ኤርምያስ 45 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 45:1-5

ለባሮክ የተነገረ መልእክት

1በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት በአራተኛው ዓመት፣ ኤርምያስ በቃል የነገረውን ባሮክ በብራና ላይ ከጻፈ በኋላ፣ ነቢዩ ኤርምያስ ለኔርያ ልጅ ለባሮክ የተናገረው ይህ ነው፤ 2“ባሮክ ሆይ፤ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይልሃል፤ 3አንተ፣ ‘እግዚአብሔር በሕመሜ ላይ ሐዘን ጨምሮብኛልና ወዮልኝ፤ ከልቅሶዬ ብዛት የተነሣ ደክሜአለሁ፤ ዕረፍትም የለኝም’ ብለሃል።”

4እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እንዲህ በለው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በምድር ሁሉ የገነባሁትን አፈርሳለሁ፤ የተከልሁትን እነቅላለሁ። 5ታዲያ፣ ለራስህ ታላቅ ነገር ትሻለህን? በሰው ልጆች ሁሉ ላይ ጥፋት አመጣለሁና አትፈልገው፤ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ሁሉ ሕይወትህ እንዲተርፍልህ አደርጋለሁ።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 45:1-5

พระเจ้าทรงสัญญากับบารุค

1ในปีที่สี่แห่งรัชกาลเยโฮยาคิมโอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ หลังจากที่บารุคบุตรเนริยาห์ได้บันทึกพระดำรัสลงในม้วนหนังสือตามคำบอกของเยเรมีย์แล้ว ผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์กล่าวกับบารุคบุตรเนริยาห์ว่า 2“บารุคเอ๋ย พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสกับท่านว่า 3เจ้าพูดว่า ‘วิบัติแก่ข้าพเจ้า! ข้าพเจ้าเจ็บปวดอยู่แล้ว องค์พระผู้เป็นเจ้ายังทรงเพิ่มความทุกข์โศกให้ข้าพเจ้าอีก ข้าพเจ้าอ่อนระโหยไปเพราะการครวญครางและไม่ได้พักผ่อน’ ”

4องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “จงบอกบารุคว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่าเราจะทลายสิ่งที่เราสร้างและถอนรากสิ่งที่เราปลูกทั่วดินแดนนี้ 5เช่นนี้แล้วเจ้าควรเสาะหาสิ่งที่ยิ่งใหญ่เพื่อตัวเองหรือ? อย่าเลย เพราะเราจะนำภัยพิบัติมายังประชากรทั้งปวง แต่ไม่ว่าเจ้าจะไปไหน เราจะให้เจ้ารอดชีวิต องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น’ ”