ኤርምያስ 4 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 4:1-31

1“እስራኤል ሆይ፤ ብትመለስ፣

ወደ እኔ ብትመለስ”

ይላል እግዚአብሔር

“አስጸያፊ ነገሮችህን ከፊቴ ብታስወግድ፣

ባትናወጥ ብትቆምም፣

2በእውነት፣ በቅንነትና በጽድቅ፣

‘ሕያው እግዚአብሔርን!’ ብለህ ብትምል፣

አሕዛብ በእርሱ ይባረካሉ፤

በእርሱም ይከበራሉ።”

3እግዚአብሔር ለይሁዳና ለኢየሩሳሌም ሰዎች እንዲህ ይላል፤

“ዕዳሪውን መሬት ዕረሱ፤

በእሾኽም መካከል አትዝሩ።

4እናንተ የይሁዳ ሰዎች፣ የኢየሩሳሌምም ነዋሪዎች፤

ለእግዚአብሔር ተገረዙ፤

የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ፤

አለዚያ ስለ ሠራችሁት ክፋት፣

ቍጣዬ እንደ እሳት ይንበለበላል፤

ሊገታውም የሚችል የለም።

ጥፋት ከሰሜን መምጣቱ

5“ ‘በምድሪቱ ሁሉ መለከትን ንፉ’ ብላችሁ፤

በይሁዳ ተናገሩ፣ በኢየሩሳሌም ዐውጁ፤

ጩኹ፤ እንዲህም በሉ፤

‘በአንድነት ተሰብሰቡ፤

ወደ ተመሸጉት ከተሞች እንሽሽ!’

6ወደ ጽዮን ለመግባት ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤

ቶሎ ሸሽታችሁ አምልጡ፤

ከሰሜን መቅሠፍትን፣

ታላቅ ጥፋትን አመጣለሁና።”

7አንበሳ ከደኑ ወጥቷል፤

ሕዝብንም የሚያጠፋ ተሰማርቷል፤

ምድርሽን ባዶ ሊያደርግ፣

ከስፍራው ወጥቷል።

ከተሞችሽ ፈራርሰው ይወድቃሉ፤

ያለ ነዋሪም ይቀራሉ።

8ስለዚህ ማቅ ልበሱ፤

ዕዘኑ፤ ዋይ በሉ፤

የእግዚአብሔር አስፈሪ ቍጣ፣

ከእኛ አልተመለሰምና።

9“በዚያ ቀን” ይላል እግዚአብሔር

“ንጉሡና ሹማምቱ ወኔ ይከዳቸዋል፤

ካህናቱ ድንጋጤ ይውጣቸዋል፤

ነቢያቱም ብርክ ይይዛቸዋል።”

10እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰይፍ ዐንገታቸው ላይ ተቃጥቶ ሳለ፣ ‘ሰላም ይሆንላችኋል’ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ለምን እጅግ አታለልህ?” አልሁ።

11በዚያን ጊዜ፣ ለእዚህ ሕዝብና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ተብሎ ይነገራል፤ “ለማበጠር ወይም ለማጥራት ሳይሆን፣ ከዚያ የበረታ የሚጠብስ ደረቅ ነፋስ በምድረ በዳ ካሉት ባድማ ኰረብቶች ወደ ወገኔ ሴት ልጅ 12በእኔ ትእዛዝ ይነፍሳል፤4፥12 ወይም በእኔ ትእዛዝ የሚመጣው እንግዲህ ፍርዴን በእነርሱ ላይ እናገራለሁ።”

13እነሆ፤ እንደ ደመና ይንሰራፋል፤

ሠረገሎቹ እንደ ዐውሎ ነፋስ ይመጣሉ፤

ፈረሶቹም ከንስር ይፈጥናሉ፤

መጥፋታችን ነውና ወዮልን!

14ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እንድትድኚ ከልብሽ ክፋት ታጠቢ፤

እስከ መቼ ክፉ ሐሳብ በውስጥሽ ይኖራል?

