ኤርምያስ 5 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 5:1-31

ቅን ሰው አለመገኘቱ

1“በኢየሩሳሌም መንገዶች እስቲ ውጡ፤ ወደ ላይ ወደ ታችም ውረዱ፤

ዙሪያውን ተመልከቱ ቃኙ፤

በአደባባይዋም ፈልጉ፤

እውነትን የሚሻና በቅንነት የሚሄድ፣

አንድ ሰው እንኳ ብታገኙ፣

እኔ ይህችን ከተማ እምራታለሁ።

2‘ሕያው እግዚአብሔርን!’ ቢሉም፣

የሚምሉት በሐሰት ነው።”

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐይኖችህ እውነትን አይመለከቱምን?

አንተ መታሃቸው፤ እነርሱ ግን አልተሰማቸውም፤

አደቀቅሃቸው፤ እነርሱ ግን አልታረሙም፤

ፊታቸውን ከድንጋይ ይልቅ አጠነከሩ

በንስሓ ለመመለስም አልፈለጉም።

4እኔም በልቤ እንዲህ አልሁ፤ “እነዚህ ድኾች ናቸው፤

ሞኞች ናቸው፤

የእግዚአብሔርን መንገድ፣

የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና።

5ስለዚህ ወደ ታላላቆቹ እሄዳለሁ፤

ለእነርሱም እናገራለሁ፤

በርግጥ እነርሱ የእግዚአብሔርን መንገድ፣

የአምላካቸውንም ሕግ ያውቃሉና።”

ነገር ግን እነርሱም ቢሆኑ ያው እንደዚያው ቀንበሩን ሰብረዋል፤

እስራቱንም በጥሰዋል።

6ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰባብራቸዋል፣

የበረሓ ተኵላም ይቦጫጭቃቸዋል፤

ብቅ የሚለውን ሰው ሁሉ ለመገነጣጠል፣

ነብር በከተሞቻቸው ዙሪያ ያደባል፤

ዐመፃቸው ታላቅ፣

ክሕደታቸው ብዙ ነውና።

7“ታዲያ፣ እንዴት ይቅር ልልሽ እችላለሁ?

ልጆችሽ ትተውኛል፤

እውነተኛውን አምላክ ትተው አማልክት ባልሆኑት ምለዋል፤

እስኪጠግቡ ድረስ መገብኋቸው፤

እነርሱ ግን አመነዘሩ፤

ወደ ጋለሞቶችም ቤት ተንጋጉ።

8እንደ ተቀለበ ብርቱ ድንጉላ ፈረስ ሆኑ፤

እያንዳንዱም የሌላውን ሚስት ተከትሎ አሽካካ።

9ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀጣቸውምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“እኔ ራሴ እንደዚህ ዐይነቱን ሕዝብ

አልበቀልምን?

10“ወደ ወይን አትክልቷ ስፍራ ገብታችሁ አበላሹት፤

ነገር ግን ፈጽማችሁ አታጥፉት፤

ቅርንጫፎቿን ገነጣጥሉ፤

የእግዚአብሔር አይደሉምና፤

11የእስራኤል ቤትና የይሁዳ ቤት፣

ፈጽመው ከድተውኛል፤”

ይላል እግዚአብሔር

12በእግዚአብሔር ላይ ሐሰትን ተናገሩ፤

እንዲህም አሉ፤ “እሱ ምንም አያደርግም!

ክፉ ነገር አይደርስብንም፤

ሰይፍም ራብም አናይም፤

13ነቢያቱ ነፋስ እንጂ ሌላ ነገር አይደሉም፤

ቃሉም በውስጣቸው የለም፤

ያሉት ሁሉ በእነርሱ ላይ ይመለስ።”

14ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሕዝቡ ይህን ቃል ስለ ተናገረ፣

ቃሌን በአፍህ ውስጥ የሚፋጅ እሳት፣

ይህንም ሕዝብ ማገዶ አደርጋለሁ፤

እሳቱም ይበላቸዋል፤

15የእስራኤል ቤት ሆይ፤” ይላል እግዚአብሔር

“ከሩቅ ሕዝብን አመጣባችኋለሁ፤

ጥንታዊና ብርቱ፣

ቋንቋውን የማታውቁት፣ ንግግሩንም

የማትረዱት ሕዝብ ነው።

16የፍላጻቸው ሰገባ እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፤

ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎች ናቸው።

17ሰብልህንና ምግብህን ጠራርገው ይበሉብሃል፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆችህን ይውጣሉ፤

