尼羅河必乾涸,

亞述的驕傲必掃地,

埃及的勢力必滅沒。

12我必讓他們靠著我強盛,

他們必奉我的名行事。

這是耶和華說的。」