15ድምፅ ከዳን ይሰማልና፤

ከኤፍሬም ተራሮችም ጥፋትን ያውጃል።

16“ይህን ለሕዝቦች አሳውቁ፤

ለኢየሩሳሌምም እንዲህ ብላችሁ በይፋ ንገሩ፤

‘ከብበው የሚያስጨንቁ ከሩቅ አገር ይመጣሉ፤

በይሁዳ ከተሞችም ላይ ይደነፋሉ፤

17ሰብል እንደሚጠብቁ ሰዎች ይከቧታል፤

በእኔ ላይ ዐምፃለችና፤’ ”

ይላል እግዚአብሔር

18“የገዛ መንገድሽና ተግባርሽ፣

ይህን አምጥቶብሻል፤

ይህም ቅጣትሽ ነው፤

ምንኛ ይመርራል!

እንዴትስ ልብ ይሰብራል!”

19ወይ አበሳዬ! ወይ አበሳዬ!

ሥቃይ በሥቃይ ላይ ሆነብኝ፤

አወይ፣ የልቤ ጭንቀት!

ልቤ ክፉኛ ይመታል፤

ዝም ማለት አልችልም፤

የመለከትን ድምፅ፣

የጦርነትንም ውካታ ሰምቻለሁና።

20ጥፋት በጥፋት ላይ ይመጣል፤

ምድሪቱም በሞላ ባድማ ትሆናለች፤

ድንኳኔ በድንገት፣

መጠለያዬም በቅጽበት ጠፋ።

21እስከ መቼ የጦርነት ዐርማ እመለከታለሁ?

እስከ መቼስ የመለከት ድምፅ እሰማለሁ?

22“ሕዝቤ ተላሎች ናቸው፤

እኔን አያውቁኝም።

ማስተዋል የጐደላቸው፣

መረዳትም የማይችሉ ልጆች ናቸው።

ክፋትን ለማድረግ ጥበበኞች፣

መልካም መሥራት ግን የማያውቁ።”

23ምድርን ተመለከትሁ፤

እነሆ ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች፤

ሰማያትንም አየሁ፣

ብርሃናቸው ጠፍቷል።

24ተራሮችን ተመለከትሁ፣

እነሆ ይንቀጠቀጡ ነበር፤

ኰረብቶችም ሁሉ ተናጡ።

25አየሁ፤ ሰው አልነበረም፤

የሰማይ ወፎች ሁሉ በረው ጠፍተዋል።

26ተመለከትሁ፤ እነሆም፣ ፍሬያማው ምድር በረሓ ሆነ፤

ከተሞቹ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት፣

ከብርቱ ቍጣው የተነሣ ፈራረሱ።

27እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ምድር ሁሉ ባድማ ትሆናለች፤

ነገር ግን ፈጽሜ አላጠፋትም።

28ስለዚህ ምድር ታለቅሳለች፤

ሰማያትም በላይ ይጨልማሉ፤

ተናግሬአለሁ፤ ሐሳቤን አልለውጥም፤

ወስኛለሁ፤ ወደ ኋላም አልልም።”

29ከፈረሰኞችና ከቀስተኞች ጩኸት የተነሣ፣

ከተማ ሁሉ ይሸሻል፤

አንዳንዶች ደን ውስጥ ይገባሉ፤

ሌሎችም ቋጥኝ ላይ ይወጣሉ፤

ከተሞች ሁሉ ባዶ ቀርተዋል፤

የሚኖርባቸውም የለም።

30አንቺ ለጥፋት የተዳረግሽ ሆይ፤ ምን መሆንሽ ነው?

ቀይ ቀሚስ የለበስሽው ለምንድን ነው?

ለምን በወርቅ አጌጥሽ?

ዐይኖችሽንስ ለምን ተኳልሽ?

እንዲያው በከንቱ ተሽሞንሙነሻል፤

የተወዳጀሻቸው ንቀውሻልና፤

ነፍስሽንም ሊያጠፉ ይፈልጋሉ።

31የበኵር ልጇን ለመውለድ እንደምታምጥ፣

በወሊድ እንደምትጨነቅ ሴት ድምፅ ሰማሁ፤

የጽዮን ሴት ልጅ ትንፋሽ ዐጥሯት ስትጮኽ፣

እጇን ዘርግታ፣

“ወዮልኝ! ተዝለፈለፍሁ፣

በነፍሰ ገዳዮች እጅ ወደቅሁ!” ስትል ሰማሁ።

King James Version

Jeremiah 4:1-31

1If thou wilt return, O Israel, saith the LORD, return unto me: and if thou wilt put away thine abominations out of my sight, then shalt thou not remove. 2And thou shalt swear, The LORD liveth, in truth, in judgment, and in righteousness; and the nations shall bless themselves in him, and in him shall they glory.

