ኤርምያስ 46 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 46:1-28

ስለ ግብፅ የተነገረ መልእክት

1ስለ ሕዝቦች ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

2ስለ ግብፅ፤ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት በአራተኛው ዓመት በኤፍራጥስ ወንዝ በከርከሚሽ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ባሸነፈው በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ኒካዑ ሰራዊት ላይ የተነገረ መልእክት ይህ ነው፤

3“ትልቁንና ትንሹን ጋሻ አዘጋጁ፤

ለውጊያም ውጡ!

4ፈረሶችን ጫኑ፤

በላያቸውም ተቀመጡ!

የራስ ቍር ደፍታችሁ፣

በየቦታችሁ ቁሙ፤

ጦራችሁን ወልውሉ፤

ጥሩራችሁን ልበሱ!

5ነገር ግን ይህ የማየው ምንድን ነው?

እጅግ ፈርተዋል፤

ወደ ኋላ እያፈገፈጉ ነው፤

ብርቱ ጦረኞቻቸው ተሸንፈዋል፤

ዘወር ብለውም ሳያዩ፣

በፍጥነት እየሸሹ ነው፤

በየቦታውም ሽብር አለ፣”

ይላል እግዚአብሔር

6“ፈጣኑ መሸሽ አይችልም፤

ብርቱውም አያመልጥም፤

በሰሜን በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ፣

ተሰናክለው ወደቁ።

7“ይህ እንደ አባይ ወንዝ ሙላት የሚዘልለው፣

እንደ ደራሽ ወንዝ የሚፈስሰው ማነው?

8ግብፅ እንደ አባይ ወንዝ ሙላት ይዘልላል፤

እንደ ደራሽ ወንዝ ይወረወራል፤

‘እወጣለሁ፤ ምድርንም እሸፍናለሁ፤

ከተሞችንና ነዋሪዎቻቸውን አጠፋለሁ’ ይላል።

9ፈረሶች ሆይ ዘልላችሁ ውጡ፤ ሠረገሎችም ሸምጥጡ፤

ጋሻ ያነገባችሁ የኢትዮጵያና46፥9 የላይኛው አባይ አካባቢ ነው የፉጥ ሰዎች፣

ቀስት የገተራችሁ የሉድ ጀግኖች፣

እናንተ ብርቱ ጦረኞች ተነሥታችሁ ዝመቱ።

10ያ ቀን ግን የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ቀን ነው፤

ጠላቶቹን የሚበቀልበት የበቀል ቀን።

ሰይፍ እስኪጠግብ ድረስ ይበላል፤

ጥማቱም እስኪረካ ድረስ ደም ይጠጣል።

በሰሜን ምድር በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር መሥዋዕት አዘጋጅቷልና።

11“ድንግሊቱ የግብፅ ሴት ልጅ ሆይ፤

ወደ ገለዓድ ውጪ፤ የሚቀባ መድኀኒትም አምጪ፤

ነገር ግን መድኀኒት የምታበዢው በከንቱ ነው፤

ፈውስ አታገኚም።

12ሕዝቦች ኀፍረትሽን ይሰማሉ፤

ልቅሶሽም ምድርን ይሞላል።

ጦረኛ በጦረኛው ይደናቀፋል፤

ሁለቱም ተያይዘው ይወድቃሉ።”

13የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር መጥቶ ግብፅን እንደሚወጋ፣ እግዚአብሔር ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረው መልእክት ይህ ነው፤

14“ይህን በግብፅ ተናገር፤ በሚግዶልም አሰማ፤

በሜምፎስና46፥14 ዕብራይስጡ ኖፍ ይላል፤ 19 ይመ። በጣፍናስም እንዲህ ብለህ ዐውጅ፤

‘በቦታችሁ ቁሙ፤ ተዘጋጁም፤

በዙሪያችሁ ያሉትን ሰይፍ ይበላቸዋልና።’

15ጦረኞችህ ለምን ተዘረሩ?

