ኢሳይያስ 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 2:1-22

የእግዚአብሔር ተራራ

1የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ይህ ነው፤

2በዘመኑም ፍጻሜ፣

የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተራራ

ከተራሮች ከፍ ብሎ ይመሠረታል፤

ከኰረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፤

ሕዝቦችም ሁሉ ወደዚያ ይጐርፋሉ።

3ብዙ ሕዝቦችም መጥተው እንዲህ ይላሉ፤

“ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣

ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንውጣ፤

እርሱ መንገዱን ያስተምረናል፤

በጐዳናውም እንሄዳለን።”

ሕግ ከጽዮን፣

የእግዚአብሔር ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣልና።

4እርሱ በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

የብዙ ሰዎችን አለመግባባት ያስወግዳል።

እነርሱም ሰይፋቸውን ቀጥቅጠው ማረሻ፣

ጦራቸውንም ማጭድ ያደርጋሉ።

ሕዝብ በሕዝብ ላይ ሰይፍ አያነሣም፤

ጦርነትንም ከእንግዲህ አይማሩም።

5እናንተ የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ ኑ፤

በእግዚአብሔር ብርሃን እንመላለስ።

የእግዚአብሔር ቀን

6የያዕቆብ ቤት የሆነውን

ሕዝብህን ትተሃል፤

እነርሱ በምሥራቅ ሰዎች ከንቱ አምልኮ ተሞልተዋልና፤

እንደ ፍልስጥኤማውያን ያሟርታሉ፤

ከባዕዳን ጋር አገና ይማታሉ።

7ምድራቸው በብርና በወርቅ ተሞልታለች፤

ሀብታቸውም ልክ የለውም።

ምድራቸው በፈረሶች ተሞልታለች፤

የሠረገሎቻቸውም ብዛት ልክ የለውም።

8ምድራቸው በጣዖታት ተሞልታለች፤

ጣቶቻቸው ላበጇቸው፣

ለእጆቻቸው ሥራ ይሰግዳሉ።

9ሰው ዝቅ ብሏል፤

የሰው ልጅም ተዋርዷል፤

ስለዚህ በደላቸውን ይቅር አትበል2፥9 ወይም፣ ከፍ አታድርጋቸው ማለት ነው።

10ከእግዚአብሔር አስፈሪነትና ከግርማው ሽሽ፤

ወደ ዐለቶች ሂድ፤

በመሬትም ውስጥ ተሸሸግ።

11የእብሪተኛ ሰው ዐይን ይሰበራል፤

የሰዎችም ትዕቢት ይዋረዳል፤

በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻውን ከፍ ከፍ ይላል።

12የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

እብሪተኛውንና ትዕቢተኛውን ሁሉ፣

የተኵራራውን በሙሉ

የሚያዋርድበት ቀን አለው።

13ረዥምና ከፍ ከፍ ያሉትን የሊባኖስ ዝግባዎች ሁሉ፣

የባሳንን የወርካ ዛፎች ሁሉ፣

14ታላላቁን ተራራ ሁሉ፣

ከፍ ያለውን ኰረብታ ሁሉ፣

15ረዣዥሙን ግንብ ሁሉ፣

የተመሸገውን ቅጥር ሁሉ፣

16የተርሴስን መርከቦች2፥16 ወይም የንግድ መርከቦች ማለት ነው። ሁሉ፣

የክብር ጀልባዎችን ሁሉ የሚያዋርድበት ቀን አለው።

17የሰው እብሪት ይዋረዳል፤

የሰውም ኵራት ይወድቃል፤

በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻ ከፍ ከፍ ይላል፤

18ጣዖቶች ሁሉ ፈጽሞ ይወድማሉ።

19እግዚአብሔር ምድርን ለማናወጥ በሚነሣበት ጊዜ፣

ሰዎች ከአስፈሪነቱ

ከግርማውም የተነሣ፣

ወደ ዐለት ዋሻ፣

ወደ መሬትም ጕድጓድ ለመሸሸግ ይሮጣሉ።

20በዚያን ቀን ሰዎች

ሊያመልኳቸው ያበጇቸውን፣

የብርና የወርቅ ጣዖቶቻቸውን

ለፍልፈልና ለሌሊት ወፍ ይወረውራሉ።

21እግዚአብሔር ምድርን ለማናወጥ በሚነሣበት ጊዜ፣

ሰዎች ከአስፈሪነቱ

እንዲሁም ከግርማው የተነሣ፣

ወደ ድንጋይ ዋሻ፣

ወደ ዐለት ስንጣቂ ሮጠው ይገባሉ።

22እስትንፋስ አፍንጫው ላይ ባለች

በሰው አትታመኑ፤

ከቶ ምን የሚበጅ ነገር አለው!

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 2:1-22

主必统治万邦

1亚摩斯的儿子以赛亚看到以下有关犹大耶路撒冷的异象。

2在末后的日子,耶和华殿所在的山必耸立,

高过群山,超过万岭,

万族都要涌向它。

3众民都必来,说:

“来吧!让我们登耶和华的山,

雅各之上帝的殿。

祂必将祂的路指示给我们,

使我们走祂的道。”

因为训诲必出于锡安

耶和华的话语必来自耶路撒冷

4祂必在各国施行审判,

为列邦平息纷争。

他们必将刀剑打成犁头,

把矛枪制成镰刀。

国与国不再刀兵相见,

人们不用再学习战事。

5雅各家啊,来吧!

让我们走在耶和华的光中。

耶和华审判的日子

6耶和华啊,你离弃了你的子民——雅各的后裔,

因为他们当中充满了东方的恶俗,

非利士人一样占卜,

跟外族人同流合污。

7他们境内金银遍地,

财宝无穷;

他们境内马匹充裕,

战车无数。

8他们境内偶像林立,

他们跪拜自己用手所造的物品,

跪拜自己用指头所造之物。

9他们必遭羞辱和贬抑。

耶和华啊,

求你不要赦免他们。

10要躲进岩穴,藏入地洞,

逃避耶和华的愤怒和威荣!

11到那日,狂妄的人将被挫败,

骄傲的人将遭贬抑;

唯独耶和华将受尊崇。

12因为万军之耶和华已定了日子,

要惩罚一切骄傲狂妄和自高自大的人,

使他们沦为卑贱;

13祂必毁灭黎巴嫩高大的香柏树和巴珊的橡树,

14毁灭一切崇山峻岭,

15毁灭高耸的城楼和坚固的城墙,

16毁灭他施的商船和一切华美的船只。

17到那日,狂妄的人必被挫败,

骄傲的人必遭贬抑,

唯独耶和华受尊崇。

18偶像必被彻底铲除。

19耶和华使大地震动的时候,

众人躲进岩穴,藏入地洞,

逃避祂的愤怒和威荣。

20到那日,众人必把造来敬拜的金银偶像丢给田鼠和蝙蝠。

21耶和华使大地震动的时候,

众人必躲进山洞和岩缝,

逃避祂的愤怒和威荣。

22不要再倚靠世人,

他们的生命不过是一口气,

他们有什么值得称道的呢?