ምሳሌ 16 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 16:1-33

1የልብ ዕቅድ የሰው ነው፤

የአንደበት መልስ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ንጹሕ መስሎ ይታየዋል፤

መነሻ ሐሳቡ ግን በእግዚአብሔር ይመዘናል።

3የምታደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤

ዕቅድህም ሁሉ ይሳካልሃል።

4እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ለራሱ ዐላማ ሠርቷል፤

ክፉዎችንም እንኳ ለጥፋት ቀን አዘጋጅቷል።

5እግዚአብሔር በልብ የሚታበዩትን ሁሉ ይጸየፋል፤

እነርሱም ከቅጣት እንደማያመልጡ በርግጥ ዕወቅ።

6በፍቅርና በታማኝነት ኀጢአት ይሰረያል፤

እግዚአብሔርን በመፍራት ሰው ከክፋት ይርቃል።

7የሰው መንገድ እግዚአብሔርን ደስ ሲያሰኘው፣

ጠላቶቹ እንኳ አብረውት በሰላም እንዲኖሩ ያደርጋል።

8ከጽድቅ ጋር ጥቂቱ ነገር፣

በግፍ ከሚገኝ ብዙ ትርፍ ይሻላል።

9ሰው በልቡ መንገዱን ያቅዳል፤

እግዚአብሔር ግን ርምጃውን ይወስንለታል።

10የንጉሥ ከንፈሮች እንደ አምላክ ቃል ይናገራሉ፤

አንደበቱ ፍትሕን ያዛባ ዘንድ አይገባም።

11ሐቀኛ መስፈሪያና ሚዛን ከእግዚአብሔር ናቸው፤

በከረጢት ውስጥ ያሉት መመዘኛዎችም ሁሉ ሥራዎቹ ናቸው።

12ክፋትን ማድረግ ለነገሥታት አስጸያፊ ነው፤

ዙፋን የሚጸናው በጽድቅ ነውና።

13ነገሥታት በታማኝ ከንፈሮች ደስ ይላቸዋል፤

እውነት የሚናገረውን ሰው ይወድዱታል።

14የንጉሥ ቍጣ የሞት መልእክተኛ ነው፤

ጠቢብ ሰው ግን ቍጣውን ያበርዳል።

15የንጉሥ ፊት ሲፈካ ሕይወት አለ፤

በጎነቱም ዝናብ እንዳዘለ የበልግ ደመና ነው።

16ከወርቅ ይልቅ ጥበብን ማግኘት፣

ከብርም ማስተዋልን መምረጥ ምንኛ ይበልጣል!

17የቅኖች ጐዳና ከክፋት የራቀ ነው፤

መንገዱንም የሚጠብቅ ሕይወቱን ይጠብቃል።

18ትዕቢት ጥፋትን፣

የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።

19በተዋረደ መንፈስ ከተጨቈኑት ጋር መሆን፣

ከትዕቢተኞች ጋር ብዝበዛን ከመካፈል ይሻላል።

20ምክርን የሚሰማ ይለመልማል፤

በእግዚአብሔርም የሚታመን ቡሩክ ነው።

21ልባቸው ጠቢብ የሆነ አስተዋዮች ይባላሉ፤

ደስ የሚያሰኙ ቃላትም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥21 ወይም ቃላትም ተደማጭነት ያስገኛሉ

22ማስተዋልን ገንዘብ ላደረጋት የሕይወት ምንጭ ናት፤

ቂልነት ግን በተላሎች ላይ ቅጣት ታመጣባቸዋለች።

23የጠቢብ ሰው ልብ አንደበቱን ይመራል፤

ከንፈሮቹም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥23 ወይም አንደበቱን አሳማኝ ያደርጋሉ