እግዚአብሔር ገፍትሮ ስለሚጥላቸው መቆም አይችሉም።

16ደጋግመው ይሰናከላሉ፣

አንዱም በሌላው ላይ ይወድቃል፤

‘ተነሡ እንሂድ፤

ወደ ሕዝባችንና ወደ ትውልድ አገራችን እንመለስ፤

ከጠላትም ሰይፍ እናምልጥ’ ይላሉ።

17በዚያም የግብፅን ንጉሥ ፈርዖንን፣

‘በተሰጠው ዕድል ያልተጠቀመ፣

አለሁ አለሁ ባይ ደንፊ!’ ብለው ይጠሩታል።”

18ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው ንጉሡ እንዲህ ይላል፤

“በሕያውነቴ እምላለሁ”።

በተራሮች መካከል ያለውን የታቦር ተራራ የሚመስል፣

ባሕርም አጠገብ ያለውን የቀርሜሎስ ተራራ የሚመስል አንድ የሚመጣ አለ።

19እናንተ በግብፅ የምትኖሩ ሆይ፤

በምርኮ ለመወሰድ ጓዛችሁን አሰናዱ፤

ሜምፎስ ፈራርሳ፣

ሰው የማይኖርባት ባድማ ትሆናለችና።

20“ግብፅ ያማረች ጊደር ናት፤

ነገር ግን ተናዳፊ ዝንብ

ከሰሜን ይመጣባታል።

21ቅጥረኞች ወታደሮቿም

እንደ ሠቡ ወይፈኖች ናቸው፤

የሚቀጡበት ጊዜ ስለ ደረሰ፣

ጥፋታቸው ስለ ተቃረበ፣

እነርሱም ወደ ኋላ ተመልሰው በአንድነት ይሸሻሉ፤

በቦታቸውም ጸንተው ሊቋቋሙ አይችሉም።

22ጠላት ገፍቶ ሲመጣባት፣

ግብፅ እንደሚሸሽ እባብ ታፏጫለች፤

ዛፍ እንደሚቈርጡ ሰዎች፣

መጥረቢያ ይዘው ይመጡባታል።

23ጥቅጥቅ ጫካ ቢሆንም፣ ደኗን ይመነጥራሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ብዛታቸው እንደ አንበጣ ነው፤

ሊቈጠሩም አይችሉም።

24የግብፅ ሴት ልጅ ለኀፍረት ትጋለጣለች፤

ለሰሜን ሕዝብም ዐልፋ ትሰጣለች።”

25የእስራኤል አምላክ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በቴብስ46፥25 ወይም ኖእ አምላክ በአሞን ላይ፣ በፈርዖን ላይ፣ በግብፅና በአማልክቷ ላይ፣ በነገሥታቷም ላይ፣ እንዲሁም በፈርዖን በሚታመኑት ላይ ቅጣት አመጣለሁ፤ 26ነፍሳቸውን ለሚሹት ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆርና ለጦር መኰንኖቹ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ግብፅ እንደ ቀድሞው ዘመን የሰው መኖሪያ ትሆናለች” ይላል እግዚአብሔር

27“አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤

እስራኤል ሆይ፤ አትሸበር፤

አንተን ከሩቅ ስፍራ፣

ዘርህንም ተማርኮ ከሄደበት ምድር አድናለሁ።

ያዕቆብም ተመልሶ በሰላምና በርጋታ ይቀመጣል፤

የሚያስፈራውም አይኖርም።

28አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና” ይላል እግዚአብሔር

“አንተን የበተንሁበትን ሕዝብ ሁሉ፣

ፈጽሜ ባጠፋም እንኳ፣

አንተን ግን ፈጽሜ አላጠፋህም።

ተገቢውን ቅጣት እሰጥሃለሁ እንጂ፣

ያለ ቅጣት አልተውህም።”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 46:1-28

พระดำรัสเกี่ยวกับอียิปต์

1องค์พระผู้เป็นเจ้ามีพระดำรัสมาถึงผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์เกี่ยวกับชนชาติต่างๆ ดังนี้

2พระดำรัสเกี่ยวกับอียิปต์

ว่าด้วยกองทัพของฟาโรห์เนโคกษัตริย์แห่งอียิปต์ ซึ่งถูกกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนพิชิตที่คารเคมิชริมฝั่งแม่น้ำยูเฟรติส ในปีที่สี่ของรัชกาลเยโฮยาคิมโอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ความว่า

3“จงเตรียมโล่ทั้งเล็กและใหญ่ของเจ้า

แล้วรุดหน้าออกไปประจัญบาน!