በጎችህንና ከብቶችህን ይፈጃሉ፤

የወይን ተክሎችህንና የበለስ ዛፎችህን ያወድማሉ፤

የታመንህባቸውንም የተመሸጉ ከተሞች

በሰይፍ ያጠፏቸዋል።

18“ይሁን እንጂ፣ በዚያን ዘመን እንኳ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ፈጽሜ አላጠፋችሁም። 19ሕዝቡ፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ይህን ሁሉ ነገር ለምን አደረገብን?’ ብለው ቢጠይቁ፣ ‘እኔን፣ እንደ ተዋችሁኝና በራሳችሁ ምድር ባዕዳን አማልክትን እንዳገለገላችሁ፣ እንደዚሁ የእናንተ ባልሆነ ምድር ባዕዳንን ታገለግላላችሁ’ ትላቸዋለህ።

20“በያዕቆብ ቤት ይህን አሰሙ፤

በይሁዳም እንዲህ ብላችሁ ዐውጁ፤

21እናንት ዐይን እያላችሁ የማታዩ፣

ጆሮ እያላችሁ የማትሰሙ፣

ሞኞችና የማታስተውሉ ሰዎች ይህን ስሙ፤

22ልትፈሩኝ አይገባችሁምን?” ይላል እግዚአብሔር

“በእኔ ፊት ልትንቀጠቀጡስ አይገባምን?

ለዘላለም ዐልፎት መሄድ እንዳይችል፣

አሸዋን ለባሕር ድንበር አደረግሁ፤

ማዕበሉ እየጋለበ ቢመጣ ከዚያ አያልፍም፤

ሞገዱ ቢጮኽም ሊያቋርጠው አይችልም።

23ይህ ሕዝብ ግን የሸፈተና እልኸኛ ልብ አለው፤

መንገድ ለቆ ሄዷል፤

24በልባቸውም፣

‘የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ በጊዜው የሚያዘንበውን፣

መከርን በወቅቱ የሚያመጣልንን፣

አምላካችንን እግዚአብሔርን እንፍራ’ አላሉም።

25በደላችሁ እነዚህን አስቀርቶባችኋል።

ኀጢአታችሁ መልካሙን ነገር ከልክሏችኋል።

26“በሕዝቤ መካከል ክፉ ሰዎች አሉና፤

ወፍ እንደሚያጠምዱ ሰዎች፣

ወጥመድ ዘርግተው ሰው እንደሚይዙ ሰዎችም ያደባሉ።

27ወፎች እንደ ሞሉት ጐጆ፣

ቤታቸው በማጭበርበር የተሞላ ነው፤

ባለጠጎችና ኀያላን ሆነዋል፤

28ወፍረዋል፤ ሠብተዋልም።

ክፋታቸው ገደብ የለውም፤

ወላጅ የሌላቸው ፍትሕ እንዲያገኙ

አልቆሙላቸውም፤

ለድኾችም መብት አልተከራከሩም።

29ስለ እነዚህ ነገሮች ልቀጣቸው አይገባኝምን?”

ይላል እግዚአብሔር

እንዲህ ዐይነቶቹን ሕዝብ፣

እኔ ራሴ ልበቀላቸው አይገባኝምን?

30“የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ነገር

በምድሪቱ ላይ ሆኗል፤

31ነቢያት በሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤

ካህናት በነቢያቱ ምክር ያስተዳድራሉ፤

ሕዝቤም እንዲህ ያለውን ይወድዳሉ፤

ፍጻሜው ሲደርስ ግን ምን ታደርጉ ይሆን?”

