ምሳሌ 15 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 15:1-33

1የለዘበ መልስ ቍጣን ያበርዳል፤

ክፉ ቃል ግን ቍጣን ይጭራል።

2የጠቢብ አንደበት ዕውቀትን ታወድሳለች፤

የተላሎች አንደበት ግን ቂልነትን ያፈልቃል።

3የእግዚአብሔር ዐይኖች በሁሉም ስፍራ ናቸው፤

ክፉዎችንም ደጎችንም ነቅተው ይመለከታሉ።

4ፈውስ የምታመጣ ምላስ የሕይወት ዛፍ ናት፤

አታላይ ምላስ ግን መንፈስን ትሰብራለች።

5ተላላ የአባቱን ምክር ይንቃል፤

መታረምን የሚቀበል ግን አስተዋይነቱን ያሳያል።

6የጻድቃን ቤት በብዙ ሀብት የተሞላ ነው፤

የክፉዎች ገቢ ግን መከራን ታመጣባቸዋለች።

7የጠቢባን ከንፈር ዕውቀትን ታስፋፋለች፤

የተላሎች ልብ ግን እንዲህ አይደለም።

8እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤

የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።

9እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤

ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወድዳቸዋል።

10ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤

ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።

11ሲኦልና የሙታን ዓለም15፥11 በዕብራይስጡ ሲኦልና አባዶን ይላል። በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤

የሰዎች ልብማ የቱን ያህል የታወቀ ነው!

12ፌዘኛ መታረምን ይጠላል፤

ጠቢባንንም አያማክርም።

13ደስተኛ ልብ ፊትን ያፈካል፤

የልብ ሐዘን ግን መንፈስን ይሰብራል።

14አስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይሻል፤

የተላላ አፍ ግን ቂልነትን ያመነዥካል።

15የተጨቈኑ ሰዎች ዘመናቸው ሁሉ የከፋ ነው፤

በደስታ የተሞላ ልብ ግን የማይቋረጥ ፈንጠዝያ አለው።

16እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር፣

ሁከት ካለበት ትልቅ ሀብት ይበልጣል።

17ፍቅር ባለበት ጐመን መብላት፣

ጥላቻ ባለበት የሰባ ፍሪዳ ከመብላት ይሻላል።

18ግልፍተኛ ሰው ጠብ ያነሣሣል፤

ታጋሽ ሰው ግን ጠብን ያበርዳል።

19የሀኬተኛ መንገድ በእሾኽ የታጠረች ናት፤

የቅኖች መንገድ ግን የተጠረገ አውራ ጐዳና ነው።

20ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤

ተላላ ሰው ግን እናቱን ይንቃል።

21ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤

አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

22ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤

በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።

23ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤

በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!

24ወደ ሲኦል15፥24 ወይም መቃብር ከመውረድ እንዲድን፣

የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

25እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤

የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።

26እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤

የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።

27ስስታም ሰው በቤተ ሰቡ ላይ ችግር ያመጣል፤

ጕቦን የሚጠላ ግን በሕይወት ይኖራል።

28የጻድቅ ሰው ልብ የሚሰጠውን መልስ ያመዛዝናል፤

የክፉ ሰው አፍ ግን ክፋትን ያጐርፋል።

29እግዚአብሔር ከክፉዎች ሩቅ ነው፤

የጻድቃንን ጸሎት ግን ይሰማል።

30ብሩህ ገጽታ ልብን ደስ ያሰኛል፤

መልካም ዜናም ዐጥንትን ያለመልማል።

31ሕይወት ሰጭ የሆነውን ተግሣጽ የሚሰማ፣

በጠቢባን መካከል ይኖራል።

32ተግሣጽን የሚንቅ ራሱን ይንቃል፤

ዕርምትን የሚቀበል ግን ማስተዋልን ያገኛል።

33እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብን መማር ነው፤15፥33 ወይም ጥበብ እግዚአብሔርን መፍራት ታስተምራለች።

ትሕትናም ክብርን ትቀድማለች።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 15:1-33

15

1穏やかに答えれば相手の心を静め、

激しいことばでやり返すとけんかになります。

2良い教師がいれば学習が楽しくなり、

無力な教師は益にならないことをまくし立てます。

3主はあらゆる所で、

悪人も正しい人も一人残らず見張っています。

4優しいことばは人を元気づけ、

不平は人の気をくじきます。

5愚かな子ほど父親の忠告を見くびり、

利口な子ほど、ひと言ひと言を熱心に聞きます。

6正しい人は裕福になり、悪者は収穫を得ても、

めんどうなことに巻き込まれます。

7人を教えられるのは知恵のある人だけで、

神に背く者にはとてもできません。

8主は悪者の供え物を憎み、正しい人の祈りを喜びます。

9-10主は悪者の行いをきらい、

正しく生きようとする人を愛します。

しかし途中で心変わりしたら、

きびしい罰が待っています。

その罰を受け入れなければ死ぬだけです。

11地獄の深遠まで知っている主には、

人の心など手に取るようにわかります。

12人をさげすむ者は、しかられるのをきらって、

知恵のある人を避けようとします。

13楽しければ顔が輝き、

悲しければ顔が曇ります。

14知恵のある人は熱心に真理を求め、

人をさげすむ者はつまらないことに熱中します。

15気が重いと何もかも悪く見え、

気分がいいと、いつも喜んでいられます。

16財産があるばかりにあれこれ気を遣うより、

貧しくとも主を信じて生きるほうが幸せです。

17憎む者といっしょにごちそうを食べるより、

愛する人と質素な食事をするほうが幸せです。

18気の短い者はすぐにけんかを始め、

冷静な人はその場をうまく収めます。

19怠け者は年中問題をかかえ込み、

誠実な人は平和な一生を送ります。

20分別がある息子は父親を喜ばせ、

反抗的な息子は母親を悲しませます。

21愚かなことをして喜ぶのは、

何かが間違っている証拠です。

分別の備わった人は正しい道を踏みはずしません。

22良い助言をくれる人が少ないと計画は失敗し、

多いと成功します。

23良い助言は喜びをもたらし、

時宜にかなったことばは、

いかにすばらしいものか。

24神を恐れる人の道は天国へ上る道。

地獄からはどんどん遠ざかります。

25主は高慢な者を破産させ、

未亡人を心に留めます。

26主は悪者の計画を憎み、

親切なことばを喜びます。

27不正を働いて得た金は家族みんなを不幸にし、

わいろを憎むことは幸福をもたらします。

28正しい人はよく考えてから話し、

悪者は見境なく悪いことばを吐き出します。

29主は悪者とは距離を置き、

正しい人の祈りを聞きます。

30生き生きした目の輝きと良い知らせは、

人を喜ばせ、力づけます。

31-32有益な批判を取り入れるのは賢い人です。

批判を拒絶すれば自分をだめにします。

33主を恐れ、謙遜に生きる人は知恵を身につけ、

人の称賛を得ます。