ማርቆስ 2 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 2:1-28

ኢየሱስ ሽባ ፈወሰ

2፥3-12 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥2-8ሉቃ 5፥18-26

1ኢየሱስ ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቅፍርናሆም እንደ ተመለሰ፣ ወደ ቤት መግባቱን ሕዝቡ ሰማ። 2ስለዚህ ከበሩ ውጭ እንኳ ሳይቀር ስፍራ እስኪታጣ ድረስ ብዙ ሕዝብ ተሰበሰበ፤ እርሱም የእግዚአብሔርን ቃል ሰበከላቸው። 3ጥቂት ሰዎችም አንድ ሽባ በአራት ሰዎች አሸክመው ወደ እርሱ አመጡ። 4ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ ኢየሱስ ወዳለበት መቅረብ ስላልቻሉ፣ የቤቱን ጣራ እርሱ ባለበት በኩል ነድለው ቀዳዳ በማበጀት ሽባው የተኛበትን ዐልጋ በዚያ አወረዱ። 5ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፣ “አንተ ልጅ፣ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል!” አለው።

6በዚያ ተቀምጠው የነበሩ አንዳንድ ጸሐፍት ስለዚህ ነገር በልባቸው እያሰላሰሉ፣ 7“ይህ ሰው እንዴት እንዲህ ይላል? በአምላክ ላይ የስድብ ቃል እየተናገረ እኮ ነው! ከአንዱ ከእግዚአብሔር በስተቀር ማን ኀጢአትን ሊያሰተሰርይ ይችላል?” ብለው አሰቡ።

8ኢየሱስም ወዲያው በልባቸው የሚያስቡትን በመንፈሱ ተረድቶ፣ “እንዴት እንዲህ ታስባላችሁ? 9ሽባውን፣ ‘ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል’ ከማለትና፣ ‘ተነሥተህ ዐልጋህን ተሸክመህ ሂድ’ ከማለት የቱ ይቀልላል? 10ነገር ግን የሰው ልጅ በምድር ላይ ኀጢአትን ለማስተስረይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ” በማለት ሽባውን፣ 11“ተነሥተህ ዐልጋህን ተሸክመህ ወደ ቤትህ ሂድ” አለው። 12እርሱም ተነሥቶ ሁሉም እያዩት ዐልጋውን ተሸክሞ ሄደ፤ በስፍራው የነበሩትም ሁሉ በሁኔታው በመደነቅ፣ “የዚህ ዐይነት ነገር ፈጽሞ አይተን አናውቅም!” በማለት ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀረቡ።

የሌዊ መጠራት

2፥14-17 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥9-13ሉቃ 5፥27-32

13ኢየሱስም ዳግም ወደ ባሕሩ ዳርቻ ወጣ፤ ሕዝቡም በብዛት ወደ እርሱ መጡ፤ እርሱም አስተማራቸው። 14በዚያም ሲያልፍ የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን በቀረጥ መቀበያው ስፍራ ተቀምጦ አየውና፣ “ተከተለኝ” አለው፤ እርሱም ተነሥቶ ተከተለው።

15በማቴዎስ ቤት በማእድ ተቀምጦ ሳለ፣ ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና ኀጢአተኞች ተከትለውት ስለ ነበር፣ ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ይመገቡ ነበር። 16ከፈሪሳውያን ወገን የነበሩ ጸሐፍት ከኀጢአተኞችና ከቀረጥ ሰብሳቢዎች ጋር ሲበላ ባዩት ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱን “ከቀረጥ ሰብሳቢዎችና ከኀጢአተኞች ጋር ለምን ይበላል?” ሲሉ ጠየቋቸው።

17ኢየሱስም የሚናገሩትን ሰምቶ፣ “ሐኪም የሚያስፈልጋቸው ሕመምተኞች እንጂ ጤነኞች አይደሉም፤ እኔ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ወደ ንስሓ ልጠራ አልመጣሁም” አላቸው።

ስለ ጾም የቀረበ ጥያቄ

2፥18-22 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥14-17ሉቃ 5፥33-38

18የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጾሙ ነበር፤ አንዳንድ ሰዎችም መጥተው ኢየሱስን፣ “የዮሐንስና የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት ሲጾሙ፣ የአንተ ደቀ መዛሙርት የማይጾሙት ለምንድን ነው?” አሉት።

19ኢየሱስም፣ እንዲህ አላቸው፤ “ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ሚዜዎቹ ሊጾሙ ይችላሉን? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ሊጾሙ አይችሉም፤ 20ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወቅት ይመጣል፤ በዚያን ጊዜ ግን ይጾማሉ።

21“በአሮጌ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ የሚጥፍ ማንም የለም፤ ይህ ቢደረግ ግን፣ አዲሱ ጨርቅ አሮጌውን ይቦጭቀዋል፤ ቀዳዳውም የባሰ ይሰፋል። 22እንዲሁም አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቍማዳ የሚያስቀምጥ የለም፤ ይህ ከተደረገማ የወይን ጠጁ አቍማዳውን ያፈነዳዋል፤ የወይን ጠጁም አቍማዳውም ይበላሻሉ። ስለዚህ አዲስ የወይን ጠጅ መቀመጥ ያለበት በአዲስ አቍማዳ ነው።”

