ምሳሌ 17 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 17:1-28

1ጠብ እያለ ግብዣ17፥1 ዕብራይስጡ መሥዋዕት ይላል። ከሞላበት ቤት ይልቅ፣

በሰላምና በጸጥታ የእንጀራ ድርቆሽ ይሻላል።

2ጠቢብ አገልጋይ በወራዳ ልጅ ላይ ሥልጣን ይኖረዋል፤

ከወንድማማቾቹም እንደ አንዱ ውርስ ይካፈላል።

3ማቅለጫ ለብር፣ ከውር ለወርቅ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ልብን ይመረምራል።

4እኩይ ሰው ክፉ ንግግር ያዳምጣል፤

ሐሰተኛም የተንኰለኛን አንደበት በጥንቃቄ ይሰማል።

5በድኾች የሚያፌዝ ፈጣሪያቸውን ይንቃል፤

በሌላው ሰው መከራ ደስ የሚለው ከቅጣት አያመልጥም።

6የልጅ ልጆች ለአረጋውያን ዘውድ ናቸው፤

ወላጆችም ለልጆቻቸው አለኝታ ናቸው።

7መልካም አነጋገር17፥7 ወይም የኵራት አነጋገር ለተላላ አይሰምርለትም፤

ለገዥማ ሐሰተኛ አንደበት የቱን ያህል የከፋ ይሆን!

8እጅ መንሻ ለሰጭው እንደ ድግምት ዕቃ ነው፤

በሄደበትም ቦታ ሁሉ ይሳካለታል።

9በደልን የሚሸፍን ፍቅርን ያዳብራል፤

ነገርን የሚደጋግም ግን የልብ ወዳጆችን ይለያያል።

10መቶ ግርፋት ተላላን ከሚሰማው ይልቅ፣

ተግሣጽ ለአስተዋይ ጠልቆ ይሰማል።

11ክፉ ሰው ዐመፅን ብቻ ይፈልጋል፤

በእርሱም ላይ ጨካኝ መልእክተኛ ይላክበታል።

12ተላላን በቂልነቱ ከመገናኘት፣

ግልገሎቿን የተነጠቀችን ድብ መጋፈጥ ይሻላል።

13በበጎ ፈንታ ክፉ የሚመልስ ሰው፣

ክፉ ነገር ከቤቱ አይርቅም።

14ጠብ መጫር ግድብን እንደ መሸንቈር ነው፤

ስለዚህ ጠብ ከመጫሩ በፊት ከነገር ራቅ።

15በደለኛውን ንጹሕ ማድረግ ሆነ፣ ንጹሑን በደለኛ ማድረግ፣

ሁለቱም በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ናቸው።

16ጥበብን ለማግኘት ፍላጎት ስለሌለው፣

ተላላ እጅ የገባ ገንዘብ ጥቅሙ ምንድን ነው?

17ወዳጅ ምንጊዜም ወዳጅ ነው፤

ወንድምም ለክፉ ቀን ይወለዳል።

18ማስተዋል የጐደለው ሰው ቃል በመግባት እጅ ይመታል፤

ለወዳጁም ዋስ ይሆናል።

19ጠብ የሚወድድ ኀጢአትን ይወድዳል፤

በሩን ከፍ አድርጎ የሚሠራም ጥፋትን ይጋብዛል።

20ጠማማ ልብ ያለው ሰው አይሳካለትም፤

በአንደበቱ የሚቀላምድም መከራ ላይ ይወድቃል።

21ተላላ ልጅ መውለድ ሐዘን ያስከትላል፤

የተላላም አባት ደስታ የለውም።

22ደስተኛ ልብ ጥሩ መድኀኒት ነው፤

የተሰበረ መንፈስ ግን ዐጥንትን ያደርቃል።

23ክፉ ሰው ፍትሕ ለማዛባት፣

በስውር ጕቦ ይቀበላል።

24አስተዋይ ሰው ጥበብን ከፊቱ አይለያትም፤

የተላሎች ዐይኖች ግን እስከ ምድር ዳርቻ ይንከራተታሉ።

25ተላላ ልጅ በአባቱ ላይ ሐዘን ያስከትላል፤

ለወለደችውም ምሬት ይሆንባታል።

26ንጹሑን ሰው መቅጣት ተገቢ አይደለም፤

ሹሞችን ስለ ቅንነታቸው መግረፍ መልካም አይደለም።

27ዐዋቂ ሰው ንግግሩ ቍጥብ ነው፤

አስተዋይም መንፈሱ የረጋ ነው።

28አላዋቂ እንኳ ዝም ቢል ጠቢብ፣

አንደበቱንም ቢገዛ አስተዋይ ይመስላል።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 17:1-28

17

1ごちそうがありながら毎日争いごとがある家より、

たった一切れのパンを

仲良く食べる家のほうが幸せです。

2賢い使用人は、主人の恥知らずの息子を監督し、

財産の分け前をもらいます。

3銀や金は火で精錬しますが、

人の心をきよめるのは主です。

4悪人は悪人同士でつき合い、

うそつきはうそつき同士でつき合います。

5貧しい人をさげすむのは、

その人を造った神をさげすむのと同じです。

神は人の不幸を喜ぶ者を罰します。

6孫は老人の無上の栄誉、

子どもの栄誉は彼らの父です。

7神に背く者が真実を言ったり、

王がうそをついたりすることはめったにありません。

8わいろには魔力があり、

だれが使っても効果があります。

9愛のある人は人の誤りを水に流し、

いつまでもこだわる者は親友までも失います。

10理解力ある人は一度しかれば十分です。

それは、聞き分けのない者の背を

百ぺんむち打つよりも効き目があります。

11悪者は何でも逆らって生きるので、

きびしい罰を受けます。

12愚かなことにふける愚か者に会うより、

子を奪われた雌熊に会うほうがよほど安全です。

13よくしてもらいながら、

その好意を裏切る者はのろわれます。

14いったん火のついた争いごとは、

なかなか収まりません。

だから、初めから争いはしないことです。

15間違いを正しいと言い、

正しいことを間違いだと言う者は、主に憎まれます。

16真理を学ぶ気がなければ、

いくら授業料を払っても意味がありません。

17真の友は決して裏切りません。

兄弟は苦しみに会ったときに

助け合うためにいるのです。

18思慮の足りない者は気安く保証人になり、

その人の借金の責任を負います。

19罪人は争いが大好きで、

高ぶる者は問題を探し求めます。

20悪人はだれにでも疑いの目を向け、

いつも災いに陥ります。

21反抗する者の父親には、

生きる楽しみがありません。

22心が陽気になれば体も健康になり、

気がふさげば病気になります。

23買収されて正義を曲げるのはよくありません。

24分別のある人は知恵から目を離さず、

愚か者は遠くをぼんやり眺めています。

25反抗的な子は親泣かせです。

26正しい人を正しさゆえに罰金を科し、

高潔な人を正直さゆえに罰するのは、

なんと愚かなことでしょう。

27-28賢い人は無口で、すぐに怒ったりしません。

だから、愚かな人も黙っていれば賢く見え、

くちびるを閉じていれば得をします。