መሳፍንት 1 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 1:1-36

እስራኤላውያን ከቀሩት ከነዓናውያን ጋር ያደረጉት ውጊያ

1ጕኢያሱ ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን፣ “ከነዓናውያንን ለመውጋት ማን ቀድሞ ይውጣልን?” ብለው እግዚአብሔርን ጠየቁ።

2እግዚአብሔርም፣ “ይሁዳ ቀድሞ ይውጣ፤ እነሆ ምድሪቱን በእጁ አሳልፌ ሰጥቼዋለሁ” በማለት መለሰ።

3የይሁዳም ሰዎች ወንድሞቻቸውን የስምዖንን ልጆች፣ “ከነዓናውያንን ለመውጋት ድርሻችን ወደ ሆነው ምድር አብረን እንውጣ፤ እኛም እንደዚሁ ድርሻችሁ ወደ ሆነው ምድር አብረናችሁ እንወጣለን” አሏቸው፤ ስለዚህም የስምዖን ሰዎች አብረዋቸው ሄዱ።

4ይሁዳ በከነዓናውያንና በፌርዛውያን ላይ ወጣ፤ እግዚአብሔርም በእጃቸው አሳልፎ ሰጣቸው፤ ቤዜቅ በተባለውም ስፍራ ዐሥር ሺሕ ሰው ገደሉ። 5በዚህም ኦዶኒቤዜቅን አግኝተው ተዋጉት፤ ከነዓናውያንንና ፌርዛውያንን ድል አደረጉ። 6አዶኒቤዜቅም ከዚያ ሸሸ፤ እነርሱ ግን አሳድደው ያዙት፤ የእጆቹንና የእግሮቹንም አውራ ጣቶች ቈረጡ።

7ከዚያም አዶኒቤዜቅ፣ “የእጃቸውና የእግራቸው አውራ ጣቶች የተቈረጡባቸው ሰባ ነገሥታት ከገበታዬ ሥር የወደቀ ፍርፋሪ ይለቃቅሙ ነበር፤ አሁን ግን እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የፈጸምሁትን አመጣብኝ” አለ፤ እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም አመጡት፤ በዚያም ሞተ።

8የይሁዳ ሰዎች ኢየሩሳሌምን ወግተው ያዟት፤ ከተማዪቱንም በሰይፍ ስለት መተው፣ በእሳት አቃጠሏት።

9ከዚያም በኋላ የይሁዳ ሰዎች በኰረብታማው አገር፣ በኔጌብና በምዕራቡ ኰረብታ ግርጌ የሚኖሩትን ከነዓናውያንን ለመውጋት ወረዱ፤ 10ቀደም ሲል ቂርያት አርባቅ ተብላ በምትጠራው በኬብሮን በሚኖሩት ከነዓናውያን ላይ ዘመቱ፤ ሴሲንን፣ አኪመንንና ተላሚንን ድል አደረጉ።

11ከዚያም ቀደም ሲል ቅርያትሤፍር ተብላ በምትጠራው በዳቤር በሚኖሩት ሰዎች ላይ ዘመቱ። 12ካሌብም፣ “ቅርያት ሤፍርን ወግቶ ለሚይዛት ሰው ልጄን ዓክሳንን እድርለታለሁ” አለ። 13በዚህ ጊዜ የካሌብ ወንድም የቄኔዝ ልጅ ጎቶንያል ከተማዪቱን ያዘ፤ ካሌብም ልጁን ዓክሳንን ዳረለት።

14እርሷም ወደ ጎቶንያል በመጣች ጊዜ፣ አባቷ የዕርሻ መሬት እንዲሰጠው ይለምነው ዘንድ አጥብቃ ነገረችው፤1፥14 ዕብራይስጡ፣ ሰብዓ ሊቃናትና ቩልጌት አጥብቆ ነገረው ይላሉ። ካሌብም እርሷ ከአህያዋ ላይ እንደ ወረደች “ምን እንዳደርግልሽ ትፈልጊያለሽ?” ሲል ጠየቃት።

15እርሷም፣ “እባክህ አንድ ነገር አድርግልኝ፤ በኔጌብ መሬት እንደ ሰጠኸኝ ሁሉ፣ አሁንም የውሃ ምንጭ ስጠኝ” አለችው፤ ካሌብም የላይኛውንና የታችኛውን ምንጮች ሰጣት።

16የቄናዊው የሙሴ ዐማት ዝርያዎች ከዓራድ አጠገብ በኔጌብ ውስጥ በይሁዳ ምድረ በዳ ካሉት ሕዝቦች ጋር አብረው ለመኖር፣ ከይሁዳ ሰዎች ጋር በመሆን ከባለ ዘንባባዋ ከተማ ከኢያሪኮ ወጡ።