King James Version

Jeremiah 5:1-31

1Run ye to and fro through the streets of Jerusalem, and see now, and know, and seek in the broad places thereof, if ye can find a man, if there be any that executeth judgment, that seeketh the truth; and I will pardon it. 2And though they say, The LORD liveth; surely they swear falsely. 3O LORD, are not thine eyes upon the truth? thou hast stricken them, but they have not grieved; thou hast consumed them, but they have refused to receive correction: they have made their faces harder than a rock; they have refused to return. 4Therefore I said, Surely these are poor; they are foolish: for they know not the way of the LORD, nor the judgment of their God. 5I will get me unto the great men, and will speak unto them; for they have known the way of the LORD, and the judgment of their God: but these have altogether broken the yoke, and burst the bonds. 6Wherefore a lion out of the forest shall slay them, and a wolf of the evenings shall spoil them, a leopard shall watch over their cities: every one that goeth out thence shall be torn in pieces: because their transgressions are many, and their backslidings are increased.5.6 evenings: or, deserts5.6 are increased: Heb. are strong

7¶ How shall I pardon thee for this? thy children have forsaken me, and sworn by them that are no gods: when I had fed them to the full, they then committed adultery, and assembled themselves by troops in the harlots’ houses. 8They were as fed horses in the morning: every one neighed after his neighbour’s wife. 9Shall I not visit for these things? saith the LORD: and shall not my soul be avenged on such a nation as this?

10¶ Go ye up upon her walls, and destroy; but make not a full end: take away her battlements; for they are not the LORD’s. 11For the house of Israel and the house of Judah have dealt very treacherously against me, saith the LORD. 12They have belied the LORD, and said, It is not he; neither shall evil come upon us; neither shall we see sword nor famine: 13And the prophets shall become wind, and the word is not in them: thus shall it be done unto them. 14Wherefore thus saith the LORD God of hosts, Because ye speak this word, behold, I will make my words in thy mouth fire, and this people wood, and it shall devour them. 15Lo, I will bring a nation upon you from far, O house of Israel, saith the LORD: it is a mighty nation, it is an ancient nation, a nation whose language thou knowest not, neither understandest what they say. 16Their quiver is as an open sepulchre, they are all mighty men. 17And they shall eat up thine harvest, and thy bread, which thy sons and thy daughters should eat: they shall eat up thy flocks and thine herds: they shall eat up thy vines and thy fig trees: they shall impoverish thy fenced cities, wherein thou trustedst, with the sword. 18Nevertheless in those days, saith the LORD, I will not make a full end with you.

19¶ And it shall come to pass, when ye shall say, Wherefore doeth the LORD our God all these things unto us? then shalt thou answer them, Like as ye have forsaken me, and served strange gods in your land, so shall ye serve strangers in a land that is not yours.

20Declare this in the house of Jacob, and publish it in Judah, saying, 21Hear now this, O foolish people, and without understanding; which have eyes, and see not; which have ears, and hear not:5.21 understanding: Heb. heart 22Fear ye not me? saith the LORD: will ye not tremble at my presence, which have placed the sand for the bound of the sea by a perpetual decree, that it cannot pass it: and though the waves thereof toss themselves, yet can they not prevail; though they roar, yet can they not pass over it? 23But this people hath a revolting and a rebellious heart; they are revolted and gone. 24Neither say they in their heart, Let us now fear the LORD our God, that giveth rain, both the former and the latter, in his season: he reserveth unto us the appointed weeks of the harvest.

25¶ Your iniquities have turned away these things, and your sins have withholden good things from you. 26For among my people are found wicked men: they lay wait, as he that setteth snares; they set a trap, they catch men.5.26 they lay…: or, they pry as fowlers lie in wait 27As a cage is full of birds, so are their houses full of deceit: therefore they are become great, and waxen rich.5.27 cage: or, coop 28They are waxen fat, they shine: yea, they overpass the deeds of the wicked: they judge not the cause, the cause of the fatherless, yet they prosper; and the right of the needy do they not judge. 29Shall I not visit for these things? saith the LORD: shall not my soul be avenged on such a nation as this?

30¶ A wonderful and horrible thing is committed in the land;5.30 A wonderful…: or, Astonishment and filthiness 31The prophets prophesy falsely, and the priests bear rule by their means; and my people love to have it so: and what will ye do in the end thereof?5.31 bear…: or, take into their hands