3¶ For thus saith the LORD to the men of Judah and Jerusalem, Break up your fallow ground, and sow not among thorns. 4Circumcise yourselves to the LORD, and take away the foreskins of your heart, ye men of Judah and inhabitants of Jerusalem: lest my fury come forth like fire, and burn that none can quench it, because of the evil of your doings.

5Declare ye in Judah, and publish in Jerusalem; and say, Blow ye the trumpet in the land: cry, gather together, and say, Assemble yourselves, and let us go into the defenced cities. 6Set up the standard toward Zion: retire, stay not: for I will bring evil from the north, and a great destruction.4.6 retire: or, strengthen4.6 destruction: Heb. breaking 7The lion is come up from his thicket, and the destroyer of the Gentiles is on his way; he is gone forth from his place to make thy land desolate; and thy cities shall be laid waste, without an inhabitant. 8For this gird you with sackcloth, lament and howl: for the fierce anger of the LORD is not turned back from us. 9And it shall come to pass at that day, saith the LORD, that the heart of the king shall perish, and the heart of the princes; and the priests shall be astonished, and the prophets shall wonder. 10Then said I, Ah, Lord GOD! surely thou hast greatly deceived this people and Jerusalem, saying, Ye shall have peace; whereas the sword reacheth unto the soul. 11At that time shall it be said to this people and to Jerusalem, A dry wind of the high places in the wilderness toward the daughter of my people, not to fan, nor to cleanse, 12Even a full wind from those places shall come unto me: now also will I give sentence against them.4.12 a full…: or, a fuller wind than those4.12 give…: Heb. utter judgments 13Behold, he shall come up as clouds, and his chariots shall be as a whirlwind: his horses are swifter than eagles. Woe unto us! for we are spoiled. 14O Jerusalem, wash thine heart from wickedness, that thou mayest be saved. How long shall thy vain thoughts lodge within thee? 15For a voice declareth from Dan, and publisheth affliction from mount Ephraim. 16Make ye mention to the nations; behold, publish against Jerusalem, that watchers come from a far country, and give out their voice against the cities of Judah. 17As keepers of a field, are they against her round about; because she hath been rebellious against me, saith the LORD. 18Thy way and thy doings have procured these things unto thee; this is thy wickedness, because it is bitter, because it reacheth unto thine heart.

19¶ My bowels, my bowels! I am pained at my very heart; my heart maketh a noise in me; I cannot hold my peace, because thou hast heard, O my soul, the sound of the trumpet, the alarm of war.4.19 my very…: Heb. the walls of my heart 20Destruction upon destruction is cried; for the whole land is spoiled: suddenly are my tents spoiled, and my curtains in a moment. 21How long shall I see the standard, and hear the sound of the trumpet? 22For my people is foolish, they have not known me; they are sottish children, and they have none understanding: they are wise to do evil, but to do good they have no knowledge. 23I beheld the earth, and, lo, it was without form, and void; and the heavens, and they had no light. 24I beheld the mountains, and, lo, they trembled, and all the hills moved lightly. 25I beheld, and, lo, there was no man, and all the birds of the heavens were fled. 26I beheld, and, lo, the fruitful place was a wilderness, and all the cities thereof were broken down at the presence of the LORD, and by his fierce anger. 27For thus hath the LORD said, The whole land shall be desolate; yet will I not make a full end. 28For this shall the earth mourn, and the heavens above be black: because I have spoken it, I have purposed it, and will not repent, neither will I turn back from it. 29The whole city shall flee for the noise of the horsemen and bowmen; they shall go into thickets, and climb up upon the rocks: every city shall be forsaken, and not a man dwell therein. 30And when thou art spoiled, what wilt thou do? Though thou clothest thyself with crimson, though thou deckest thee with ornaments of gold, though thou rentest thy face with painting, in vain shalt thou make thyself fair; thy lovers will despise thee, they will seek thy life.4.30 face: Heb. eyes 31For I have heard a voice as of a woman in travail, and the anguish as of her that bringeth forth her first child, the voice of the daughter of Zion, that bewaileth herself, that spreadeth her hands, saying, Woe is me now! for my soul is wearied because of murderers.