ኢየሱስ የሰንበት ጌታ ነው

2፥23-28 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥1-8ሉቃ 6፥1-5

3፥1-6 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥9-14ሉቃ 6፥6-11

23በሰንበት ቀን ኢየሱስ በዕርሻ መካከል ሲያልፍ፣ አብረውት በመጓዝ ላይ የነበሩት ደቀ መዛሙርቱ እሸት ይቀጥፉ ጀመር። 24ፈሪሳውያንም፣ “እነሆ፤ በሰንበት ቀን ለምን የተከለከለ ነገር ያደርጋሉ?” ሲሉ ጠየቁት።

25እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ዳዊት በተራበና የምግብ ፍላጎት በጸናበት ጊዜ አብረውት ከነበሩት ሰዎች ጋር ያደረገውን አላነበባችሁምን? 26በሊቀ ካህናቱ በአብያታር ዘመን ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ፣ ካህናት ብቻ እንዲበሉት የተፈቀደውን የተቀደሰ ኅብስት ራሱ በልቶ አብረውት ለነበሩትም ሰዎች ሰጣቸው።”

27ደግሞም እንዲህ አላቸው፤ “ሰንበት ለሰው ተፈጠረ እንጂ፣ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፤ 28ስለዚህ የሰው ልጅ የሰንበት ጌታዋ ነው።”

Knijga O Kristu

Marko 2:1-28

Isus iscjeljuje uzetog čovjeka

(Mt 9:1-8; Lk 5:17-26)

1Nekoliko dana nakon toga vrati se u Kafarnaum, a vijest o njegovu dolasku brzo se pročuje gradom. 2U kući u kojoj je boravio okupilo se toliko ljudi da više nije bilo mjesta ni za koga, čak ni pred vratima. A on im je propovijedao Riječ. 3Uto dođu četvorica noseći uzetog čovjeka na nosilima. 4Kako nisu mogli kroz mnoštvo doći do Isusa, načine rupu u glinenom krovu nad njegovom glavom i spuste bolesnika na nosilima ravno pred Isusa. 5Kad Isus vidje njihovu vjeru, reče bolesniku: “Sinko, oprošteni su ti grijesi!”

6Ali neki židovski vjerski vođe koji su ondje sjedili rekoše u sebi: 7“Kako ovaj može tako govoriti! On huli! Tko može opraštati grijehe osim jedinoga Boga!”

8Isus duhom prozre njihove misli pa ih upita: “Zašto to smatrate hulom? 9Što je lakše reći uzetom čovjeku: ‘Grijesi su ti oprošteni’ ili ‘Ustani, uzmi svoja nosila i idi’? 10Dokazat ću vam da ja, Sin Čovječji, imam vlast na zemlji opraštati grijehe.” Okrene se zatim prema uzetome i reče: 11“Zapovijedam ti: ustani, uzmi nosila i idi kući!”

12Čovjek smjesta ustane, uzme nosila i iziđe naočigled mnoštvu. Svi su se divili i slavili Boga govoreći: “Takvo što još nikad nismo vidjeli!”

Isus poziva Levija

(Mt 9:9-13; Lk 5:27-32)

13Isus ponovno ode na obalu jezera. Poučavao je mnoštvo koje se okupilo oko njega. 14Prolazeći tuda, opazi Levija, Alfejeva sina, kako ubire porez te ga pozove: “Pođi sa mnom!” Levi ustane i pođe za njim.

15Dok je Isus poslije bio u kući za stolom, došli su brojni ubirači poreza i grešnici i pridružili se njemu i njegovim učenicima. Mnogo takvih bilo je među onima koji su išli za Isusom. 16No kad neki pismoznanci, farizeji, ugledaju Isusa kako jede s tim ozloglašenim ljudima, kazaše njegovim učenicima: “Zašto vaš učitelj jede s ubiračima poreza i drugim grešnicima?”

17Kad je Isus to čuo, reče im: “Ne treba liječnik zdravima, nego bolesnima. Nisam došao zvati pravednike, već grešnike.”

Rasprava o postu

(Mt 9:14-17; Lk 5:33-39)

18Ivanovi učenici i farizeji povremeno su postili. Jednoga dana neki ljudi dođu Isusu i upitaju ga: “Zašto Ivanovi učenici i farizeji poste, a tvoji učenici ne poste?”

19Isus im odgovori: “Mogu li uzvanici na svadbenoj večeri postiti dok su s mladoženjom? Ne mogu postiti dok je mladoženja s njima. 20Ali doći će dani kada će im ugrabiti mladoženju. Tada će postiti.

21Nitko ne krpa rupe na staroj odjeći zakrpom od još nesmočena platna. Zakrpa bi se skupila, razvukla tkaninu i napravila još veću rupu. 22Nitko ne ulijeva novo vino u stare mjehove jer bi se raspuknuli. Vino bi se prolilo, a mjehovi uništili. Novo se vino lijeva u nove mjehove.”

Rasprava o suboti

(Mt 12:1-8; Lk 6:1-5)

23Jedne su subote Isus i njegovi učenici prolazili poljem usjeva. Učenici počnu putem trgati klasje. 24Farizeji rekoše Isusu: “Zašto čine ono što je subotom zabranjeno? Zakonom je zabranjeno skupljati usjev subotom!”

25Ali Isus im odgovori: “Niste li nikada u Pismu čitali o tomu što je učinio kralj David kad su on i njegovi pratioci u nevolji ogladnjeli? 26Ušao je u Dom Božji 2:26 U Hram. Vidjeti 1 Samuelova 21:1-6. (u to je doba veliki svećenik bio Ebijatar) i jeo prineseni kruh koji je dopušteno jesti samo svećenicima te ga je dao jesti i svojim pratiocima. 27Subota je stvorena radi čovjeka, a ne čovjek radi subote. 28Ja, Sin Čovječji, gospodar sam čak i subote.”