ኢሳይያስ 3 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 3:1-26

በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ላይ የሚመጣ ፍርድ

1እነሆ፤ ጌታ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ

ድጋፉንና ርዳታውን፣

የምግብና የውሃ ርዳታውን ሁሉ ይነሣል፤

2ጀግናውንና ተዋጊውን፣

ፈራጁንና ነቢዩን፣

አስማተኛውንና ሽማግሌውን፣

3የአምሳ አለቃውንና ባለ ማዕረጉን፣

አማካሪውንና ጠቢቡን የእጅ ባለሙያ፣

ብልኁንም ምትሀተኛ ይነሣል።

4ልጆችን መሪዎቻቸው አደርጋለሁ፤

ያልበሰሉ ሕፃናትም ይገዟቸዋል።

5ሕዝብ እርስ በርሱ ይጨቋቈናል፤

ሰው በሰው ላይ፤ ባልንጀራ በባልንጀራው ላይ፣

ወጣቱ በሽማግሌው ላይ፣

ተራው ሰው በተከበረው ላይ ይነሣል።

6ሰውም በአባቱ ቤት

ከወንድሞቹ አንዱን ይዞ፣

“አንተ ልብስ ስላለህ መሪ ሁነን፤

ይህንም የፍርስራሽ ክምር ግዛ!” ይለዋል።

7እርሱ ግን በዚያ ቀን ድምፁን ከፍ አድርጎ፣

“እኔ መፍትሔ አልሆንም፤

በቤቴም ልብስና ምግብ የለኝም፤

የሕዝብ መሪ አታድርጉኝ” ይላል።

8ኢየሩሳሌም ተንገዳግዳለች፤

ይሁዳም ለመውደቅ ተቃርባለች፤

ንግግራቸውም ሆነ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚቃወም፣

የክብሩንም መገኘት የሚያቃልል ነውና።

9የፊታቸው ገጽታ ይመሰክርባቸዋል፤

ኀጢአታቸውን እንደ ሰዶም በይፋ ይናገራሉ፤

አይደብቁትምም፤

ጥፋትን በራሳቸው ላይ ስላመጡ፣

ወዮላቸው!

10ጻድቃን መልካም ነገር እንደሚያገኙ ንገሯቸው፤

የሥራቸውን ፍሬ ይበላሉና።

11በደለኞች ወዮላቸው፤ ጥፋት ይመጣባቸዋል፤

የእጃቸውን ያገኛሉና።

12ወጣቶች ሕዝቤን ያስጨንቃሉ፤

ሴቶችም ይገዟቸዋል።

ሕዝቤ ሆይ፤ መሪዎችህ አሳስተውሃል፤

ከመንገድህም መልሰውሃል።

13እግዚአብሔር በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጧል፤

በሕዝቡም ላይ ለመፍረድ ተነሥቷል።

14እግዚአብሔር

ከአለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሌዎች ጋር እንዲህ ሲል ይፋረዳል፤

“የወይኔን ቦታ ያጠፋችሁ እናንተ ናችሁ፤

ከድኾች የዘረፋችሁትም በቤታችሁ ይገኛል፤

15ሕዝቤን በችግር ስታደቅቁት፣

የድኾችንም ፊት በሐዘን ስታገረጡት ምን ማለታችሁ ነው?”

