ማርቆስ 3 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 3:1-35

1በሌላ ጊዜ ወደ ምኵራብ ገባ፤ በዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር። 2በምክንያት ሊከስሱት የሚፈልጉ ሰዎችም በሰንበት ቀን ይፈውሰው እንደ ሆነ ለማየት ይጠባበቁ ነበር። 3እርሱም እጁ የሰለለችውን ሰው፣ “በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ተነሥተህ ቁም” አለው።

4ኢየሱስም፣ “በሰንበት ቀን የተፈቀደው መልካም ማድረግ ነው ወይስ ክፉ? ሕይወት ማዳን ነውን ወይስ ማጥፋት?” አላቸው። እነርሱ ግን ዝም አሉ።

5በልባቸው ደንዳናነት ዐዝኖ በዙሪያው የቆሙትን በቍጣ ተመለከታቸውና ሰውየውን፣ “እጅህን ዘርጋ!” አለው፤ ሰውየውም እጁን ዘረጋ፤ እጁም ፍጹም ደኅና ሆነችለት።

6ፈሪሳውያንም እንዴት ሊያጠፉት እንደሚችሉ ከሄሮድስ ወገን ከሆኑት ጋር መመካከር ጀመሩ።

ብዙ ሰዎች ኢየሱስን ተከተሉ

3፥7-12 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥1516ሉቃ 6፥17-19

7ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባሕሩ ሄደ፤ ከገሊላ የመጣ እጅግ ብዙ ሕዝብም ተከተለው፤ 8የሚሠራውን ነገር የሰሙ ሰዎችም ከይሁዳ፣ ከኢየሩሳሌም፣ ከኤዶምያስ፣ በዮርዳኖስ ማዶ ካለው አገር እንዲሁም ከጢሮስና ከሲዶና አካባቢ ወደ እርሱ መጡ። 9የተሰበሰበውም ሕዝብ እንዳያጨናንቀው አነስተኛ የሆነ ጀልባ እንዲያዘጋጁለት ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው። 10ብዙዎችን ፈውሶ ስለ ነበር፣ በሕመም የሚሠቃዩ ሁሉ ሊዳስሱት ይሽቀዳደሙ ነበር። 11ርኩሳን3፥11 ወይም ክፉ፤ እንዲሁም 30 ይመ መናፍስትም ባዩት ቍጥር ከፊቱ እየወደቁ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” በማለት ይጮኹ ነበር። 12እርሱ ግን ማንነቱን እንዳይገልጹ አጥብቆ ይገሥጻቸው ነበር።

የዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት መሾም

3፥16-19 ተጓ ምብ – ማቴ 10፥2-4ሉቃ 6፥14-16ሐሥ 1፥13

13ኢየሱስ ወደ ተራራ ወጥቶ የሚፈልጋቸውን ወደ እርሱ እንዲመጡ ጠራቸው፤ እነርሱም ወደ እርሱ መጡ። 14ከእርሱ ጋር እንዲሆኑ፣ ለስብከትም ይልካቸው ዘንድ ዐሥራ ሁለቱን ሾማቸው፤ ሐዋርያትም ብሎ ጠራቸው3፥14 አንዳንድ ቅጆች ሐዋርያትም ብሎ ጠራቸው የሚለው ሐረግ የላቸውም።15አጋንንትን እንዲያስወጡም ሥልጣን ሰጣቸው። 16የሾማቸውም ዐሥራ ሁለቱ እነዚህ ናቸው፤ ጴጥሮስ ብሎ የጠራው ስምዖን፣ 17ቦአኔርጌስ ይኸውም፣ “የነጐድጓድ ልጆች” ብሎ የጠራቸው የዘብዴዎስ ልጆች ያዕቆብና ወንድሙ ዮሐንስ፤ 18እንድርያስ፣ ፊልጶስ፣ በርተሎሜዎስ፣ ማቴዎስ፣ ቶማስ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ታዴዎስ፣ ተቀናቃኙ ስምዖን፣ 19እንዲሁም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።

