ኢያሱ 24 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 24:1-33

ቃል ኪዳኑ በሴኬም ታደሰ

1ከዚያም ኢያሱ የእስራኤልን ነገዶች ሁሉ በሴኬም ሰበሰበ፤ የእስራኤልንም ሽማግሌዎች፣ መሪዎች፣ ፈራጆችና ሹማምት ጠራ፤ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት ቆሙ።

2ኢያሱም ሕዝቡን ሁሉ እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የቀድሞ አባቶቻችሁ፣ የአብርሃምንና የናኮርን አባት ታራን ጨምሮ ከብዙ ዘመን በፊት ከወንዙ ማዶ ኖሩ24፥2 በዚህ እንዲሁም ቍጥር 3፡14 እና 15 ላይ የተጠቀሰው የኤፍራጥስ ወንዝ ነው።፤ ሌሎችንም አማልክት አመለኩ። 3እኔ ግን አባታችሁን አብርሃምን ከወንዙ ማዶ ካለው ምድር አምጥቼ፣ በከነዓን ምድር ሁሉ መራሁት፤ ዘሮቹን አበዛሁለት፤ ይስሐቅንም ሰጠሁት። 4ለይስሐቅ ያዕቆብንና ዔሳውን ሰጠሁት፤ ለዔሳውም ኰረብታማውን የሴይርን ምድር ርስት አድርጌ ሰጠሁት፤ ያዕቆብና ልጆቹ ግን ወደ ግብፅ ወረዱ።

5“ ‘ከዚያም ሙሴንና አሮንን ላክሁ፤ ባመጣሁት መቅሠፍት ግብፃውያንን አስጨንቄ፣ እናንተን ከዚያ አወጣኋችሁ። 6አባቶቻችሁን ከግብፅ ባወጣኋቸው ጊዜ፣ ወደ ባሕሩ መጣችሁ፤ ግብፃውያንም በሠረገሎችና24፥6 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይቻላል። በፈረሰኞች እስከ ቀይ ባሕር24፥6 ዕብራይስጡ ያም ሳውፍ ይላል፤ ይኸውም የደንገል ባሕር ማለት ነው። ድረስ ተከታተሏቸው። 7እነርሱ ግን ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም በእናንተና በግብፃውያን መካከል ጨለማ እንዲሆን አደረገ። ባሕሩን በላያቸው አመጣ፤ አሰጠማቸውም። በግብፃውያን ላይ ያደረግሁትንም ራሳችሁ በዐይናችሁ አያችሁ፤ በምድረ በዳም ብዙ ጊዜ ኖራችሁ።

8“ ‘በምሥራቅ ዮርዳኖስ ወደሚኖሩት ወደ አሞራውያን ምድር አመጣኋችሁ፤ እነርሱ ወጓችሁ፤ እኔ ግን አሳልፌ በእጃችሁ ሰጠኋቸው፤ ከፊታችሁ አጠፋኋቸው፤ እናንተም ምድራቸውን ወረሳችሁ። 9የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ፣ እስራኤልን ለመውጋት ተነሣ፣ እናንተንም መጥቶ ይረግማችሁ ዘንድ ወደ ቢዖር ልጅ ወደ በለዓም መልእክተኛ ላከ፤ 10እኔ ግን በለዓምን ልሰማው አልፈለግሁም፤ ስለዚህ ደግሞ ደጋግሞ መረቃችሁ፤ እኔም፤ ከባላቅ እጅ ታደግኋችሁ።

11“ ‘ከዚያም ዮርዳኖስን ተሻገራችሁ፤ ወደ ኢያሪኮ መጣችሁ፤ አሞራውያን፣ ፌርዛውያን፣ ከነዓናውያን፣ ኬጢያውያን፣ ጌርጌሳውያን፣ ኤዊያውያንና ኢያቡሳውያን እንደ ወጓችሁ ሁሉ፣ የኢያሪኮም ነዋሪዎች ወጓችሁ። 12በፊታችሁ ተርብ ላክሁ፤ ይህም እነርሱንና ሁለቱን የአሞራውያን ነገሥታት ጭምር ከፊታችሁ አሳደደ፤ ይህ ደግሞ በራሳችሁ ሰይፍና ቀስት ያደረጋችሁት አይደለም። 13ስለዚህ ያልደከማችሁበትን ምድርና ያልሠራችኋቸውን ከተሞች ሰጠኋችሁ። እነሆ፣ በከተሞቹ ትኖራላችሁ፤ ካልተከላችሁት የወይን ተክልና የወይራ ዛፍ ትበላላችሁ።’

14“አሁንም እግዚአብሔርን ፍሩ፤ በፍጹም ታማኝነትም ተገዙለት። የቀድሞ አባቶቻችሁ ከወንዙ ማዶና በግብፅ ያመለኳቸውን አማልክት ከእናንተ አርቁ፤ እግዚአብሔርን ብቻ አምልኩ። 15እግዚአብሔርን ማምለክ የማያስፈልግ መስሎ ከታያችሁ ግን፣ የቀድሞ አባቶቻችሁ ከወንዙ ማዶ ካመለኳቸው አማልክት ወይም በምድራቸው የምትኖሩባቸው አሞራውያን ከሚያመልኳቸው አማልክት ታመልኩ እንደ ሆነ የምታመልኩትን ዛሬውኑ ምረጡ፤ እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።”