4ผูกอานม้าเถิด

และขี่ควบไป!

จงเข้าประจำที่

พร้อมกับสวมหมวกเกราะ!

จงขัดหอก

จงสวมเสื้อเกราะ!

5เราเห็นอะไร?

พวกเขาตกใจกลัว

พวกเขาถอยทัพ

นักรบของพวกเขาพ่ายแพ้

เขารีบหนี

ไม่หันกลับ

มีความสยดสยองอยู่รอบด้าน”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

6“คนฝีเท้าไวก็หนีไม่พ้น

คนเข้มแข็งก็หนีไม่รอด

ในทิศเหนือริมฝั่งแม่น้ำยูเฟรติส

พวกเขาสะดุดและล้มลง

7“นี่ใครกันหนอซึ่งพุ่งขึ้นมาเหมือนลำน้ำไนล์

เหมือนแม่น้ำที่เชี่ยวกราก?

8อียิปต์พุ่งขึ้นเหมือนลำน้ำไนล์

เหมือนแม่น้ำที่เชี่ยวกราก

อียิปต์คุยโอ่ว่า ‘ข้าจะพุ่งขึ้นปกคลุมโลก

ข้าจะทำลายนครต่างๆ และประชากรของนครเหล่านั้น’

9ม้าทั้งหลายเอ๋ย จงบุกเข้าไปเถิด!

พลรถรบเอ๋ย จงเร่งขับรถรบอย่างเร็วรี่!

นักรบเอ๋ย จงรุดหน้าเข้าไป

ทั้งชาวคูช46:9 คือ ตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์และชาวพูตซึ่งถือโล่

ชาวลิเดียซึ่งโก่งธนู

10แต่วันนั้นเป็นวันแห่งองค์พระผู้เป็นเจ้า พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์

วันแห่งการแก้แค้น เพื่อแก้แค้นศัตรูของพระองค์

ดาบจะฟาดฟันจนหนำใจ

และอาบเลือดจนชุ่มโชก

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้า พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์จะได้รับเครื่องบูชา

ในแดนภาคเหนือริมฝั่งแม่น้ำยูเฟรติส

11“ธิดาพรหมจารีแห่งอียิปต์46:11 คือ ชาวอียิปต์เอ๋ย

ขึ้นไปรับยาที่กิเลอาดสิ

แต่เจ้าเยียวยาไปก็เปล่าประโยชน์

บำบัดรักษาอย่างไรก็ไม่หาย

12ประชาชาติทั้งหลายจะได้ยินถึงความอัปยศของเจ้า

เสียงร่ำไห้ของเจ้าจะระงมไปทั่วแผ่นดินโลก

นักรบจะสะดุดทับกัน

และล้มลงด้วยกัน”

13พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าซึ่งมีมาถึงผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์เรื่องที่กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนจะมาโจมตีอียิปต์ความว่า

14“จงประกาศในอียิปต์ ป่าวร้องในมิกดล

และในเมมฟิส46:14 ภาษาฮีบรูว่าโนฟ เช่นเดียวกับข้อ 19กับทาห์ปานเหสว่า

‘จงเข้าประจำที่และเตรียมพร้อม

เพราะดาบจะฟาดฟันบรรดาผู้ที่อยู่รอบตัวเจ้า’

15เหตุใดนักรบของเจ้าจึงถูกปราบราบคาบ?