ኢየሱስና ብዔልዜቡል

3፥23-27 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥25-29ሉቃ 11፥17-22

20ከዚያም ኢየሱስ ወደ አንድ ቤት ገባ፤ እርሱና ደቀ መዛሙርቱ ምግብ መብላት እንኳ እስኪሳናቸው ድረስ ሕዝቡ እንደ ገና በብዛት ተሰበሰበ። 21ሁኔታውን የሰሙ ዘመዶቹም፣ “አእምሮውን ስቷል” በማለት ይዘውት ለመሄድ ወዳለበት መጡ።

22ከኢየሩሳሌም የመጡ ጸሐፍትም፣ “ብዔልዜቡል3፥22 ግሪኩ ብዔዜቡል ወይም ብዔልዜቡል ይላል። ዐድሮበታል፤ አጋንንትን የሚያወጣው በአጋንንት አለቃ ነው” አሉ።

23እርሱም ጠራቸውና በምሳሌ እንዲህ አላቸው፤ “ሰይጣን ሰይጣንን እንዴት ሊያስወጣ ይችላል? 24እርስ በርሱ የሚከፋፈል መንግሥት ሊጸና አይችልም፤ 25ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ሊቆም አይችልም። 26እንደዚሁም ሰይጣን እርስ በርሱ የሚፃረርና የሚከፋፈል ከሆነ ሊቆም አይችልም፤ ያበቃለታል። 27ከዚህም የተነሣ አንድ ሰው አስቀድሞ ኀይለኛውን ሰው ሳያስር ወደ ኀይለኛው ሰው ቤት ሊገባና ንብረቱን ሊዘርፍ አይችልም፤ ቤቱን መዝረፍ የሚቻለው ኀይለኛውን ሰው ሲያስር ብቻ ነው። 28እውነት እላችኋለሁ፤ የሰው ልጆች ኀጢአትና የሚሳደቡት ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤ 29ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የሚናገር ሁሉ የዘላለም ኀጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።”

30ይህንም ያለው፣ “ርኩስ መንፈስ አለበት” ስላሉት ነበር።

የኢየሱስ እናትና ወንድሞቹ

3፥31-35 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥46-50ሉቃ 8፥19-21

31ከዚህ በኋላ እናቱና ወንድሞቹ መጡ፤ በውጭ ቆመውም ሰው ልከውበት አስጠሩት። 32በዙሪያው የተቀመጡ ብዙ ሰዎችም፣ “እነሆ፤ እናትህና ወንድሞችህ ውጭ ይፈልጉሃል” አሉት።

33እርሱም መልሶ፣ “እናቴ ማን ናት፣ ወንድሞቼስ እነማን ናቸው?” አላቸው።

34በዙሪያው ወደ ተቀመጡትም በመመልከት፣ እንዲህ አለ፤ “እናቴና ወንድሞቼ እነዚህ ናቸው! 35የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ፣ እኅቴ፣ እናቴም ነውና።”

Knijga O Kristu

Marko 3:1-35

Isus iscjeljuje u subotu

(Mt 12:9-14; Lk 6:6-11)

1Isus ponovno ode u tamošnju sinagogu. Ondje je bio neki čovjek usahnule ruke. 2Isusovi neprijatelji budno su pazili hoće li mu iscijeliti ruku u subotu da ga mogu optužiti. 3Isus reče čovjeku usahnule ruke: “Ustani i dođi ovamo na sredinu!”

4Zatim ih upita: “Je li subotom dopušteno činiti dobro ili zlo, život spasiti ili pogubiti?” Šutjeli su. 5Srdito ih pogleda duboko ožalošćen tvrdoćom njihovih srca te reče čovjeku: “Ispruži ruku!” On ju ispruži, a ruka mu postane zdrava. 6Farizeji se smjesta odu dogovoriti s herodovcima da ga smaknu.