16ከዚያም ሕዝቡ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ሌሎችን አማልእክት ለማምለክ ብለን እግዚአብሔርን መተው ከእኛ ይራቅ። 17እኛንና የቀደሙ አባቶቻችንን ከዚያ ከጦርነት ምድር ከግብፅ ያወጣን፣ በፊታችንም እነዚያን ታላላቅ ምልክቶች ያደረገ ማነው? ራሱ አምላካችን እግዚአብሔር አይደለምን? በጕዟችን ላይና ባለፍንባቸውም ሕዝቦች ሁሉ ዘንድ የጠበቀን እርሱ ነው። 18እንዲሁም እግዚአብሔር በምድሪቱ የሚኖሩትን አሞራውያንን ጨምሮ ሕዝቦችን ሁሉ ከፊታችን አሳደደ፤ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔርን እናመልካለን፤ አምላካችን ነውና።”

19ኢያሱም ሕዝቡን እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔርን ማምለክ አትችሉም፤ እርሱ ቅዱስ አምላክና፤ ቀናተኛም አምላክ ነው፤ ዐመፃችሁን ወይም ኀጢአታችሁን ይቅር አይልም። 20እግዚአብሔርን ትታችሁ ባዕዳን አማልክትን የምታመልኩ ከሆነ፣ መልካም ነገር ካደረገላችሁ በኋላ ተመልሶ ክፉ ነገር ያደርግባችኋል፤ ያጠፋችኋልም።”

21ሕዝቡ ግን ኢያሱን፣ “የለም! እኛ እግዚአብሔርን እናመልካለን” አሉት።

22ከዚያም ኢያሱ፣ “እንግዲህ እግዚአብሔርን ለማምለክ መርጣችኋልና በራሳችሁ ላይ ምስክሮች ናችሁ” አላቸው።

እነርሱም፣ “አዎን ምስክሮች ነን” ሲሉ መለሱ።

23ኢያሱም፣ “እንግዲህ በመካከላችሁ ያሉትን ባዕዳን አማልክት አስወግዱ፤ ልባችሁንም ወደ እስራኤል አምላክ ወደ እግዚአብሔር መልሱ” አላቸው።

24ሕዝቡም ኢያሱን፣ “እኛ አምላካችንን እግዚአብሔርን እናመልካለን፤ እንታዘዝለታለንም” አሉት።

25በዚያን ቀን ኢያሱ ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ፤ የሚመሩበትንም ደንብና ሥርዐት እዚያው ሴኬም ሰጣቸው። 26ኢያሱም እነዚህን ቃሎች በእግዚአብሔር የሕግ መጽሐፍ ጻፋቸው፤ ትልቅ ድንጋይም ወስዶ በባሉጥ ዛፍ ሥር፣ በተቀደሰው በእግዚአብሔር ስፍራ አጠገብ አቆመው።

27ኢያሱም ሕዝቡን ሁሉ፣ “እነሆ፤ ይህ ድንጋይ፣ እግዚአብሔር የተናገረንን ሁሉ ሰምቷል፣ በእኛም ይመሰክርብናል፤ እናንተም በአምላካችሁ ዘንድ እውነተኞች ሆናችሁ ባትገኙ ምስክር ይሆንባችኋል” አላቸው።

ኢያሱ በተሰፋዪቱ ምድር ተቀበረ

24፥29-31 ተጓ ምብ – መሳ 2፥6-9

28ከዚያም ኢያሱ ሕዝቡን ሁሉ ወደየርስቱ እንዲሄድ አሰናበተ።

29ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ባሪያ የነዌ ልጅ ኢያሱ በመቶ ዐሥር ዓመቱ ሞተ። 30በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በምትገኘው፣ ከገዓስ ተራራ በስተ ሰሜን ባለችው በራሱ ርስት በተምናሴራ ቀበሩት።

31ኢያሱ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ፣ ከኢያሱም በኋላ በሕይወት በኖሩትና እግዚአብሔር ለእስራኤል ያደረገውን ሁሉ በሚያውቁት ሽማግሌዎች ዘመን ሁሉ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን አመለኩ።

32እስራኤላውያን ከግብፅ ያወጡት የዮሴፍ ዐፅም፣ ያዕቆብ ከሰኬም አባት ከኤሞር በመቶ ሰቅል24፥32 ዕብራይስጡ አንድ መቶ ከሲታሃስ ይላል፤ ክብደቱና ዋጋው በትክክል የማይታወቅ የገንዘብ ዐይነት ነው። ብር በገዛው በሴኬም ምድር ተቀበረ፤ ይህችም የዮሴፍ ዘሮች ርስት ሆነች።

33እንዲሁም የአሮን ልጅ አልዓዛር ሞተ፤ እርሱም በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በሚገኘው ለልጁ ለፊንሐስ በዕጣ በደረሰው በጊብዓ ምድር ተቀበረ።

New International Reader’s Version

Joshua 24:1-33

The Covenant Is Renewed at Shechem

1Joshua gathered all Israel’s tribes together at Shechem. He sent for the elders, leaders, judges and officials of Israel. They came and stood there in the sight of God.