พวกเขาไม่อาจยืนหยัดเพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะผลักเขาล้มลง

16นักรบทั้งหลายจะล้มลุกคลุกคลาน

ล้มทับกัน

และพวกเขาพูดกันว่า ‘ลุกขึ้นเถิด ให้เรากลับบ้านเกิดเมืองนอน

ไปหาพี่น้องร่วมชาติของเรา

หนีให้พ้นดาบของผู้กดขี่ข่มเหง’

17ที่นั่นพวกเขาจะร้องว่า

‘ฟาโรห์กษัตริย์แห่งอียิปต์ดีแต่โวยวาย

เขาพลาดโอกาสของตนแล้ว’”

18องค์กษัตริย์ผู้ทรงพระนามว่าพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า

“เรามีชีวิตอยู่แน่ฉันใด

ผู้หนึ่งซึ่งสูงตระหง่านเหมือนภูเขาทาโบร์

เหมือนภูเขาคารเมลริมทะเลนั้นจะมา

19พวกเจ้าผู้อาศัยอยู่ในอียิปต์

จงเก็บข้าวของเตรียมเป็นเชลยเถิด

เพราะเมมฟิสจะกลายเป็นซากปรักหักพัง

ถูกทิ้งร้างไม่มีผู้อยู่อาศัย

20“อียิปต์คือวัวสาวตัวงาม

แต่จะมีเหลือบจากทางเหนือ

มาต่อสู้กับมัน

21ทหารรับจ้างในกองทัพอียิปต์

เหมือนวัวที่ขุนจนอ้วน

พวกเขาก็จะหันกลับแตกหนีไปเช่นกัน

พวกเขาจะไม่ยืนหยัดอยู่

เพราะวันหายนะกำลังจะมาถึงเขาแล้ว

เป็นเวลาที่พวกเขาจะถูกลงโทษ

22อียิปต์ส่งเสียงเหมือนงูที่เลื้อยหนี

ขณะที่ศัตรูยกกำลังบุกเข้ามา

พวกเขาถือขวานบุกเข้ามา

เหมือนคนโค่นต้นไม้

23เขาจะโค่นป่าของอียิปต์”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

“แม้จะหนาทึบ

พวกเขามีจำนวนมหาศาลนับไม่ถ้วน

มากกว่าทัพตั๊กแตน

24ธิดาแห่งอียิปต์46:24 คือ ชาวอียิปต์จะอัปยศอดสู

ตกอยู่ในกำมือของคนจากทางเหนือ”

25พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า “เรากำลังจะลงโทษเทพเจ้าอาโมนแห่งเมืองเธเบส46:25 ภาษาฮีบรูว่าโน ลงโทษฟาโรห์ ดินแดนอียิปต์ บรรดาเทพเจ้าและกษัตริย์ทั้งปวง และบรรดาคนที่พึ่งฟาโรห์ 26เราจะมอบพวกเขาแก่ผู้หมายเอาชีวิตพวกเขา แก่กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนและทหารของเขา แต่ต่อมาภายหลัง อียิปต์จะมีผู้อยู่อาศัยเหมือนในอดีตที่ผ่านมา” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

27“ยาโคบผู้รับใช้ของเราเอ๋ย อย่ากลัวเลย

อิสราเอลเอ๋ย อย่าเสียขวัญเลย

เราจะช่วยเจ้าจากแดนไกลอย่างแน่นอน

จะช่วยลูกหลานของเจ้าจากดินแดนที่เขาตกเป็นเชลย

ยาโคบจะมีสันติสุขและความมั่นคงอีกครั้ง

และจะไม่มีใครทำให้เขาหวาดกลัว

28ยาโคบผู้รับใช้ของเราเอ๋ย อย่ากลัวเลย

เพราะเราอยู่กับเจ้า” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

“ถึงแม้เราจะทำลายล้างมวลประชาชาติ

ที่เราทำให้พวกเจ้ากระจัดกระจายเข้าไปนั้นจนหมดสิ้น

แต่เราจะไม่ทำลายล้างเจ้าให้สิ้นไป

เราจะตีสั่งสอนเจ้า แต่ก็ด้วยความยุติธรรมเท่านั้น

เราจะไม่ปล่อยให้เจ้าลอยนวลพ้นโทษไป”