17የይሁዳ ሰዎች ከወንድሞቻቸው ከስምዖን ልጆች ጋር ሆነው በጻፋት በሚኖሩት ከነዓናውያን ላይ ዘመቱ፤ ከተማዪቱንም ፈጽሞ ደመሰሷት1፥17 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ነገር ወይም ሰው ሙሉ ለሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው፤ ስለዚህ ከተማዪቱ ሔርማ1፥17 ሔርማ ማለት ጥፋት ማለት ነው ተብላ ተጠራች። 18ደግሞም የይሁዳ ሰዎች ጋዛ፣ አስቀሎና፣ አቃሮን የተባሉትን ከተሞች ከነግዛቶቻቸው ያዙ1፥18 ዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም አልያዙም ይላሉ።

19እግዚአብሔር ከይሁዳ ሰዎች ጋር ነበር፤ ስለዚህ ኰረብታማውን አገር ያዙ፤ ነገር ግን በረባዳው ምድር የሚኖሩት ሰዎች ከብረት የተሠሩ ሠረገሎች ስለ ነበሯቸው ከዚያ አሳድደው ሊያስወጧቸው አልቻሉም። 20ሙሴ ባዘዘው መሠረት ኬብሮን ለካሌብ ተሰጠች፤ እርሱም ሦስቱን የዔናቅ ልጆች ከውስጧ አሳደደ። 21የብንያም ልጆች በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን ኢያቡሳውያንን ከዚያ ሊያስወጧቸው አልቻሉም፤ ስለዚህ ኢያቡሳውያን እስከ ዛሬ ድረስ ከብንያማውያን ጋር በዚያ አብረው ይኖራሉ።

22የዮሴፍ ወገን ደግሞ ቤቴልን ወጉ፤ እግዚአብሔርም ከእነርሱ ጋር ነበር። 23እነርሱም ቀደም ሲል ሎዛ ትባል ወደ ነበረችው ወደ ቤቴል ሰላዮችን በላኩ ጊዜ፣ 24ሰላዮቹም አንድ ሰው ከከተማዪቱ ሲወጣ አይተው፤ “የከተማዪቱን መግቢያ አሳየን፤ እኛም ምሕረት እናደርግልሃለን” አሉት። 25እርሱም አሳያቸው፤ እነርሱም ከሰውየውና ከቤተ ሰቡ በስተቀር የከተማዪቱን ሕዝብ በሰይፍ ስለት ፈጁ። 26ሰውየውም ወደ ኬጢያውያን ምድር ሄዶ ከተማ ሠራ፤ ስሟንም ሎዛ ብሎ ጠራት፤ እስከ ዛሬም የምትጠራው በዚሁ ስም ነው።

27የምናሴ ነገድ ግን በቤትሳን፣ በታዕናክ፣ በዶር፣ በይብለዓም፣ በመጊዶንና በየአካባቢያቸው ያሉት መንደሮች ነዋሪውን ሕዝብ ስላላስወጡ፣ ከነዓናውያን ኑሯቸውን በዚያው ለማድረግ ወሰኑ። 28እስራኤላውያን በበረቱ ጊዜ ግን ከነዓናውያንን የጕልበት ሥራ እንዲሠሩ አስገደዷቸው እንጂ ፈጽሞ አላስወጧቸውም። 29እንደዚሁም የኤፍሬም ወገኖች በጌዝር የሚኖሩትን ከነዓናውያንን ማስወጣት አልቻሉም፤ ስለዚህ ከነዓናውያን በመካከላቸው እዚያው መኖርን ቀጠሉ። 30ዛብሎንም እንደዚሁ በቂድሮንና በነህሎል የነበሩትን በመካከላቸው የቀሩትን ከነዓናውያንን አላስወጣም፤ ነገር ግን የጕልበት ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው። 31አሴርም በዓኮ፣ በሲዶን፣ በአሕላብ፣ በአክዚብ፣ በሒልባ፣ በኣፌቅና በረአብ የሚኖሩትን አላስወጣም፤ 32በዚህ ምክንያት የአሴር ሕዝብ በምድሪቱ ካሉት ከነዓናውያን ጋር አብረው ኖሩ። 33ንፍታሌምም በቤት ሳሚስና በቤትዓናት የሚኖሩትን አላስወጣም፤ ስለዚህ የንፍታሌም ነገድ በምድሪቱ ከሚኖሩት ከነዓናውያን ጋር አብረው ኖሩ፤ ይሁን እንጂ በቤት ሳሚስና በቤትዓናት የሚኖሩት ለእነርሱ የጕልበት ሥራ ተገድደው ይሠሩ ነበር። 34የዳን ነገድ በኰረብታማው ምድር ብቻ እንዲወሰን እንጂ ወደ ሜዳማው አገር እንዲወርድ አሞራውያን አልፈቀዱለትም። 35አሞራውያንም በሔሬስ ተራራ፣ በኤሎንና በሸዓልቢም ኑሯቸውን ቀጠሉ፤ ይሁን እንጂ የዮሴፍ ወገን በበረታ ጊዜ ተገድደው የጕልበት ሥራ ከመሥራት አላመለጡም። 36የአሞራውያን ድንበር አቅራቢያም መተላለፊያ እስከ ሴላዕና ከዚያም የሚያልፍ ነበር።

New International Reader’s Version

Judges 1:1-36

The Israelites Fight Against the Remaining Canaanites

1Joshua died. After that, the Israelites spoke to the Lord. They asked him, “Who of us will go up first and fight against the Canaanites?”