24ደስ የሚያሰኝ ቃል የማር ወለላ ነው፤

ለነፍስ ጣፋጭ፣ ለዐጥንትም ፈውስ ነው።

25ለሰው ቀና መስሎ የሚታይ መንገድ አለ፤

በመጨረሻ ግን ወደ ሞት ይመራል።

26ሠራተኛን የዕለት ጕርስ ፍላጎቱ ታታሪ ያደርገዋል፤

ራቡም ይገፋፋዋል።

27ወራዳ ሰው ክፋትን ያውጠነጥናል፤

ንግግሩም እንደሚለበልብ እሳት ነው።

28ጠማማ ሰው ጠብን ይዘራል፤

ሐሜተኛም የቅርብ ወዳጆችን ይለያያል።

29ክፉ ሰው ባልንጀራውን ያባብለዋል፤

መልካም ወዳልሆነውም መንገድ ይመራዋል።

30በዐይኑ የሚጠቅስ ሰው ጠማማነትን ያውጠነጥናል፤

በከንፈሩ የሚያሽሟጥጥም ወደ ክፋት ያዘነብላል።

31ሽበት የክብር ዘውድ ነው፤

የሚገኘውም በጽድቅ ሕይወት ነው።

32ታጋሽ ሰው ከጦረኛ፣

ስሜቱን የሚገዛም ከተማን በጕልበቱ ከሚይዝ ይበልጣል።

33ዕጣ በጕያ ውስጥ ይጣላል፤

ውሳኔው በሙሉ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 16:1-33

16

1人は計画を立てますが、

その結果は主の手の中にあります。

2人はいつも自分が正しいと思います。

しかし、主もそう思っているでしょうか。

3自分でしようとしていることを主にゆだねなさい。

そうすればうまくいきます。

4主はすべてのものを目的をもって造りました。

悪者でさえ、罰するために造られたのです。

5主は高慢な人をきらいます。

そういう人は必ず罰せられます。

6思いやりと真心があれば罪は除かれ、

主を恐れる気持ちがあれば悪に手を染めません。

7主を喜ばせようとすれば、

その人の最大の敵も、主が味方に変えてくれます。

8人をだまして大もうけするより、

わずかずつでも正直にかせぐほうがましです。

9人は心に計画を立てます。

しかし、それを確かなものにするのは神です。

10神は、王が正しく裁けるように助けるので、

王は間違ったことを言ってはいけません。

11正直に商売すること、

それが主の決めた鉄則です。

12王が悪を行うのは恐ろしいことです。

正しく治めてこそ、その地位は長続きするのです。

13国民が正しく生きることは

王の喜びです。

14王を怒らせるのは死刑を宣告されたようなもので、

知恵のある人は王の怒りをうまくなだめます。

15王を喜ばせる者は目をかけられます。

16知恵は金にまさり、

すぐれた理解力は銀にまさります。

17神を恐れる人は悪を行いません。

その道を歩む者は安全です。

18プライドが高すぎると身を滅ぼし、

高慢は失敗を招きます。

19金持ちで高慢な人より、

貧しくても謙遜な人のほうが幸せです。

20神のみことばを聞く人は祝福されます。

主に信頼する人は幸せです。

21知恵のある人は聡明な人と呼ばれ、

人に好かれる最高の教師です。

22知恵のある人は生きる喜びにあふれ、

愚か者は愚かさのために苦しみます。

23知恵のある人のことばは的確で

説得力があります。

24親切なことばははちみつのように甘く、

人々を元気づけます。

25広くて歩きやすい道は正しい道に見えます。

しかし、その終点は死です。

26食べるために働く気を起こさせるなら、

ひもじさも役に立ちます。

27怠け者の手は悪魔の手、

その口は悪魔の口です。

28悪人は争いを起こし、

陰口を言う者は親友が離れていきます。

29悪者は仲間を作るのが大好きで、

人を罪に誘い込みます。

30悪者は心の中で悪いことを企み、

口をすぼめてうかがっています。

31白髪は光栄の冠、

神に従う人の中に多く見いだされます。

32英雄よりも温和な者のほうがすぐれ、

軍隊を動かす指揮官よりも

自分を制する者のほうに力があります。

33人はくじを引きますが、

その結果を決めるのは主です。