ይላል ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

16እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

የጽዮን ሴቶች ኰርተዋል፤

ዐንገታቸውን እያሰገጉ፣

በዐይናቸውም እየጠቀሱ ይሄዳሉ፤

እየተቈነኑ በመራመድ፣

የእግራቸውን ዐልቦ ያቃጭላሉ።

17ስለዚህ፣ ጌታ በጽዮን ሴቶች ዐናት ላይ

ቈረቈር ያመጣል፤

እግዚአብሔርም ራሳቸውን ቡሀ ያደርጋል።

18በዚያም ቀን ጌታ የክብር ጌጣቸውን ይነጥቃቸዋል፤ የእግር አንባሩን፣ የጠጕር ጌጡን፣ የጨረቃ ቅርጽ ያለውን የዐንገት ጌጥ፣ 19የጆሮ ጕትቻውን፣ የእጅ አንባሩን፣ የፊት መሸፈኛውን፣ 20የራስ መሸፈኛውን፣ ዐልቦውን፣ ሻሹን፣ የሽቶ ብልቃጡን፣ አሸንክታቡን፣ 21የጣት ቀለበቶችንና የአፍንጫ ቀለበቶችን፣ 22ያማረውን ቀሚስ፣ የውስጥ ልብሱን፣ ካባውን፣ የእጅ ቦርሳውን፣ 23መስተዋቱን፣ ከጥሩ በፍታ የተሠራውን ልብስ፣ የራስ ጌጡን፣ ዐይነ ርግቡን ሁሉ ይነጥቃቸዋል።

24በሽቶ ፈንታ ግማት፣

በሻሽ ፈንታ ገመድ፣

አምሮ በተሠራ ጠጕር ፈንታ ቡሀነት፣

ባማረ ልብስ ፈንታ ማቅ፣

በውበትም ፈንታ ጠባሳ ይሆናል።

25ወንዶቻችሁ በሰይፍ ስለት፣

ተዋጊዎቻችሁ በጦርነት ይወድቃሉ።

26የጽዮን ደጆች ያዝናሉ፣ ያለቅሳሉም፤

እርሷም ተረስታ በመሬት ላይ ትቀመጣለች።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 3:1-26

对耶路撒冷和犹大的审判

1主——万军之耶和华要从耶路撒冷犹大拿去众人倚靠的一切:粮食、水、

2英雄、战士、审判官、先知、

占卜者、长老、

3五十夫长、显贵、谋士、巧匠和巫师。

4主必使少儿做他们的首领,

让孩童治理他们。

5百姓将彼此欺凌,

邻居互相争斗,

少年目无尊长,

卑贱者欺尊犯上。

6那时,人会拉住一位同族的弟兄说:

“你至少还有件像样的衣服,

你就做我们的首领吧,

这废墟之地就交给你了!”

7但那人必高声说:

“我救不了你们。

我家中无衣无食,

不要让我做首领。”

8耶路撒冷必崩溃,

犹大必败落,

因为他们的言行冒犯耶和华,

蔑视荣耀的主。

9他们的表情显出他们心术不正,

他们跟所多玛人一样对自己的罪恶津津乐道,

毫不隐瞒。

他们必大祸临头,自招毁灭。

10要告诉义人:他们有福了,

必得善报。

11恶人有祸了!他们必大祸临头,

受到报应。

12耶和华说:“我的子民啊!

孩童欺压你们,

妇女管辖你们。

你们的首领领你们入迷途,

带你们走歧路。”

13耶和华准备就绪,

要审判祂的子民。

14祂必审问祂子民中的长老和首领,对他们说:

“你们毁坏了我的葡萄园——我的子民,

家里堆满了从穷人那里掠夺的东西。

15你们为何压榨我的子民,

虐待贫穷人?”

这是主——万军之耶和华说的。

16耶和华又说:

锡安的女子狂傲,

昂首走路,卖弄媚眼,

俏步徐行,脚镯叮当。

17所以,我要使她们头上长疮,

露出头皮。”

18到那日,主必拿去她们美丽的脚镯、发饰、项链、 19耳环、手镯、面纱、 20头饰、脚链、彩带、香盒、护身符、 21戒指、鼻环、 22礼服、外袍、披肩、钱包、 23镜子、内衣、头巾和围巾。

24她们的香气将变成臭味,

腰带将变成绳子,

美发将变成秃头,

华服将变成麻衣,

美丽的容颜将布满羞辱的烙印。

25城中的男子将丧身刀下,

勇士将战死沙场。

26锡安的城门必悲伤、哀哭,

锡安必空空地坐在地上。