2The Lord answered, “The tribe of Judah will go up. I have handed the land over to them.”

3Then the men of Judah spoke to their fellow Israelites, the men of Simeon. They said, “Come up with us. Come into the territory Joshua gave us. Help us fight against the Canaanites. Then we’ll go with you into your territory.” So the men of Simeon went with them.

4When the men of Judah attacked, the Lord helped them. He handed the Canaanites and Perizzites over to them. They struck down 10,000 men at Bezek. 5The men of Judah found Adoni-Bezek there. They fought against him. They struck down the Canaanites and Perizzites. 6But Adoni-Bezek ran away. The men of Judah chased him and caught him. Then they cut off his thumbs and big toes.

7Adoni-Bezek said, “I cut off the thumbs and big toes of 70 kings. I made them pick up scraps under my table. Now God has paid me back for what I did to them.” The men of Judah brought Adoni-Bezek to Jerusalem. That’s where he died.

8The men of Judah attacked Jerusalem and captured it. They set the city on fire. They killed its people with their swords.

9After that, the men of Judah went down to fight against some Canaanites. Those Canaanites were living in the central hill country. They also fought against those living in the Negev Desert and the western hills. 10Then the men of Judah marched out against the Canaanites living in Hebron. Hebron used to be called Kiriath Arba. The men of Judah won the battle over Sheshai, Ahiman and Talmai. 11From Hebron they marched out against the people living in Debir. It used to be called Kiriath Sepher.

12Caleb said, “I will give my daughter Aksah to be married. I’ll give her to the man who attacks and captures Kiriath Sepher.” 13Othniel captured it. So Caleb gave his daughter Aksah to him to be his wife. Othniel was the son of Kenaz. He was Caleb’s younger brother.

14One day Aksah came to Othniel. She begged him to ask her father for a field. When she got off her donkey, Caleb asked her, “What can I do for you?”

15She replied, “Do me a special favor. You have given me some land in the Negev Desert. Give me springs of water also.” So Caleb gave her the upper and lower springs.

16Moses’ father-in-law was a Kenite. His family went up from Jericho. Jericho was also known as the City of Palm Trees. His family went up with the people of Judah to the Desert of Judah. They went there to live among its people. Those people were living in the Negev Desert near Arad.

17The men of Judah marched out with their fellow Israelites, the men of Simeon. They attacked the people of Canaan living in Zephath. They set the city apart to the Lord in a special way to be destroyed. That’s why the city was called Hormah. 18The men of Judah captured Gaza, Ashkelon and Ekron. They also captured the territory around each of those cities.

19The Lord was with the men of Judah. They took over the central hill country. But they weren’t able to drive the people out of the plains. That’s because those people used chariots that had some iron parts. 20Moses had promised to give Hebron to Caleb. So Hebron was given to Caleb. He drove the three sons of Anak out of it. 21But the people of Benjamin did not drive out the Jebusites living in Jerusalem. So to this day they live there with the people of Benjamin.

22The tribes of Joseph attacked Bethel. The Lord was with them. 23They sent men to Bethel to check it out. It used to be called Luz. 24Those who were sent saw a man coming out of the city. They said to him, “Show us how to get into the city. If you do, we’ll see that you are treated well.” 25So he showed them how to get in. The men of Joseph killed the people in the city with their swords. But they spared the man from Bethel. They also spared his whole family. 26Then he went to the land of the Hittites. He built a city there. He called it Luz. That’s still its name to this day.

27But the tribe of Manasseh didn’t drive out the people of Beth Shan. They didn’t drive out the people of Taanach, Dor, Ibleam and Megiddo. And they didn’t drive out the people of the settlements that are around those cities either. That’s because the Canaanites had made up their minds to continue living in that land. 28Later, Israel became stronger. Then they forced the Canaanites to work hard for them. But Israel never drove them out completely. 29The tribe of Ephraim didn’t drive out the Canaanites living in Gezer. So the Canaanites continued to live there among them. 30The tribe of Zebulun didn’t drive out the Canaanites living in Kitron and Nahalol. So these Canaanites lived among them. But the people of Zebulun forced the Canaanites to work hard for them. 31The tribe of Asher didn’t drive out the people living in Akko and Sidon. They didn’t drive out the people of Ahlab, Akzib, Helbah, Aphek and Rehob. 32So the people of Asher lived among the Canaanites who were in the land. 33The tribe of Naphtali didn’t drive out the people living in Beth Shemesh and Beth Anath. So the people of Naphtali lived among the Canaanites who were in the land. The people of Beth Shemesh and Beth Anath were forced to work hard for them. 34The Amorites made the people of Dan stay in the central hill country. They didn’t let them come down into the plain. 35The Amorites made up their minds to stay in Mount Heres. They also stayed in Aijalon and Shaalbim. But the power of the tribes of Joseph grew. Then the Amorites were forced to work hard for them. 36The border of the Amorites started at Scorpion Pass. It went to Sela and even past it.