2Joshua spoke to all the people. He said, “The Lord is the God of Israel. He says, ‘Long ago your people lived east of the Euphrates River. They worshiped other gods there. Your people included Terah. He was the father of Abraham and Nahor. 3I took your father Abraham from the land east of the Euphrates. I led him all through Canaan. I gave him many children and grandchildren. I gave him Isaac. 4To Isaac I gave Jacob and Esau. I gave the hill country of Seir to Esau. But Jacob and his family went down to Egypt.

5“ ‘Then I sent Moses and Aaron. I made the people of Egypt suffer because of the plagues I sent on them. But I brought you out of Egypt. 6When I brought your people out, they came to the Red Sea. The people of Egypt chased them with chariots and with men on horses. They chased them all the way to the sea. 7But your people cried out to me for help. So I put darkness between you and the people of Egypt. I swept them into the sea. It completely covered them. Your own eyes saw what I did to them. After that, you lived in the desert for a long time.

8“ ‘I brought you to the land of the Amorites. They lived east of the Jordan River. They fought against you. But I handed them over to you. I destroyed them to make room for you. Then you took over their land. 9Balak, the son of Zippor, prepared to fight against Israel. Balak was the king of Moab. He sent for Balaam, the son of Beor. Balak wanted Balaam to put a curse on you. 10But I would not listen to Balaam’s curses. So he blessed you again and again. And I saved you from his power.

11“ ‘Then you went across the Jordan River. You came to Jericho. Its people fought against you. So did the Amorites, Perizzites, Canaanites, Hittites, Girgashites, Hivites and Jebusites. But I handed them over to you. 12I sent hornets ahead of you. They drove your enemies out to make room for you. That included the two Amorite kings. You did not do that with your own swords and bows. 13So I gave you a land you had never farmed. I gave you cities you had not built. You are now living in them. And you are eating the fruit of vineyards and olive trees you did not plant.’

14“So have respect for the Lord. Serve him. Be completely faithful to him. Throw away the gods your people worshiped east of the Euphrates River and in Egypt. Serve the Lord. 15But suppose you don’t want to serve him. Then choose for yourselves right now whom you will serve. You can choose the gods your people served east of the Euphrates River. Or you can serve the gods of the Amorites. After all, you are living in their land. But as for me and my family, we will serve the Lord.”

16Then the people answered Joshua, “We would never desert the Lord! We would never serve other gods! 17The Lord our God himself brought us and our parents up out of Egypt. He brought us out of that land where we were slaves. With our own eyes, we saw those great signs he did. He kept us safe on our entire journey. He kept us safe as we traveled through all the nations. 18He drove them out to make room for us. That included the Amorites. They also lived in the land. We too will serve the Lord. That’s because he is our God.”

19Joshua said to the people, “You aren’t able to serve the Lord. He is a holy God. He is a jealous God. He won’t forgive you when you disobey him. He won’t forgive you when you sin against him. 20Suppose you desert the Lord. Suppose you serve the gods that people in other lands serve. If you do, he will turn against you. He will bring trouble on you. He will destroy you, even though he has been good to you.”

21But the people said to Joshua, “No! We will serve the Lord.”

22Then Joshua said, “You are witnesses against yourselves. You have said that you have chosen to serve the Lord.”

“Yes. We are witnesses,” they replied.

23“Now then,” said Joshua, “throw away the statues of the gods that are among you. People from other lands serve those gods. Give yourselves completely to the Lord. He is the God of Israel.”

24Then the people said to Joshua, “We will serve the Lord our God. We will obey him.”

25On that day Joshua made a covenant for the people. There at Shechem he reminded them of its rules and laws. 26He recorded these things in the Book of the Law of God. Then he got a large stone. He set it up in Shechem under the oak tree. It was near the place that had been set apart for the Lord.

27“Look!” he said to all the people. “This stone will be a witness against us. It has heard all the words the Lord has spoken to us. Suppose you aren’t faithful to your God. Then the stone will be a witness against you.”

28Joshua sent the people away. He sent all of them to their own shares of land.

Joshua Is Buried in the Promised Land

29Then Joshua, the servant of the Lord, died. He was the son of Nun. He was 110 years old when he died. 30His people buried him at Timnath Serah on his own property. It’s north of Mount Gaash in the hill country of Ephraim.

31Israel served the Lord as long as Joshua lived. They also served him as long as the elders lived. Those were the elders who lived longer than Joshua did. They had seen for themselves everything the Lord had done for Israel.

32The Israelites had brought Joseph’s bones up from Egypt. They buried his bones at Shechem in the piece of land Jacob had bought. He had bought it from the sons of Hamor. He had paid 100 pieces of silver for it. Hamor was the father of Shechem. That piece of land became the share that belonged to Joseph’s children after him.

33Aaron’s son Eleazar died. He was buried at Gibeah in the hill country of Ephraim. Gibeah had been given to Eleazar’s son Phinehas.