Mnoštvo slijedi Isusa

(Mt 4:23-25; 12:15-16; Lk 6:17-19)

7Isus i njegovi učenici odu na jezero, a za njima krene veliko mnoštvo iz cijele Galileje, Judeje, 8Jeruzalema, Idumeje, s istočne strane Jordana, čak i iz okolice Tira i Sidona. Vijest o čudima koje je činio nadaleko se pročula, pa su ga dolazili osobno vidjeti.

9Isus reče učenicima da mu dovezu čamac koji će biti spreman ako se mnoštvo previše natisne oko njega. 10Toga je dana mnoge iscijelio pa je na njega nahrupilo golemo mnoštvo bolesnika pokušavajući ga dotaknuti. 11Kad bi ga vidjeli ljudi opsjednuti nečistim duhom, pali bi pred njim ničice i vikali: “Ti si Božji Sin!” 12A on im je oštro zabranjivao da ga očituju.

Isus izabira dvanaestoricu apostola

(Mt 10:1-4; Lk 6:12-16; Djela 1:13)

13Zatim ode u goru i pozove one koje je izabrao da mu se ondje pridruže te oni dođu. 14Od njih odabere dvanaestoricu da ga prate i imenuje ih apostolima. Njih je poslao da propovijedau 15i da imaju vlast istjerivati zloduhe. 16Evo imena Dvanaestorice što ih je izabrao:

Šimun (kojemu je nadjenuo ime Petar),

17Jakov i Ivan (Zebedejevi sinovi, kojima je Isus dao nadimak Boanerges, to jest “Sinovi groma”),

18Andrija,

Filip,

Bartolomej,

Matej,

Toma,

Jakov (Alfejev sin),

Tadej,

Šimun (član političke stranke koja se zalagala za nasilno svrgavanje rimske vlasti) i

19Juda Iškariotski (koji ga je poslije izdao).

Isus i knez zloduha

(Mt 12:22-29; Lk 11:14-23; 12:10)

20Kad se vratio u dom gdje je boravio, opet je nagrnulo toliko mnoštvo da nisu stigli ni jesti. 21Kad su za to čuli njegovi, dođu ga odvesti jer su govorili da je izvan sebe. 22Ali pismoznanci što su došli iz Jeruzalema rekoše da ga je opsjeo Beelzebub, poglavica zlih duhova, pa da uz njegovu pomoć izgoni zloduhe.

23Isus dozove ljude i počne im govoriti u prispodobama: “Kako može Sotona izgoniti Sotonu? 24Kraljevstvo koje je u sebi podvojeno propast će. 25Dom u kojemu vlada nesloga ne može opstati. 26Ako se dakle Sotona bori sam protiv sebe, kako će se onda održati? Ne bi uspio u tome. 27Ne možete ući u kuću snažnog čovjeka i opljačkati ga a da ga najprije ne svežete. Tek tada ga možete orobiti.

28Zaista vam kažem da se svaki ljudski grijeh može oprostiti, pa čak i hula. 29Ali hula na Svetoga Duha nikad se ne može oprostiti. To je vječni grijeh.”

30To im reče jer su govorili da ima nečistog duha.

Prava Isusova obitelj

(Mt 12:46-50; Lk 8:19-21)

31Stigli su onamo njegova majka i braća, stajali vani te mu po nekim ljudima poručili da iziđe razgovarati s njima. 32Oko njega je sjedilo mnoštvo kad mu rekoše: “Vani su ti majka, braća i sestre, žele te vidjeti.”

33On im odgovori: “Tko mi je majka? Tko su mi braća?” 34Pogleda ljude koji su sjedili u krugu oko njega, pa reče: “Ovo su mi majka i braća! 35Zaista, tko god čini Božju volju, taj mi je i brat, i sestra i majka.”